Search Results for 'አሚር አማን'

Home Forums Search Search Results for 'አሚር አማን'

Viewing 11 results - 1 through 11 (of 11 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ዘንድሮ ለሰባተኛ የተለያዩ ኢትዮጵያውያንን የሸለመው የ2011 ዓ.ም. የበጎ ሰው ሽልማት ሥነ ሥርዓት በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ (ካዛንችስ፣ አዲስ አበባ) ተካሂዷል።

    በሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዴሪ) ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እና የኢፌዴሪ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማንን ጨምሮ የተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

    ለዘንድሮው የበጎ ሰው ሽልማት በዘጠኝ ዘርፎች 291 ሰዎች ከሕዝብ ዘንድ ተጠቁመው የነበረ ሲሆን፤ ከእነዚህም ውስጥ 27ቱ ተመርጠው ለመጨረሻ ዕጩነት (በዘጠኝ ዘርፎች፣ በእያንዳንዱ ዘርፍ ሦስት ሦስት ዕጩዎች) ቀርበው ኢትዮጵያውያን አሸናፊዎችን እንዲመርጡ ተደርጎ ነበር

    ነሐሴ 26 ቀን 2011 ዓ.ም. በእያንዳንዱ ዘርፍ ከቀረቡት ዕጩዎች ውስጥ የመጨረሻ ተሸላሚዎች ይፋ ተደርገዋል። በዚህም መሠረት አሸናፊዎቹ የሚከተሉት ናቸው።

    በመምህርነት ዘርፍ

    • ወ/ሮ ህይወት ወልደመስቀል

    በሳይንስ (ህክምና፣ ቴክኖሎጂ፣ ፊዚክስ፣ ምህንድስና፣ ኬሚስትሪ፣ አርክቴክቸር፣ ወዘተ)

    • ፕሮፌሰር ሰብስቤ ደምሴ (አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በ አትክልት ምርምር ፕሮፌሰር፣ የጎለሌ ዕፅዋት ማዕከል የበላይ ኃላፊ፣ በሀገረ እንግሊዝ የተከበረው KEW International ሜዳል ተሸላሚ)

    በኪነ ጥበብ፣ ሥነ ጥበብ እና በፎቶ ግራፍ ዘርፍ

    • አቶ በዛብህ አብተው (ኢትዮጵያ ውስጥ የመጀመሪያው የስፖርት ፎቶግራፍ አንሺ)

    በበጎ አድራጎት (እርዳታ እና ሰብዓዊ አገልግሎቶች)

    • አቶ አብድላዚዝ አህመድ

    በንግድና ሥራ ፈጠራ ዘርፍ

    • አቶ ነጋ ቦንገር (የነጋ ቦንገር ሆቴል፣ እንዲሁም አዲስ አበባ ውስጥ የተለያዩ የንግድ ተቋማት ምሥራች እና ባለቤት)

    በመንግሥታዊ የሥራ ተቋማት ኃላፊነት

    • አቶ ግርማ ወንዳፍራሽ

    በቅርስና ባህል ዘርፍ

    • አቶ አብዱልፈታህ አብደላ (የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦችን የባህላዊ ዳኝነትና የፍትህ ሥርዓቶችን በመጻፍ የሚታወቁ)

    በሚዲያና ጋዜጠኝነት

    • አቶ አማረ አረጋዊ (ሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር በስሩ የሚታተመው ሪፖርተር ኢትዮጵያ (የአማርኛ እና የእንግሊዝኛ) ጋዜጣ መሥራች)

    በኢትዮጵያ እድገት አስተዋፅኦ ያበረከቱ ዲያስፖራዎች

    • አቶ ኦባንግ ሜቶ (ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) መሥራች እና ሊቀ-መንበር)

    የሰባተኛው የበጎ ሰው ሽልማት ልዩ የክብር ተሸላሚዎች

    • የጋሞ ሽማግሌዎች (በቡራዩ የተከሰተውን ግድያ በመቃወም በአርባ ምንጫ የተቃውሞ ሠልፍ ላይ፣ በቁጣ ንብረት ለማውደም የቃጡ ወጣቶች እንደነበሩ የሚታወስ ሲሆን፣ አንደ አካባቢው ባሕል ሣር ይዘው በአካላቸው ቆመው ንብረቱን ከጥፋት የተከላከሉት የጋሞ ሀገር ሽማግሌዎች ነበሩ።)

    በሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የ2011 ዓ.ም. የበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚዎችን እንኳን ደስ አላቸሁ ብለዋል። ሀገር በትውልድ ቅብብሎሽ የምትገነባ መሆኑን የገለጹት ፕሬዝደንቷ፥ የበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚዎች ለነገው ትውልድ ተረካቢዎች አርዓያ የሚሆን ሥራ በመሥራታቸው ሊደነቁ ይገባል በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

    በ2005 ዓ.ም. በዲያቆን ዳንኤል ክብረት የተቋቋመው የበጎ ሰው ሽልማት ዋና ዓላማ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵይውያን በጎ ሥራን የሠሩ እና ለሌሎች አርዓያ ሊሆኑ የሚችሉ ግለሰቦችን ማበረታታት እና ዕውቅና መስጠት ነው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    The 7th edition of Bego Sew Award የበጎ ሰው ሽልማት


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ የሚካሄደው ዓመታዊው የበጎ ሰው ሽልማት ከግንቦት 4 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ሰኔ 3 ቀን 2011 ዓ.ም. ድረስ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ዕጩዎችን ሲጠቁሙ እንደነበር ይታወሳል።

    በዚህ በተጠቀሰው የጊዘ ገደብ ውስጥም በ አጠቃላይ 291 ሰዎች ተጠቁመው 27 ዕጩዎች ለዳኞች ውሳኔ ቀርበዋል ለመጨረሻው የዳኞች ውሳኔ መቅረባቸውን የበጎ ሰው ሽልማት አስተባባሪዎች በቅርቡ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል።

    እንደወትሮው ሁሉ በሽልማቱ ዕጩዎች የተጠቆሙባቸውና ሽልማት የሚያሰጡት አስር የተለያዩ ዘርፎች ናቸው። በእያንዳንዱ የሽልማት ዘርፍ የቀረቡት ዕጩዎች የሚከተሉት ናቸው።

    በመምህርነት ዘርፍ

    1. ፕሮፌሰር ሽታዬ ዓለሙ ባልቻ (ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ)
    2. ወ/ሮ ህይወት ወልደመስቀል
    3. ዶ/ር መስከረም ለቺሳ ደበሌ (ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትምህርት እና ሥነ-ባህሪ ኮሌጅ)

    በሳይንስ (ህክምና፣ ቴክኖሎጂ፣ ፊዚክስ፣ ምህንድስና፣ ኬሚስትሪ፣ አርክቴክቸር፣ ወዘተ)

    1. ፕሮፌሰር ለገሰ ነጋሽ
    2. ፕሮፌሰር ሰብስቤ ደምሴ
    3. ዶ/ር ታደለች አቶምሳ

    በኪነ ጥበብ፣ ሥነ ጥበብ እና በፎቶ ግራፍ ዘርፍ

    1. አቶ ሚካኤል ፀጋዬ
    2. አቶ በዛብህ አብተው
    3. አቶ ዳኜ አበራ

    በበጎ አድራጎት (እርዳታ እና ሰብዓዊ አገልግሎቶች)

    1. ዶ/ር ጀምበር ተረፈ
    2. አቶ አብድላዚዝ አህመድ
    3. አቶ ላሌ ለቡኮ

    በንግድና ሥራ ፈጠራ ዘርፍ

    1. አቶ ዳንኤል መብራቱ
    2. አቶ ክቡር ገና
    3. አቶ ነጋ ቦንገር

    በመንግሥታዊ የሥራ ተቋማት ኃላፊነት

    1. አቶ በትሩ አድማሴ (ኢትዮጵያ ውስጥ የመጀመሪያው የቴሌኮሚዩኒኬሽን ሚኒስትር የነበሩ)
    2. ዶ/ር አሚር አማን (የአሁኑ የጤና ሚኒስትር)
    3. አቶ ግርማ ወንዳፍራሽ

    በቅርስና ባህል ዘርፍ

    1. አቶ አብዱልፈታህ አብደላ (የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦችን የባህላዊ ዳኝነትና የፍትህ ሥርዓቶችን በመጻፍ የሚታወቁ)
    2. አርሶ አደር አቶ አድማሴ መላኩ (በምስራቅ ጎጃም ዞን በጮቄ ተራራ አካባቢ የሚገኘውን ‹‹አባ ጃሜህ›› ደን ለ52 ዓመታት በግል ተነሳሽነት ሲጠብቁና ሲንከባከቡ የነበሩ)
    3. ሳሙኤል መኮነን (ከጎንደር)

    በሚዲያና ጋዜጠኝነት

    1. አቶ በልሁ ተረፈ
    2. አቶ አማረ አረጋዊ
    3. ወ/ሮ አንድነት አማረ

    በኢትዮጵያ እድገት አስተዋፅኦ ያበረከቱ ዲያስፖራዎች

    1. አቶ ኦባንግ ሜቶ
    2. አርቲስት ታማኝ በየነ
    3. ፕሮፌሰር ፀጋዬ ታደሰ

    በተጠቀሱት የሽልማት ዘርፎች ከእያንዳንዳቸው አንደኛ ሆነው የሚመረጡት ዕጩዎች በተመረጡበት ዘርፍ የ2011 ዓ.ም. የበጎ ሰው ሽልማት አሸናፊ ተብለው ነሐሴ 26 ቀን 2011 ዓ.ም. ኢንተርኮንቲነንታል ሆቴል (ካዛንችስ፣ አዲስ አበባ) አዳራሽ ውስጥ በሚደረገው የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ ይሸለማሉ።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የበጎ ሰው ሽልማት


    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ  (ኢፌዴሪ) መንግስት ከኔዘርላንድ መንግስት በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ የሕፃናት ሆስፒታል ለመገንባት የሚውል የ27.44 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ ስምምነት ተፈራርሟል። በተጨማሪም የአደጋ (trauma) ሕክምና መስጫ ማዕከል ይገነባል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) የኢትዮጵያ መንግስት ከኔዘርላንድ መንግስት ጋር በመተባበር ከ1.8 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ በአለርቲ ሆስፒታል ግቢ ውስጥ በአይነቱ ልዩ እና የመጀመሪያ የሆነ አዲስ የሕፃናት አጠቃላይ ሆስፒታል ለመገንባት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ።

    የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስትር ድኤታ ዶ/ር ሊያ ታደሰ በፊርማ ሥነ ስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት፥ በሕፃናት ዙሪያ የሚሰጡ የሕክምና አገልግሎቶችን ማሻሻልና ማዘመን አስፈላጊ ከመሆኑ አንጻር ሆስፒታሉ በሕፃናት ዙሪያ ያሉትን ችግሮች ለመቅረፍ የልብ፣ የነርቭ፣ የኩላሊት እንዲሁም ከ30 በላይ የሚደርሱ የሕክምና ስፔሻሊቲ አገልግሎት እንደሚኖሩት ተናግረዋል።

    በአለርት ሆስፒታል ውስጥ የሚገነባው የሕፃናት አጠቃላይ ሆስፒታል በሁለት አመት እንደሚጠናቀቅና 317 አልጋዎች እንደሚኖሩት ወጪውም በኔዘርላንድ መንግስት፣ በአሜርካን ፋውንደሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት እንደሚሸፍን በፊርማ ሥነ ስርዓቱ ላይ ተገልጧል።

    ከዚሁ ዜና ጋር በተያያዘ፥ የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የአደጋ (trauma) ሕክምና መስጫ ሆስፒታልን ለመገንባት ከእቴቴ ኮንስትራክሽን ድርጅት ጋር ሚያዝያ 2 ቀን 2011 ዓ.ም. ውል ተፈራርሟል።

    ጤና ሚኒስቴር ከእቴቴ የኮንስትራክሽን ድርጅት ጋር ውል በተፈራረሙበት ወቅት የጤና ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን እንደተናገሩት፥ በተለያዩ ምክንያቶች የሚከሰቱና ለህመም፣ ለአካል ጉዳት እና ለሞት የሚያጋልጡ አደጋዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ በመምጣታቸው በዚህ ዙሪያ የሚሰጡ የሕክምና አገልግሎቶችን ማሻሻልና ማዘመን አስፈላጊ በመሆኑ በድንገተኛ አደጋዎችና ተጓዳኝ ሕክምናዎችን የሚሰጥ ማዕከል በአዲስ አበባ ከተማ አለርት ሆስፒታል ውስጥ ይገነባል ብለዋል።

    ከ751 ሚሊዮን ብር በላይ የተመደበለት እና ባለ 8 ፎቅ የሚገነባለት ይህ ማዕከል በ3 ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ የታሰበ ሲሆን፤ ከ550 በላይ አልጋዎች የሚኖረውና በቀን ከ2000 እስከ 5000 ተገልጋዮችን ማስተናገድ የሚችል እንደሚሆን ሚኒስትሩ ጨምረው ተናግረዋል።

    የግንባታው በጀት ሙሉ በሙሉ ከመንግስት በመሆኑና ተቋራጩም በተለያዩ የግንባታ ሥራዎች ሰፊ ልምድ ያለው በመሆኑ በግንባታ ሂደቱ ወቅት ያጋጥማል ተብሎ የሚያሳስብ ችግር የለም ተብሏል።

    ምንጭ፦ ጤና ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    የሕፃናት ሆስፒታል


    Semonegna
    Keymaster

    በኢትዮጵያ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ተግባራዊ የሚሆን አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች በተገኙበት ዛሬ ይፋ ሆነ።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ አንዲት አገር በዓለም አቀፍ የጤና ህግጋት ላይ የተጠቀሱትን መሠረታዊ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችንና አደጋዎችን ለመከላከል፣ አስቀድሞ ለመለየትና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል አቅም ለማጠናከር የተቀመጡ ግቦችን እንድታሟላ የሚያስችል ዕቅድ ሲሆን በሃገሪቱ ሙሉ ባለቤትነት የሚቀረጽ የትግበራ ዕቅድ ነው።

    ማንኛውም የዓለም አቀፍ የጤና ሕግጋት ፈራሚ አገር ይህንን ዕቅድ እንደሚያዘጋጅ ሁሉ ኢትዮጵያም የዚህ ስምምነት ፈራሚ እንደመሆኗ በተደጋጋሚ የሚገጥሟትን የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎችን ለመቋቋም የሚያስፈልጓትን አቅም ለመገንባት ዕቅዱን ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኗል።

    የትግበራ ዕቅዱን በአዲስ አበባ በይፋ መጀመሩን ያበሰሩት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር  አቶመቀ መኮንን፥ ስለ አንድ አገር ሰላምና ደህንነት ስንናገር የሕዝቦቻችንን የጤና ደህንነት ጭምር አያይዘን እንደምንናገር መገንዘብ እንደሚገባ ጠቁመው፥ አገራዊ ዕቅዱ ወቅታዊና እንደአገር የሚያጋጥሙንን ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ቀድሞ ለመከላከልና ብዙ ጉዳት ሳያደርሱ ምላሽ ለመስጠት ያስችለናል ብለዋል።

    ◌ SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest

    የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን በበኩላቸው ሃገሪቱ እ.ኤ.አ በ2016 የዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ከአፍሪካ ቢሮ በመጡ ገምጋሚዎች የጤና ደህንነቷ ያለበትን ደረጃ ማስመዘኗን ገልጸው፥ ከግምገማው በተገኙ ግብረ መልሶች እና በሃገሪቱ ከተከሰቱ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ምላሽ አሰጣጣችን የተግባር ልምድ በመውሰድ አገራዊ የጤና ትግበራ ዕቅድ አዘጋጅታለች ብለዋል።

    የትግበራ ዕቅዱን ለመፈጸም በጀት ስለሚጠይቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ያለንን ሃብት አቀናጅተን በመጠቀም ለዕቅዱ መሳካት የበኩላችንን ድርሻ መወጣት ይገባናል ያሉት ደግሞ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ዶ/ር ፓሚላ ሙቱሪ ናቸው።

    የኢትዮጵይ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኤባ አባተ በበኩላቸው፥ እንደ ኩፍኝና ቢጫ ወባን የመሳሰሉ ወረርሽኞችን ለመከላከልና በዓለም ደረጃ ለሚከሰቱ እንደ ኢቦላ እና ዚካ ቫይረስ ያሉ ወረርሽኞችን ለመከላከል አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።

    ለዕቅዱ ትግበራ 368 ሚሊዮን 764 ሺህ 777 ዶላር የሚያስፈልግ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 77 በመቶ የሚሆነው የክትባት ሽፋንን ለማሳደግ የሚውል ይሆናል።

    አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅዱ ለአምስት ዓመት ማለትም ከ2011/12 እስከ 2016/17 ዓ.ም ድረስ የሚተገበር ይሆናል።

    ምንጭ፦ የጤና ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አገራዊ የጤና ደህንነት


    Semonegna
    Keymaster

    እ.ኤ.አ ከ2019 እስከ 2023 ለሚተገበረው አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ 10 ቢሊዮን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን፥ ወጪው ከኢትዮጵያ መንግሥት፣ ከልማት አጋሮችና ባለድርሻ አካላት እንደሚሰባሰብ ለማወቅ ተችሏል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – በኢትዮጵያ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ተግባራዊ የሚሆን አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች በተገኙበት ዛሬ ይፋ ሆነ።

    በዚህ ወቅት እንደተገለጸው፥ አገሪቷ መከላከልን መሠረት ያደረገ ስልት ቀይሳ የምታደርገውን ጥረት በጉልህ ይደግፋል። በተለይም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ አካባቢዎች በተፈጠሩ አለመረጋጋት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ተላላፊ ለሆኑ በሽታዎች እንዳይጋለጡ አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችል ነው።

    እ.ኤ.አ ከ2019 እስከ 2023 ለሚተገበረው አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ 10 ቢሊዮን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን፥ ወጪው ከኢትዮጵያ መንግሥት፣ ከልማት አጋሮችና ባለድርሻ አካላት እንደሚሰባሰብ ለማወቅ ተችሏል።

    የጤና ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን እንደተናገሩት፥ በዕቅድ ዝግጅቱ የሚመለከታቸው መሥሪያ ቤቶች ተሳትፎ አድርገዋል።

    አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ ችገሮች ከመከሰታቸው በፊት አስቀድሞ በመለየት መከላከል፣ ችግሮች ሲከሰቱ ፈጣን ምላሽ መስጠት በኅብረተሰቡ ላይ በህመምና በሞት የከፋ ጉዳት ሳይደርስ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ስትራቴጂ ነው።

    ◌ SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest

    ባለፉት ሁለት ዓመታት የጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵይ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) ጋር በመሆን ዕቅዱን ዝግጅት ሲደረግ እንደነበረ ዶ/ር አሚር ገልጸው፥ አገሪቷ በዘርፉ ምን ክፍተት አለባት? የሚለውን በጥናት ላይ የተመሰረተ ሥራ መከናወኑን አስረድተዋል። እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፥ ዕቅዱ ከመዘጋጀቱ በፊት አገር አቀፍ የዳሰሳ ጥናት ተካሂዷል።

    ዶ/ር አሚር እንደሚሉት፥ በጥናቱ መሠረት ዝቅተኛ አፈጻጸም የታየበት አደጋ ሲከሰት ፈጣን ምላሽ መስጠት መሆኑ የተለየ ሲሆን ችግሩን ለመፍታት በሁለቱ ከተማ መስተዳደሮችና በዘጠኙ ክልሎች ማዕከላት ተቋቁሟል።

    ከኬሚካልና ጨረር ጋር በተያያዘ አደጋ ቢያጋጥም ምላሽ ለመስጠት በቂ ዝግጅት እንደሌለ በጥናት የተለየ ሌላው ችግር መሆኑን ጠቁመው በዚህም ላይ የማስተካከያ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አብራርተዋል።

    በዕቅዱ ላይ እንደ ክፍተት የተቀመጡ ችግሮችን ለመፍታት መንግሥት 25 ሚሊዮን ዶላር በመመደብ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጸዋል።

    የኢትዮጵይ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኤባ አባተ በበኩላቸው፥ አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅዱ በአገሪቷ ተላላፊ በሽታዎችና ወረርሽኝን አስቀድሞ ለመግታት ወሳኝ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።

    ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በዚሁ ወቅት እንደገለጹትዕ አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅዱ ወቅታዊና አስፈላጊ ነው። አደጋዎችን ቀድሞ የመከላከል፣ ብዙ ጉዳት ሳያደርሱ የመቆጣጠርና መልሶ የማገገምና እንዳይደገም የማድረግን አቅምን መገንባት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ


    Semonegna
    Keymaster

    “በርቱ! ባየሁት ነገር ተደስቻለሁ… የሥራ ፍላጎት ተነሳሽነት ለለውጥ ወሳኝ መሆኑን ከጴጥሮስ መረዳት እንችላለን” – የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ገብረየሱስ 

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ገብረየሱስ የካቲት 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተገኘተው የሥራ እንቅስቃሴን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

    በቆይታቸውም የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልና የቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ በጋራ ያስገነቡትን የልብ ህክምና ማዕከል፣ በሀገሪቱ ብቸኛና የመጀመሪያ የሆነውን የተመረዙ ሰዎች የሚታከሙበት የቶክሲኮሎጂ ህክምና ማዕከል እንዲሁም የእናቶችና ህጻናት የህክምና ከፍልን ዋና ዳይሬክተሩ ጎብኝተዋል።

    በሆስፒታሉ ፈጣን እድገት ተደስቻለሁ ያሉት ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የልብ ህክምና አገልግሎት መስጠት መጀመሩና በሀገሪቱ ካለው የህክምና እጥረት አኳያ ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልጸው ብዙም ትኩረት ያልተሰጠበት የመመረዝ ህክምና በሆስፒታሉ መሰጠቱም ይበል የሚያሰኝ ነው ብለዋል።

    ቪዲዮ፦ የኢትዮጵያዊያን-አሜሪካዊያን ዶክተሮች ቡድን እያስገነባ ያለው ግዙፉ ዓለምአቀፋዊ ሆስፒታል በአዲስ አበባ

    ሆስፒታሉ የሰሳንባ ነቀርሳ (ቲቢ) ህክምና ብቻ ይሰጥ እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር ቴዎድሮስ በአሁኑ ሰዓት አጠቃላይ መሠረታዊ የሆስፒታል አገልግሎቶችን መስጠት መጀመሩና የተወሰኑ የህክምና አገልግሎቶች ላይም የበለጠ ስፔሻላይዝድ ለማድረግ መሥራቱ በጣም እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል።

    ከዚህ ሌላም የሆስፒታሉ ሰራተኞች የሥራ ተነሳሽነትም በጣም እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል። ለሆስፒታሉ ፈጣን ዕድገትም ሁሉም የሆስፒታሉ ሠራተኞች ዋና ተዋናይ መሆናቸውን እንዳዩ ገልጸው በዚህም የሥራ ፍላጎት መኖር ለለውጥ ወሳኝ መሆኑን ከጴጥሮስ መረዳት እንችላለን ብለዋል።

    የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በዚሁ ዕለት የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን ከመጎብኘታቸው በተጨማሪም ከየኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዴሪ) የጤና ሚኒስትር አሚር አማን (ዶ/ር) እንዲሁም ከኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ጋር ተገናኝትው በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።

    ከሰኔ 24 ቀን 2009 ዓ.ም. ቀን ጀምሮ ዋና መቀመጫው ጄነቭ፣ ስዊዘርላንድ የሆነውን የዓለም ጤና ድርጅትን (WHO) በዋና ዳይረክተርነት የሚመሩት ኢትዮጵያዊው ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከዚህ ስልጣናቸው በፊት ከ ከኅዳር 20 ቀን 2005 ዓ.ም. እስከ ጥቅምት 22 ቀን 2009 ዓ.ም. ድረስ የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ከጥቅምት 2 ቀን 1998ዓ.ም. እስከ ኅዳር 19 ቀን 2005 ዓ.ም. ደግሞ የኢፌዴሪ የጤና ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።

    ምንጭ፦ የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

     

    የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም


    Semonegna
    Keymaster

    በአስር ሺህ ካሬ ሜትር ላይ በ58 ሚሊዮን ብር ወጪ በአዳማ ከተማ የተገነባዉ ጊዜ ያለፈባቸው እና ጥቅም ላይ የማይውሉ መድኃኒቶችን ማስወገጃ ማዕከል 10 ሺህ ኪሎ ግራም በሰዓት የማቃጠል አቅም ያለው ሲሆን፥ በሌሎች 7 ከተሞችም 500 ኪሎ ግራም በሰዓት ማቃጠል የሚችሉ ማዕከላትም በመገንባት ላይ ይገኛሉ።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ የመድኃኒት ፈንድና አቅርቦት ኤጀንሲ በ100 ቀናት ዕቅድ የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው እና በተለያዩ ምክንያቶች ጥቅም ላይ የማይውሉ መድኃኒቶችን እና የህክምና ግብአቶችን ማስወገጃ ማዕከል ገንብቶ አስመረቀ።

    በአስር ሺህ ካሬ ሜትር ላይ በ58 ሚሊዮን ብር ወጪ በአዳማ ከተማ የተገነባዉ ጊዜ ያለፈባቸው እና ጥቅም ላይ የማይውሉ መድኃኒቶችን ማስወገጃ ማዕከል (incinerator) ምረቃ ሥነ ስርዓትላይ የተገኙት የኢፌዴሪ የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን እንደተናገሩት፥ ማዕከሉ 10 ሺህ ኪሎ ግራም በሰዓት የማቃጠል አቅም ያለው ሲሆን፥ በሌሎች 7 ከተሞችም 500 ኪሎ ግራም በሰዓት ማቃጠል የሚችሉ ማዕከላትም በመገንባት ላይ ይገኛሉ ብለዋል። በቅርቡም ግንባታቸው ተጠናቆ አገልግሎት እንደሚጀምሩ ዶ/ር አሚር አክለው ተናግረዋል።

