Search Results for 'ደሳለኝ መንገሻ'

Home Forums Search Search Results for 'ደሳለኝ መንገሻ'

Viewing 3 results - 1 through 3 (of 3 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በኪነ ህንፃ ሲያስመርቅ ዘንድሮ ለሦስተኛ ጊዜ ሲሆን፥ ዘንድሮ የተመረቁት 18 ወንዶችና 16 ሴቶች በአጠቃላይ 34 የኪነ ህንፃ ሙያተኞች መሆናቸውን በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ ተገልጿል።

    ጎንደር (ሰሞነኛ)–የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለአምስት ዓመት ተኩል በኪነ ህንፃ ትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ቅዳሜ፥ የካቲት 9 ቀን 2011 ዓ.ም. በባችለር ዲግሪ (BSc in Architecture) አስመረቀ።

    በምረቃ ሥነ ስርአቱ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት ያስተላለፉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደሳለኝ መንገሻ፥ ዩኒቨርሲቲው በኪነ ህንፃ የትምህርት ዘርፍ ዘንድሮ ተማሪዎችን ሲያስመርቅ ለሦስተኛ ጊዜ መሆኑን ገልፀዋል።

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአሁኑ ወቅት በቴክኖሎጂ የትምህርት መስኮች ከ5 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያሰለጠነ እንደሚገኝ የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ፥ ቅዳሜ ዕለት የተመረቁት 18 ወንዶችና 16 ሴቶች በአጠቃላይ 34 የኪነ ህንፃ ሙያተኞችም በሀገራችን የሚታየውን የህንፃ ጥበብ ችግር ለማስተካከልም ሆነ በሙያው የሚታየውን የሰለጠነ የሰው ኃይል ለመቅረፍ እንዲተጉ አሳስበዋል።

    የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለፓን አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ ማሰገንቢያ የሚውል አስር ሚሊዮን ብር ለገሰ

    የጎንደር ከተማ ም/ከንቲባ ዶ/ር ሙሉቀን አዳነ በምርቃቱ ሥነ ስርዓት ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው የተመራቂዎቹ የምርቃት ዕለት የልጅነት ዘመን አብቅቶ ለሀገር ብቁ የሆነ የኪነ ህንፃ ባለሙያ የሚሆኑበት ዕለት እንደሆነ አስገንዝበዋል። ከዚህ በኋላም ተመራቂዎቹ ሀገሪቱ ለረዥም ዓመታት የምትጠራበትና የምትታወስበትን የኪነ ህንፃ ጥበብ እንደሚያበረክቱ እምነታቸውን ገልፀዋል።

    ተመራቂዎቹም በሙያቸው ሀገራቸውን ለማገልገል የገቡትን ቃል ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

    ከዩኒቨርሲቲው ዜና ጋር በተያያዘ የዩኒቨርሲቲው ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የማኔጅመንትና የህዝብ አስተዳደር ት/ቤት “በወቅታዊ የፖለቲካ ለውጥ ዘላቂነት ላይ የምሁራን ሚና” (‘The Role of Academicians in Sustaining the Current Political Reforms’) በሚል ርዕስ ዙሪያ ከካቲት 6 እስከ 7 ቀን 2011 ዓ.ም. ኮንፈረንስ አካሂዷል።

    በዕለቱ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ደሳለኝ መንገሻ፣ በጠቅላይ ሚኒስቴር ፅ/ቤት የመሰረተ ልማትና የከተማ ልማት አማካሪ ዶ/ር አምባቸው መኮንን፣ የጎንደር ከተማ ም/ከንቲባ ዶ/ር ሙሉቀን አዳነ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ፖለቲከኛ ፕ/ር መረራ ጉዲና፣ ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ ደራሲና የታሪክ ተመራማሪው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ የጎንደር ከተማ የልማትና የሰላም ሸንጎ አባላት የዩኒቨርሲቲው ም/ፕሬዚዳንቶች፣ ዲኖች፣ መምህራን፣ ተማሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

