Home › Forums › Semonegna Stories › የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የኤሌክትሮኒክ ግብይት (ኢ-ኮሜርስ) ማዕከል ኢትዮጵያ ውስጥ ሊገነባ ነው
Tagged: ምስራቅ አፍሪካ, ቲታንስ ዲ አፍሪቅ, የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር, የኤሌክትሮኒክ ግብይት, ጌታሁን መኩሪያ
- This topic has 3 replies, 2 voices, and was last updated 6 years, 3 months ago by
Anonymous.
-
AuthorPosts
-
February 5, 2019 at 5:04 pm #9499
Anonymous
Inactiveየኤሌክትሮኒክስ ግብይት በኢትዮጵያ ለመጀመር የአለም አቀፉ የፖስታ ድርጅት ቲክኒካል ኮሚቴ ጥናት ጀመረ፡፡
—–አፍሪካን በተለያዩ ቀጠናዎች ከፍሎ የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ለመጀመር እየሰራ የሚገኘው ዓለማቀፍ የፖስታ ኅብረት (Universal Postal Union) አጥኚ ቡድኑን ወደ ኢትዮጵያ የላከው ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በተፈራረመው ስምምነት መሰረት ነው፡፡
ቡድኑ የኢትዮጵያ ዝግጁነት ከፖሊሲ፣ ከመሰረተ ልማትና ከኢ-ታክስ አኳያ፤ ኢትዮጵያ ስርዓቱን ለመዘርጋት ምን ማድረግ አለባት፣ ትግበራውን በምን መልኩ መከናወን ይኖርበታል የሚሉትንና የመሳሰሉትን ጉዳዮች ያጠናል፡፡
የግብይት ስርዓትን ለማዘመን፣ ገዢና ሻጭን በቀጥታ ለማገናኘት፣ ቀጠናዊ ትስስር ለመፍጠር፣ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ሃብት ለማሳደግ ትልቅ ጠቀሜታ ይኖረዋል ተብሎ የሚታሰበው የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ስርዓት በኢትዮጵያ በቅርቡ ተግባራዊ ለማድረግ ርብርብ እንደሚደረግ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ተናግረዋል፡፡
የአለም አቀፉ የፖስታል ድርጅት የምስራቅ አፍሪካ ማዕከሉን ኢትዮጵያ ውስጥ ለመገንባት ማቀዱ ይታወሳል፡፡
በ2017 በአፍሪካ በኤሌክትሮኒክስ ግብይት ከ85 ቢሊየን እስከ 100 ቢሊየን ዶላር የገበያ ድርሻ ይይዛል ተብሎ ይገመታል፡፡
February 6, 2019 at 3:28 am #9523Anonymous
Inactiveኢትዮጵያ የኤሌክትሮኒክስ ግብይትን ለመዘርጋት የጀመረችውን ስራ ዴንማርክ እንድታግዝ ጠየቀች፡፡
—–በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ካሪን ፖውልሰን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎች ጋር በግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያና በኤሌክትሮኖክስ ግብይት ዙሪያ ምክክር አድርገዋል፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ኢትዮጵያ የጀመረችውን የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ዴንማርክ እንድታግዝና ቴክሎጂን በሚጠቀም የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ዘረፍ እንድትሳተፍ ጠይቃዋል፡፡
1ቢሊየን ዶላር ገደማ የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኘውን ቡና እሴት ጨምሮ በኤሌክትሮኖክስ ግብይት ወደ ገበያ ማቅረብ ቢጀመር ገቢውን በ4 እና 5 እጥፍ ማሳደግ እንደሚቻል ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡
የኤሌክትሮኒክስ ግብይትን በኢትዮጵያ ለመጀመር የአለም አቀፉ ፖስታል ድርጅት ቴክኒካል ኮሚቴ ጥናት መጀመሩ ይታወሳል፡፡
February 24, 2019 at 4:48 pm #9874Anonymous
Inactiveቡናን ከምርት እስከ ውጭ ገበያ ያለውን ሂደት በቴክኖሎጂ ለማገዝ ስምምነት ተፈረመ
—–‹‹ቲታንስ ዲ አፍሪቅ›› በተለያዩ የቴክኖሎጂ ዘርፎች በአፍሪካ ውስጥ የሚሰራ ድርጅት ሲሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ቡናን ከምርት ጀምሮ እስከ ውጭ ገበያ ያለውን ሂደት በቴክኖሎጂ ለማገዝ ተስማምቷል፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ‹‹ከቲታንስ ዲ አፍሪቅ›› ጋር ቴክኖሎጂን የሚጠቀም የግብርና ስራ ላይ በጋራ ለመስራት ተስማሙ፡፡
በዚህ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የግብርና ስራ ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር እቅድ እንደተያዘም ተገልጿል፡፡
ኢትዮጵያ የቡና አምራች ሀገር ብትሆንም ዘርፉ በቴክኖሎጂ ባለመደገፉ እና እሴት መጨመር ላይ ትኩረት ባለመደረጉ ከዘርፉ የሚገባትን ያክል ተጠቃሚ አይደለችም፡፡
ይህንን ችግር ለመቅረፍ ዘርፉን በቴክኖሎጂ መደገፍ አስፈላጊ በመሆኑ ነው ድርጅቱ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በጋራ ለመስራት የተስማማው፡፡
ስምምነቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር ሹመቴ ግዛው እና የቲታንስ ዲ አፍሪቅ ማኒጂንግ ዳይሬክተር ዶክተር ጊልበርት ሳጊያ ተፈራርመዋል፡፡
ቴክኖሎጂ በሁሉም ዘርፍ የሚገባ በመሆኑ የትኛውንም ስራ በቴክኖሎጂ ለመደገፍ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተቋማዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እየሰራ መሆኑን ሚኒስቴር ዴኤታው ተናግረዋል፡፡
‹‹ቲታንስ ዲ አፍሪቅ›› አፍሪካ ውስጥ በቴክኖሎጂ የበለፀገ ማህበረሰብ ለመገንባት እየሰራ ያለ ድርጅት ነው፡፡
ምንጭ፡- የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር
-
AuthorPosts
- You must be logged in to reply to this topic.