    ጊዜ ያለፈባቸው መድኃኒቶች እና ግብዓቶች ማስወገጃ ማዕከሉ ለሀገራችን የመጀመሪያ ሲሆን ከዚሀ ቀደም በየተቋሟቱ በተለያዩ ምክንያቶች ጥቅም ላይ የማይውሉ ወይም የተበላሹ መድኃኒቶችን በማስወገድ ረገድ ይገጥሙ የነበሩ ችግሮችን ከመሠረቱ እንደሚፈታ የገለጹት ሚኒስትሩ፥ የምለሳ ሎጂስቲክ (recycle logistic) ስርዓትን በመተግበር የማያገለግሉ የህክምና ግብአቶች እና በባኅሪያቸው ጎጂ የሆኑ ኬሚካሎችን በዘመናዊ መንገድ አካባቢን በማይበክል ሁኔታ በማስወገድ ከዚህ ቀደም አካባቢ የሚበከልበትን ሁኔታ እንደሚያስቀር ተናግረዋል።

    የኢትዮ-አሜሪካውያን ዶክተሮች ቡድን እያስገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አገልግሎት ይሰጣል ተብሎ የሚጠበቀው ሆስፒታል

    ለዚህ ሥራ መሳካት ተባባሪ የሆኑ ያካባቢው ማኅበረሰብ አባላትና የአዳማ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤትን ያመሰገኑት ሚኒስትሩ፥ ማዕከሉ ለአካባቢ ነዋሪዎች ቅድሚያ ተጠቃሚ የሚያደረግ ስልጠናና የሥራ ዕድል በኤጀንሲው እንዲመቻችላቸውም ተናግረዋል።

    የኢትዮጵያ የመድኃኒት ፈንድና አቅርቦት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬከተር ዶ/ር ሎኮ አብርሀም በበኩላቸው የአዳማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በሌላው ዓለም የሚተገበሩ ዘመናዊ አሠራሮችን በመቀመር የመድኃኒት እና የህክምና መገልገያ አቅርቦት እና ስርጭት የልህቀት ማዕከል ሆኖ ለሌሎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች መማማሪያ እንዲሆን ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን ተናግረው ለአካባቢው፥ ማኅበረሰብም የሥራ ዕድል እየፈጠረ እንደሆነ እና በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    መድኃኒቶችን ማስወገጃ


    Semonegna
    Keymaster

    ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የ2011ዓ.ም. አዲስ ገቢ ተማሪዎችን በታህሳስ ወር መጨረሻ ላይ ለመቀበል ቅድመ ዝግጅት መጨረሱን ገለጸ። ዩኒቨርሲቲ አዲስ እንደመሆኑ መጠን ራሱን ለማስፋፋት ያስችለው ዘንድ መምህራንን እና ሠራተኞችን በስፋት እየቀጠረ ነው።

    አሰበ ተፈሪ (ሰሞነኛ) – ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የ2011ዓ.ም. አዲስ ገቢ ተማሪዎችን በታህሳስ ወር መጨረሻ ላይ ለመቀበል ቅድመ ዝግጅት መጨረሱን ገለጸ።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙክታር ሙሀመድ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው በ2010ዓ.ም. ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ ተቀብሎ ማስተማር የጀመረ ሲሆን፥ በማስፋፊያ ግንባታ መዘግየት ምክንያት በ2011ዓ.ም. የተመደቡትን ተማሪዎች እስካሁን ድረስ ጥሪ ያላደረገ አብራርተው በዚህ ወር መጨረሻ ግን ለተማሪዎቹ ጥሪ እንደሚያደርግ ገለጸዋል።

    የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ግርማ መኮንን በበኩላቸው የተማሪዎች የመኖሪያ ቤቶች (ዶርምተሪ) ግንባታ እየተጠናቀቀ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ 15 ቀናት ውስጥ በማስታወቂያ ለተማሪዎቹ ጥሪ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

    የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የጤና እና የህክምና ሳይንስ ኮሌጅ የህክምና ዶክተሮችን ጨምሮ 220 የጤና ባለሞያዎችን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን በተገኙበት ዛሬ አስመርቋል።

    ከዚሁ ጋር በተያያዘ ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ አዲስ እንደመሆኑ መጠን ራሱን ለማስፋፋት፣ የትምህርት ክፍሎችን (ዲፓርትመንቶች) እና የተማሪዎችን ቁጥር ለመጨመር ያስችለው ዘንድ መምህራንን እና ሠራተኞችን በስፋት እየቀጠረ ነው።

    ዩኒቨርሲቲው ባለፈው ዓመት በአካባቢው ያለውን የብዝሀ ሕይወት ለመንከባከብና ለመጠበቅ በሚል ዓላማ ከኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ጋር ተባብሮ ለመሥራት የሚያስችለውን ስምምነት መፈራረሙን መዘገባችን ይታወሳል።

    ምንጭ፦ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር | ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ


    Semonegna
    Keymaster

    ሐረር (ሰሞነኛ)–የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የጤና እና የህክምና ሳይንስ ኮሌጅ የህክምና ዶክተሮችን ጨምሮ 220 የጤና ባለሞያዎችን ዛሬ አስመርቋል። በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን ተመራቂ የጤና ባለሙያዎች ዘርፉ የሚጠይቀውን ሥነ- ምግባር በመላበስ ኅብረተሰቡን በቅንነት እንዲያገለግሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

    ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት “ተመራቂ የጤና ባለሙያዎች የሙያውን ሥነ- ምግባር በመላበስ ኅብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት የማገልገል ኃላፊነት ተጥሎባችኋል” ብለዋል።

    “ከራስ ጥቅም ይልቅ ለወገን ቅድሚያ መስጠት፣ ብልሹ አሠራሮችን መከላከልና ውጤታማ ሥራን በማከናወን ለሌሎች አርአያ መሆን ይጠበቅባችኋል” ሲሉም አሳስበዋል።

    ◌ ቪዲዮ፦ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ዶክተሮችና የጤና ባለሙያዎች የምረቃ ሥነ ሥርዓት በአጭሩ

    በሽታን አስቀድሞ መከላከል ላይ የተመሠረተውን የአገሪቱን የጤና ፖሊሲ የሚያጠናክሩ አገልግሎቶችን መስጠትና ጥናትና ምርምሮችን ማካሄድ እንዲሁም በእናቶችና ህጻናት ጤና ላይ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

    የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንደዘገበው የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ አቶ ኦርዲን በድሪ ዩኒቨርሲቲው በጤናው ዘርፍ የባለሙያዎችን እጥረት ለማቃለል እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሌጁ በህክምና ሳይንስ ዘርፍ እያከናወነ ባለው የመማር፣ ማስተማርና ምርምር ሥራዎች በክልሉና አጎራባች አካባቢዎች እንዲሁም በአገር አቀፍ ደረጃ ዘርፉን የሚያጠናክሩ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን አክለው ገልጸዋል።

    ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የተማረ የሰው ኃይል የማፍራት ሥራውን እንዲያጠናክር የክልሉ ህዝብና መንግሥት ድጋፍ እንደማይለየው ርዕሰ መስተዳድሩ አረጋግጠዋል።

    የዩኒቨርሲቲው በሐረር ከተማ በሚገኘው ኮሌጁ በመደበኛው የትምህርት መርሐ ግብር ካስመረቃቸው መካከል 173ቱ የህክምና ዶክተሮች መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ የኮሌጁ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ያደታ ደሴ ናቸው። ቀሪዎቹ ተመራቂዎች በመጀመሪያ ዲግሪ በነርስነት የሰለጠኑ ናቸው። በተያያዘም ከአጠቃላይ ተመራቂዎች ውስጥ 38ቱ ሴቶች መሆናቸውንም ዶ/ር ያደታ ተናግረዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ኮሌጁ በዚህ ዓመት በሕክምና ሳይንስ የቅድመ ምረቃ መርሐ ግብር በ11 ዘርፎች 2ሺህ 616 ተማሪዎች እያሰለጠነ ነው።

    ◌ ተመሳሳይ ዜና፦ Addis Ababa University’s School of Medicine graduates 288 medical doctors

    በዕለቱ በከፍተኛ የማዕረግ ዕጩ ተመራቂ ዶ/ር ምኅረት ለገሠ “የሙያ ሥነ- ምግባሩን በማክበር ኅብረተሰቡን በቅንነት ለማገልገል ተዘጋጅቻለሁ” ብላለች። የእናቶችንና የህጻናትን ሞት ለመቀነስ፣ የጤና አገልግሎቱን ለማሻሻልና በሽታን አስቀድሞ ለመከላከል የተየዘውን ጤና ልማት ግብ ለማሳካት የበኩሏን እንደምትወጣ ገልጻለች።

    ዕጩ ተመራቂ ዶ/ር ቢሊሱማ ደገፉ በበኩሉ አገሪቱ የነደፈችውን የጤና ፖሊሲ ተግባራዊ ለማድረግ ኃላፊነቱን እንደሚወጣ አስታውቋል።
    የሐረማያ ዩኒቨርሲ ከአገሪቱ ቀደምት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አንዱ ቢሆንም፤ የህክምና ዶክተሮችን ሲያስመረቅ የአሁኑ ለሰድስተኛ ጊዜ ነው።

    ምንጭ፦ ኢዜአ | ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የህክምና ዶክተሮችን አስመረቀ


    Semonegna
    Keymaster

    ለመጀመሪያ ጊዜ ከተሽከርካሪ ነፃ የሆኑ መንገዶች ቀን በአዲስ አበባ እና በሌሎች የክልል ከተሞች የተመረጡ መንገዶችን ለሰዓታት ለተሽከርካሪዎች ዝግ በማድረግ እና በመንገዶቹም ላይ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን የማድረግ መርሃ ግብር ተካሄደ።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በኢትዮጵያ እየተስፋፋ የመጣውን ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን (non-communicable diseases/ NCD) በተመለከተ ግንዛቤ ለማስጨበጥና የእግር ጉዞ ልምድን ለማበረታታትና ባህል ለማድረግ በአዲስ አበባ ከተማ መንገዶችን ለትራፊክ ዝግ በማድረግ (car free day) የጤናና አካል ብቃት ስፖርቶች ተካሄዱ።

