Search Results for 'ኤባ አባተ'

Home Forums Search Search Results for 'ኤባ አባተ'

Viewing 3 results - 1 through 3 (of 3 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    በኢትዮጵያ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ተግባራዊ የሚሆን አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች በተገኙበት ዛሬ ይፋ ሆነ።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ አንዲት አገር በዓለም አቀፍ የጤና ህግጋት ላይ የተጠቀሱትን መሠረታዊ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችንና አደጋዎችን ለመከላከል፣ አስቀድሞ ለመለየትና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል አቅም ለማጠናከር የተቀመጡ ግቦችን እንድታሟላ የሚያስችል ዕቅድ ሲሆን በሃገሪቱ ሙሉ ባለቤትነት የሚቀረጽ የትግበራ ዕቅድ ነው።

    ማንኛውም የዓለም አቀፍ የጤና ሕግጋት ፈራሚ አገር ይህንን ዕቅድ እንደሚያዘጋጅ ሁሉ ኢትዮጵያም የዚህ ስምምነት ፈራሚ እንደመሆኗ በተደጋጋሚ የሚገጥሟትን የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎችን ለመቋቋም የሚያስፈልጓትን አቅም ለመገንባት ዕቅዱን ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኗል።

    የትግበራ ዕቅዱን በአዲስ አበባ በይፋ መጀመሩን ያበሰሩት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር  አቶመቀ መኮንን፥ ስለ አንድ አገር ሰላምና ደህንነት ስንናገር የሕዝቦቻችንን የጤና ደህንነት ጭምር አያይዘን እንደምንናገር መገንዘብ እንደሚገባ ጠቁመው፥ አገራዊ ዕቅዱ ወቅታዊና እንደአገር የሚያጋጥሙንን ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ቀድሞ ለመከላከልና ብዙ ጉዳት ሳያደርሱ ምላሽ ለመስጠት ያስችለናል ብለዋል።

    ◌ SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest

    የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን በበኩላቸው ሃገሪቱ እ.ኤ.አ በ2016 የዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ከአፍሪካ ቢሮ በመጡ ገምጋሚዎች የጤና ደህንነቷ ያለበትን ደረጃ ማስመዘኗን ገልጸው፥ ከግምገማው በተገኙ ግብረ መልሶች እና በሃገሪቱ ከተከሰቱ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ምላሽ አሰጣጣችን የተግባር ልምድ በመውሰድ አገራዊ የጤና ትግበራ ዕቅድ አዘጋጅታለች ብለዋል።

    የትግበራ ዕቅዱን ለመፈጸም በጀት ስለሚጠይቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ያለንን ሃብት አቀናጅተን በመጠቀም ለዕቅዱ መሳካት የበኩላችንን ድርሻ መወጣት ይገባናል ያሉት ደግሞ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ዶ/ር ፓሚላ ሙቱሪ ናቸው።

    የኢትዮጵይ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኤባ አባተ በበኩላቸው፥ እንደ ኩፍኝና ቢጫ ወባን የመሳሰሉ ወረርሽኞችን ለመከላከልና በዓለም ደረጃ ለሚከሰቱ እንደ ኢቦላ እና ዚካ ቫይረስ ያሉ ወረርሽኞችን ለመከላከል አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።

    ለዕቅዱ ትግበራ 368 ሚሊዮን 764 ሺህ 777 ዶላር የሚያስፈልግ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 77 በመቶ የሚሆነው የክትባት ሽፋንን ለማሳደግ የሚውል ይሆናል።

    አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅዱ ለአምስት ዓመት ማለትም ከ2011/12 እስከ 2016/17 ዓ.ም ድረስ የሚተገበር ይሆናል።