    Semonegna
    Keymaster

    ጎንደር (ሰሞነኛ)– በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እየተተገበረ ለሚገኘው የጤና መረጃ አብዮት ትልቅ የሰው ኃይል የሚፈጥር የቀጠና/ወረዳ ጤና መረጃ ሥርዓት (District Health Information System 2 – DHIS2) አካዳሚ እና የኤለክትሮኒክስ ጤና ፈጠራ ቤተሙከራ (e-health innovation lab) በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ጥር 30 ቀን 2011 ዓ.ም ተመረቀ።

    በምረቃ ፕሮግራሙ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ደሳለኝ መንገሻ፣ የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አበባው ገበየሁ፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚዳንቶች እንዲሁም በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሄልዝ ኢንፎርማቲክስ (Health Informatics) ትምህርት ክፍል የሁለተኛ እና ሦስተኛ ዲግሪ ተማሪዎች፣ የአቅም ግንባታ እና የሜንተርሽፕ ድጋፍ ፕሮጀክትን (Capacity Building and Mentorship Project – CBMP) ከሚተገብሩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ ተሳታፊ መምህራን እና የጤና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

    VIDEO: Ethio-American Doctors Group (EADG): Building a regional healthcare system & medical tourism

    የምረቃ መርሀግብሩን በንግግር የከፈቱት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ደሳለኝ መንገሻ የተመረቀው አካዳሚ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና በተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች እየተተገበረ የሚገኘውን የአቅም ግንባታ እና የሜንተርሽፕ ድጋፍ ፕሮጀክት (CBMP) ለመደገፍ ታስቦ የተከፈተ መሆኑን ገልፀው፤ በተለይ በአማራ እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለሚገኙ የጤና ተቋማት የሰው ኃይል በማሰልጠን ትልቅ ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ሀገሪቱ የያዘችውን የጤና መረጃ ሥርዓት በማዘመን የልህቀት ማዕከል ለመሆን ዩኒቨርሲቲው እየሠራ ይገኛል ብለዋል። ለተሳታፊዎች ለፕሮጀክቱ ቡድን አባላት እዲሁም ለጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና ለክልሉ ጤና ጥበቃ ቢሮ ምስጋና አቅርበዋል ዶ/ር ደሳለኝ በንግግራቸው መብቂያ።

    በሀገራችን የሚታየው የጤና መረጃ አያያዝ ሥርዓት ከማሰባሰብ እስከ መረጃ መተንተን የሚታዩ በርካታ ክፍተቶች ያሉበት በመሆኑ እንደ DHIS2 ዓይነት ሥርዓቶችን መጠቀም ግድ መሆኑን የተናገሩት ዶ/ር አበባው፥ ዩኒቨርሲቲው በትክክለኛው ሰዓት አካዳሚውን በመክፈቱ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል። ዶ/ር አበባው አያይዘውም ዩኒቨርሲቲው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችን መስጠት አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበው የተጀመረው ሥራ እንደሀገርም እንደ ዩኒቨርሲቲም የሚያኮራ ነው ብለዋል።

    በአሁኑ ሰዓት 90 በመቶ የሚሆኑ የጤና ተቋማት በDHIS2 ሥርዓት ሪፖርቶችን ማቅረብ መጀመራቸው ከጤና ጥበቃ ሚንስተር የመጡ ኃላፊዎች ተናግረዋል። መሆኑም ተመርቆ የተከፈተው አካዳሚ የጤና ኬላዎችን በመከታተል እና በመገምገም ድጋፍ ማድረግ እንዲሁም ወረዳዎችን በመረጃ አያያዝ ሥርዓት ሞዱል የማድረግ ኃላፊነት እንዳለበት ኃላፊዎች ተናግረዋል።

    የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር ተቀራርቦ እየሠራ የሚገኘው ሥራ ለሌሎች ተቋማትም አርአያ መሆኑን የገለፁት ተሳታፊዎች፥ የ DHIS2 አካዳሚ በዩኒቨርሲቲው መከፈቱ የዩኒቨርሲቲውን አመራሮች እና አጠቃላይ የዩኒቨርሲቲውን ማኅበረሰብ የሚያኮር ሥራ መሆኑ ገልፀዋል።

    በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በተያዘው የጤና መረጃ አብዮት ዙሪያ ማብራሪያ የቀረበ ሲሆን፥ ዶ/ር ቢንያም ጫቅሉ በአቅም ግንባታ እና የሜንተርሽፕ ድጋፍ ፕሮጀክት (CBMP) እስካሁን የተሠሩ ተግባራትን እና የወደፊት አቅጣጫዎችን አቅርበዋል። በቀረበው ሀሳብ ላይ ውይይት ተደርጎ መርሀ ግብሩ ተጠናቋል።

    District Health Information System 2 (DHIS2) ምን እንደሆነ በዝርዝር ለማንበብ እዚህ ይጫኑ (እንግሊዝኛ)

    ምንጭ፦ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    DHIS2


    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት የሚያዘጋጀው ሽልማት ዓላማ በኢትዮጵያ አምራቾችና አገልግሎት ሰጪዎች እንዲሁም በግንባታ ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች ለጥራት የሚያደርጉትን ሥራ ማበረታታት መሆኑ በሽልማቱ ሥነ-ሥርዓት ወቅት ተገልጿል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለሦስተኛ ጊዜ የአገር አቀፍ የጥራት ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆነ። ዩኒቨርሲቲው ያገኘውን ሽልማት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ደሳለኝ መንገሻ (ዶ/ር) ከፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እጅ ተቀብለዋል።

    የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ስድስተኛ ዙር የጥራት ሽልማት ጥር 2 ቀን 2011 ዓ.ም. ምሽት በብሔራዊ ቤተ-መንግስት ተካሂዷል። በሽልማትና ዕውቅና ሥነ-ሥርዓቱ ላይ 40 ድርጅቶችና ተቋማት የምስክር ወረቀትና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በውድድሩ ላይ

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ሐረር ቢራ አክሲዮን ማኅበር እና አማራ መልሶ ማቋቋምና ልማት ድርጅት የአንደኛ ደረጃ ዋንጫ ተሸላሚ ሲሆኑ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለተከታታይ ሦስት ዓመታት የጥራት ደረጃውን ጠብቆ አሸናፊ በመሆኑ የልዩ ዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

    The Ethiopian Quality Award Organization

    ከ336 በላይ ድርጅቶች እንዲመዘገቡ ጥሪ የተደረገ ቢሆንም የተመዘገቡት 52 ነበሩ። ከነዚህ ውስጥ 21 በአምራች፣ አምስት በአገልግሎት፣ አራት በከፍተኛ ትምህርት፣ አምስት በጤና እና አምስት በግንባታ ዘርፍ የተሰማሩ፤ በድምሩ 40 ተቋማት እስከመጨረሻው በውድድሩ የዘለቁ ናቸው።

    የሽልማቱ ዋና ዓላማ በኢትዮጵያ አምራቾችና አገልግሎት ሰጪዎች እንዲሁም በግንባታ ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች ለጥራት የሚያደርጉትን ሥራ ማበረታታት መሆኑ በሥነ-ሥርዓቱ ወቅት ተገልጿል።

    የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት የበላይ ጠባቂ የሆኑት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የጥራት ጉዳይ የሥነ-ልቦናና የፈረጠመ የኢኮኖሚ የበላይነት እንዲሁም የበለፀገ ማኅበረሰብ መገለጫዎች ናቸው ብለዋል። የምርትና አገልግሎት ጥራትን ለማስጠበቅና ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ከደረሱበት የጥራት ደረጃ ለመድረስ ጠንክሮ መሥራት እንደሚገባም አሳስበዋል።

    የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት በ2000 ዓ.ም በዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከልና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትብብር የተቋቋመ ነው። ድርጅቱ ሲመሠረት ዓላማውን መንግስት በጥራት ረገድ የሚያደርገውን ጥረት ለመደገፍና የጥራት ጽንሰ ሀሰብን በማኅበረሰቡ፣ በአምራቾች፣ በአገልግሎት ሰጪዎችና በግንባታ (ኮንስትራክሽን) ዘርፍ በተሰማሩ ድርጅቶችና ተቋማት ዘንድ እንዲሰርጽ ለማድረግ ነው። እስካሁን 49 ድርጅቶችና ተቋማት የድርጅቱን የልዕቀት ማዕረግ የዋንጫ ሽልማት አግኝተዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት


Viewing 3 results - 1 through 3 (of 3 total)