    ህዳር 30 ቀን 2011 ዓ.ም. በመዲናዋ መንገዶችን ለትራፊክ ዝግ በማድረግ በተከናወነው የጤና የአካል ብቃት ስፖርቶች መርሃ ግብር የጤና ሚኒስትሩ አሚር አማን (ዶ/ር) እና የትራንስፖርት ሚኒስትሯ ዳግማዊት ሞገስን ጨምሮ በርካታ የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የመንግሥት ባለስልጣናት እና ታዋቂ ግለሰቦች ተሳታፊ ሆነዋል።

    መርሃ ግብሩ በየወሩ የሚከናወንና በሌሎች የክልል ከተሞች የሚስፋፋ እንደሆነም ተጠቁሟል። በአዲስ አበባ የተጀመረውን መርሃ ግብር ተከትለው በዚሁ ዕለት ባህር ዳር፣ ጅማ፣ መቐለ፣ ሀዋሳ እና ጅግጅጋ “ከተሽከርካሪ ፍሰት ነፃ የሆኑ መንገዶች ቀን” በሚል ተመሳሳይ ዝግጅቶችን ማዘጋጀታቸውን ዶ/ር አሚር አማን በማኅበራዊ ገጻቸው አስታውቀዋል።

    በመዲናዋ መርሃ ግብሩ ሲከናወን የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ አደባባዮችና ጎዳናዎች ዝግ ተደርገው ህብረተሰቡ በእግሩ እንዲጓዝ ተደርጓል።

    መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ሰለሞን ኪዳኔ የአዲስ አበባ መንገዶችን በወር አንድ ጊዜ የእግር ጉዞ እና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንዲደረግባቸው ለማስቻል እየተሠራ እንደሆነ ገልጸዋል። በሚቀጥለው ዓመት 15 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ለእግረኛ እና ለብስክሌት መንቀሳቀሻ ምቹ መንገዶችን ለመስራት መታሰቡን ጠቁመዋል።

    በየወሩ መጨረሻ እሁድ በመላው አገሪቱ በእግር የመጓዝ ልምድን ለማበረታታትና ባህል ለማድረግ “ከተሽከርካሪ ፍሰት ነፃ የሆኑ መንገዶች ቀን” በሚል መሪ ሀረግ መንገዶችን ለትራፊክ ዝግ እንደሚደረጉ ለማወቅ ተችሏል።

    ህዳር 30 ቀን 2011 ዓ.ም. በተደረገው መርሃ ግብር በርካታ ቁጥር ያላቸው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን ጨምሮ የእግር ጉዞና የተለያዩ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን አድርገዋል።

    ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችንና አጋላጭ መንስዔዎቻቸውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲቻል ህብረተሰቡ የመመርመር ልምዱን እንዲያሳድግም ጥሪ ቀርቧል። የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) እ.ኤ.አ የ2016 ዓ.ም. መረጃን/ውሂብን ተገን አድርጎ በ2018 ዓ.ም. ባወጣው የሀገራት ሪፖርት ኢትዮጵያ ውስጥ በየዓመቱ ከሚሞተው ሰው 39 በመቶው ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች ምክንያት እንደሆነ ያሳያል። ይህ አሀዝ በበሽታዎች ሲከፋፈልም፥ ከልብ ጋር የተያያዙ በሽታዎች (16 በመቶ)፣ የተለያዩ የካንሰር በሽታዎች (7 በመቶ)፣ ከመተንፈሻ አካላት ጋር የተያያዙ በሽታዎች (2 በመቶ) እና የስኳር በሽታ (2 በመቶ) ሲይዙ የተቀረው 12 በመቶ ደግሞ በሌሎች የተለያዩ ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች እንደሆነ ሪፖርቱ ያትታል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እና የዓለም ጤና ድርጅት (WHO)

    ነፃ የሆኑ መንገዶች

    Semonegna
    Keymaster

    በኢትዮጵያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የጤናውን ዘርፍ ለማገዝ የተሰራችው ሰው አልባ አውሮፕላን (drone) ከቢሾፍቱ አየር ኃይል ወደ አዳማ ከተማ የተሳካ በረራ አድርጋለች።

    የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሰው አልባ አውሮፕላንን በመጠቀም የህክምና መሣርያዎችን እና መድኃኒቶችን ለማጓጓዝ የሚያስችል ስምምነትም ተፈራርመዋል።

    ስምምነቱ በ6 ጣቢያዎች 24 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን በመጠቀም እስከ 5ኪ.ግ. የህክምና ቁሳቁሶችንና መድኃኒቶችን ለማድረስ የሚያስችል ነው።
    ስምምነቱን የተፈራረሙት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስተር ጌታሁን መኩርያ (ዶ/ር ኢንጂ.) እና የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን ናቸው።

    የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌታሁን መኩርያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ሰው አልባ አውሮፕላንኗ በሳይንስና ቴክኖሎጂ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዞች መሠራቷን ጠቅሰው ለሳይንስና ቴክኖሎጂ መዳበር የበለጠ አስተዋጽዖ ሊያደርጉ የሚችሉ የሙያ ማኅበራትንና ወጣት የፈጠራ ባለሙያዎችን በመደገፍ በቀጣይ መሰል ቴክኖሎጂዎች ሽግግር ዙርያ ከቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዞች ጋር በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።

    ምንጭ፦ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

Viewing 11 results - 1 through 11 (of 11 total)