    ምንጭ፦ የጤና ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አገራዊ የጤና ደህንነት


    Semonegna
    Keymaster

    እ.ኤ.አ ከ2019 እስከ 2023 ለሚተገበረው አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ 10 ቢሊዮን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን፥ ወጪው ከኢትዮጵያ መንግሥት፣ ከልማት አጋሮችና ባለድርሻ አካላት እንደሚሰባሰብ ለማወቅ ተችሏል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – በኢትዮጵያ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ተግባራዊ የሚሆን አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች በተገኙበት ዛሬ ይፋ ሆነ።

    በዚህ ወቅት እንደተገለጸው፥ አገሪቷ መከላከልን መሠረት ያደረገ ስልት ቀይሳ የምታደርገውን ጥረት በጉልህ ይደግፋል። በተለይም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ አካባቢዎች በተፈጠሩ አለመረጋጋት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ተላላፊ ለሆኑ በሽታዎች እንዳይጋለጡ አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችል ነው።

    እ.ኤ.አ ከ2019 እስከ 2023 ለሚተገበረው አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ 10 ቢሊዮን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን፥ ወጪው ከኢትዮጵያ መንግሥት፣ ከልማት አጋሮችና ባለድርሻ አካላት እንደሚሰባሰብ ለማወቅ ተችሏል።

    የጤና ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን እንደተናገሩት፥ በዕቅድ ዝግጅቱ የሚመለከታቸው መሥሪያ ቤቶች ተሳትፎ አድርገዋል።

    አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ ችገሮች ከመከሰታቸው በፊት አስቀድሞ በመለየት መከላከል፣ ችግሮች ሲከሰቱ ፈጣን ምላሽ መስጠት በኅብረተሰቡ ላይ በህመምና በሞት የከፋ ጉዳት ሳይደርስ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ስትራቴጂ ነው።

    ◌ SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest

    ባለፉት ሁለት ዓመታት የጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵይ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) ጋር በመሆን ዕቅዱን ዝግጅት ሲደረግ እንደነበረ ዶ/ር አሚር ገልጸው፥ አገሪቷ በዘርፉ ምን ክፍተት አለባት? የሚለውን በጥናት ላይ የተመሰረተ ሥራ መከናወኑን አስረድተዋል። እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፥ ዕቅዱ ከመዘጋጀቱ በፊት አገር አቀፍ የዳሰሳ ጥናት ተካሂዷል።

    ዶ/ር አሚር እንደሚሉት፥ በጥናቱ መሠረት ዝቅተኛ አፈጻጸም የታየበት አደጋ ሲከሰት ፈጣን ምላሽ መስጠት መሆኑ የተለየ ሲሆን ችግሩን ለመፍታት በሁለቱ ከተማ መስተዳደሮችና በዘጠኙ ክልሎች ማዕከላት ተቋቁሟል።

    ከኬሚካልና ጨረር ጋር በተያያዘ አደጋ ቢያጋጥም ምላሽ ለመስጠት በቂ ዝግጅት እንደሌለ በጥናት የተለየ ሌላው ችግር መሆኑን ጠቁመው በዚህም ላይ የማስተካከያ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አብራርተዋል።

    በዕቅዱ ላይ እንደ ክፍተት የተቀመጡ ችግሮችን ለመፍታት መንግሥት 25 ሚሊዮን ዶላር በመመደብ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጸዋል።

    የኢትዮጵይ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኤባ አባተ በበኩላቸው፥ አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅዱ በአገሪቷ ተላላፊ በሽታዎችና ወረርሽኝን አስቀድሞ ለመግታት ወሳኝ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።

    ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በዚሁ ወቅት እንደገለጹትዕ አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅዱ ወቅታዊና አስፈላጊ ነው። አደጋዎችን ቀድሞ የመከላከል፣ ብዙ ጉዳት ሳያደርሱ የመቆጣጠርና መልሶ የማገገምና እንዳይደገም የማድረግን አቅምን መገንባት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰቡን ዘርፈ ብዙ የጤና ችግሮች ለመፍታት በሚደረገው ጥረት ባለድርሻ አካላት በመናበብ እና አቅማቸውን ይበልጥ አጠናክረው መሥራት እንዳለባቸው ተገለጸ።

    የኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ማዕከል የስድስት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ከየካቲት 18 እስከ 21 ቀን 2011 ዓ.ም. በኢንስቲትዩቱ አዳራሽ ተካሂዷል።

    የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማው ዋና ዓላማ በሃገር አቀፍ ደረጃ የሕብረተሰብ ጤናን ከማስጠበቅ አንጻር የተሠሩትን በርካታ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ከዕቅድ አኳያ ምን ያክሉን ማሳካት እንደተቻለ፥ በመቀጠልም የታዩ ክፍተቶችን በመለየት በቀጣይ የተሻሉ ዘዴዎችን በመቀየስ ችግሮቹን ለማስወገድ ታስቦ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ነበር።

    የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኤባ አባተ በመክፈቻ ሥነ-ስርዓቱ ወቅት እንደገለጹት አጠቃላይ የሕብረተሰቡን ጤና አደጋዎች ለመከላከልና ለመቆጣጠር ይቻል ዘንድ ከፌዴራል ጀምሮ እስከ ታችኛው የሕብረተሰብ ክፍል ያለው አስተዳደራዊ መዋቅር ሰንሰለቱን ጠብቆ ጠንካራ የሆነ መስተጋብር ሊፈጥር ይገባል፤ በመሆኑም የክልል ጤና ቢሮዎች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በጤናው ዘርፍ በቅንጅት እየሠሩ የሚገኙ ሲሆን፥ ይህ መድረክ በዚህ የግማሽ ዓመት የሕብረተሰቡን ጤና ችግሮች ከመፍታት አንጻር የታዩ ጠንካራ ሥራዎች እና ድክመቶችን በመለየት በቀጣይ ለሚሠሩ ተግባራት ላይ የጋራ መግባባት የሚደረስበት በመድረክ ነው ብለዋል።

    ዶ/ር በየነ ሞገስ የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር በበኩላቸው እንደሀገር ከሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር አንጻር እየሠራን ነው፣ ምን ላይስ እንገኛለን፣ በዚህ ግማሽ ዓመት ምን ዋና ዋና ውጤቶች ተመዝግበዋል የሚሉትን በመፈተሽ በቀጣይ ችግር ፈቺ የሆኑ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የጋራ መግባባት የሚደረስበት መድረክ ነው የተዘጋጀው ሲሉ ተናግረዋል።

    የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ማዕከል ከዕቅድ አንጻር በግማሽ ዓመቱ ያከናወናቸውን ተግባራት፣ በመቶ ቀናት ውስጥ የታቀዱ ተግባራት፣ የነበሩ ጠንካራና አፈፃፀሞችና የነበሩ ክፍተቶች እንዲሁም የነበሩ ስጋቶች፣ ተይዞ የነበረው የበጀት አፈጻጸም፣ ዓለም አቀፍና አገር አቀፍ በሽታዎች ከዕቅድ አንጻር ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙ፣ ሀገራዊ የጤና ደህንነት እቅድ፣ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ስጋቶች፣ ተጋላጭነትና ምላሽ ዳሰሳ ጥናት በግምገማ መድረኩ ላይ በዝርዝርና በስፋት ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

    የጤና ሚኒስቴር እና በስሩ የሚገኙ መሥሪያ ቤቶች፣ የኢንስቲትዩቱ የበላይ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች፣ የክልል ጤና ቢሮዎች፣ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር የሥራ ሂደት ኃላፊዎች፣ የዕቅድ ክትትል እና ምዘና ኃላፊዎች እንዲሁም የእናቶችና ህፃናት ቡድን መሪዎች በውይይትና ግምገማ መድረኩ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት / ሰሞነኛ ኢትዮጵ

    የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት


Viewing 3 results - 1 through 3 (of 3 total)