የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አዲሱ ካምፓስ (በንሳ ዳዬ ካምፓስ) ተማሪዎችን በመቀበል በይፋ ሥራ ጀመረ

Home Forums Semonegna Stories የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አዲሱ ካምፓስ (በንሳ ዳዬ ካምፓስ) ተማሪዎችን በመቀበል በይፋ ሥራ ጀመረ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8866
    Semonegna
    Keymaster

    የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በንሳ ዳዬ ካምፓስ ካለው ርቀትና የመሬት አቀማማጥ አኳያ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ራሱን ወደቻለ ዩኒቨርሲቲ ሊያድግ የሚችል በመሆኑ ግንባታዎቹ ይህንኑን ታሳቢ አድርጎ የተካሄዱ እንደሆነ ታውቋል።

    ሀዋሳ (ሰሞነኛ)– ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ያቋቋመውና ላለፉት 4 ዓመታት በግንባታ ሂዳት ላይ የነበረው የበንሳ ዳዬ ካምፓስ ጥቅምት 30 ቀን 2011ዓ.ም. ወደ ካምፓሱ ለተመደቡ 340 አዲስ ገቢ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል በማድረግ በይፋ ሥራውን ጀምሯል።

    በበንሳ ወረዳ ዳዬ ከተማ ውስጥ ወደተገነባው ካምፓስ ተማሪዎቹ በመጡበት ጊዜ በአከባቢው ማኀበረሰብ ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አቶ አያኖ በራሶ በቦታው በመገኘትለተማሪዎቹ የዩኒቨርሲቲው አባልነታቸውን አረጋግጠውላቸዋል።

    አቶ አያኖ ለተማሪዎች፣ ለአካባቢው ህብረተሰብ እና ለእንግዶች ባስተላለፉት መልዕክት መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በያዘው የትኩረት አቅጣጫ ካምፓሱ የተገነባ ሲሆን ሙሉ በሙሉ ባይጠናቀቅም የሰው ሃይልና አስፈላጊ ቁሳቁሶች በመሟላታቸው ወደ ሥራ መገባቱን አስረድተዋል።

    በንሳ ዳዬ ካምፓስ ካለው ርቀትና የመሬት አቀማማጥ አኳያ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ራሱን ወደቻለ ዩኒቨርሲቲ ሊያድግ የሚችል በመሆኑ ግንባታዎቹ ይህንኑን ታሳቢ አድርጎ የተካሄዱ እንደሆነ ያስታወቁት ፕሬዝዳንቱ፥ ተማሪዎች፣ ሠራተኞችና የአከባቢው ማኀበረሰብ እንደግል ንብረታቸው መንከባከብና ለመጭው ትውልድ የማስተላፍ ግዴታ እንዲወጡ አሳስበዋል።

    አዲስ የተመደቡ ተማሪዎችም ከቤተሰብ ተለይተው የመጡበትን ዓላማ በማንገብ ጊዜያዊ ተግዳሮቶችን በመቋቋም፣ ከአልባሌ ሱሶች (እና ድርጊቶች) በመራቅና በርትቶ በማጥናት ከቤተሰብና ሀገር የተጣለባቸውን አደራ ለመወጣት ራሳቸውን ማዘጋጀት እንዳለባቸው አቶ አያኖ በራሶ አስገንዝበዋል።

    የካምፓሱ ማኔጅንግ ዳይሬክቴር አቶ ገነነ ካቢሶ በበኩላቸው ካምፓሱ በእርሻ ሜካናይዜሼንና በመምህራን ስልጠና የትምህርት መስኮች ተማሪዎችን ተቀብሎ የሚያሰለጥን ሲሆን፥ በተማሪዎቹ በሚካሄዱ አሳታፊና ችግር ፌች ምርምሮች የአከባቢውን ማሀበረሰብ ያሳተፈ እንዲሆን ህብረተሰቡ እንዲተባበር ተከታታይ ስልጠናዎች የሚሰጡ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

    በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንቶች፣ የበንሳ ዳዬ ከተማ፣ የአከባቢው ቀበሌ ገበሬ ማኀበራት አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ከአከባቢው ማኀበረሰብ የወጣቶችና ሴቶች ተወካዮች መገኘታቸው ታውቋል።

    ምንጭ፦ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    በንሳ ዳዬ ካምፓስ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.