የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ አንድ ቋት ዋሽ አካውንት ፕሮግራምን ተቀላቀለ
—–
የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (KOICA) የዋን ዋሽ ብሔራዊ ፕሮግራም አካል የሆነውን አንድ ቋት ዋሽ አካውንት (Consolidated WASH Account) ፕሮግራም ተቀላቀለ።
የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (KOICA) ላለፉት በርካታ ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን፤ በመስኖ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ህብረተሰብን ተጠቃሚ በሚያደርጉ የልማት ፕሮጀክቶች ላይ በመሳተፍ ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል።
ኤጀንሲው በመደበኛ ፕሮግራሙ ከሚያከናውናቸው ተግባራት በተጨማሪ ከ2012 በጀት ዓመት ጀምሮ በሚከናወነው የሁለተኛው ዙር አንድ ቋት ዋሽ አካውንት (Consolidated WASH Account) ፕሮግራም በመቀላቀል ፕሮግራሙን ለመደገፍ 10 (አሥር) ሚሊን ዶላር የድጋፍ ስምምነትን የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ዳይሬክተር የሆኑ ሚስተር ዶንግ ሆ ኪም እና የውሃ ፤ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ነጋሽ ዋጌሾ መጋቢት 18/2011 ዓ.ም ተፈራርመዋል።
የሁለቱ ሀገራት የረጅም ዘመናት ትብብር ይበልጥ እየተጠናከረ መምጣቱን ሚኒስቴር ዴኤታው በማስታወስ ከዚህ ከተመደበው በጀት ውስጥ 7 ሚለዮን ዶላር ለመጠጥ ውሃ አቅርቦት እና ቀሪው 3 ሚሊዮን ዶላር ኮይካ ከዚህ በፊት የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን በሚያከናውንባቸው አከባቢዎች የገጠር ሳኒቴሽንን ሽፋን ለማሳደግ የሚውል በጀት መሆኑን አስረድተዋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት