Search Results for 'ሙዚቃ'

Home Forums Search Search Results for 'ሙዚቃ'

Viewing 10 results - 16 through 25 (of 25 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    «በ1950ዎቹ ዓመታት መጨረሻ ጋሽ ጥላሁንን፤ አለማየሁ እሸቴን እና ታምራት ሞላን የመሳሰሉ እንቁዎች ሰምቼ ከሙዚቃ ፍቅር ያዘኝ» ድምፃዊ የግጥምና ዜማ ደራሲ እንዲሁም የሙዚቃ አቀናባሪ አንጋፋዉ አርቲስት አያሌዉ መስፍን። ከሁሉ ከሁሉ የአዲስ አበቤ ፍቅረኛሞች ቀጠሮአቸዉ አያሌዉ መስፍን ሙዚቃ ቤት ጋር እንደነበር የሚያስታዉስ ያስታዉሰዋል።

    ድምፃዊ የግጥምና ዜማ ደራሲ እንዲሁም የሙዚቃ አቀናባሪ ነው፤ አንጋፋዉ አርቲስት አያሌዉ መስፍን። ወሎ የሙዚቃ ባለ ኃብቶችን የሙዚቃ ምሁራንን፤ ያፈራች ሃገር መሆንዋ አብዛኞች ይመሰክሩላታል። ወሎ ካፈራችዉ አያሌዉ መስፍን ከመሳሰሉ ከያኒዎች መካከል በባህል ሙዚቃ ገናና ስምን የተከለዉ የማሲንቆዉ ቀንድ፤ በማሞካሸት የጥበብ ጀማሪ አሰፍዬ አባተ ይባል የነበረዉ፤ አንጋፋዋ ድምፃዊ ማሪቱ ለገሰ፤ አለማየሁ እሸቴ፤ ኃብተሚካኤል ደምሴ ከአብዛኞቹ የጥበብ እንቁዎች እጅግ ጥቂቶቹ ናቸዉ።

    ወሎ ከያኒዎችን ብቻ ሳይሆን አራቱን የኢትዮጵያ የሙዚቃ ቅኝቶች ያፈራች እንደሆነችም ይነገርላታል። «በ 50 ዎቹ ዓመታት መጨረሻ ጋሽ ጥላሁንን፤ አለማየሁ እሸቴን እና ታምራት ሞላን የመሳሰሉ እንቆዎች ሰምቼ ከሙዚቃ ፍቅር ያዘኝ» ያለን አንጋፋዉ አርቲስት አያሌዉ መስፍን፤ ስለአገር ፍቅር ስለፍትህ፤ ስለአንድነት ስለፍቅር አዚሞአል፤ ገጥሞአልም። በተለይ በሙዚቃዎቹ ከኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት ጋር በጋራ የሃገር ድንበርን ማስከበሩ ይነገርለታል። በደረሳቸዉ ግጥሞች በርካታ ከያንያን ተወዳጅ ዜማቸዉን ለአድማጭ ጆሮ አድርሰዉ ታዋቂ ሆነዋል። ከሁሉ ከሁሉ የአዲስ አበቤ ፍቅረኛሞች ቀጠሮአቸዉ አያሌዉ መስፍን ሙዚቃ ቤት ጋር እንደነበር የሚያስታዉስ ያስታዉሰዋል።

    ምን እሱ ብቻ! እንዲህ እንደአሁኑ የእጀታ ስልክ (ሞባይል) ኖሮ፤ የኢንተርኔት አገልግሎት ከሞላ ጎደል ተስፋፍቶ «ሜሴጅ አድግ አድርጊልኝ» በማይባልበት በዝያ ዘመን ከክፍለሃገር የመጡ ኢትዮጵያዉያን አያሌዉ ሙዚቃ ቤት መገናኛቸዉ ነበር። የመዲናዋም ወጣቶች ቢሆኑ በአያሌዉ ሙዚቃ ቤት በራፍ ግራና ቀኝ ከቆመዉ ነጎድጓድ ድምፅን ከሚተፋዉ አምፕሊፋየር «አልያም የድምፅ ማጉያ » በተለይ አዲስ ሙዚቃ ተለቀቀ ከተባለ አካባቢዉ ላይ ቆመዉ ማድመጫቸዉ ነበር፤ የሆነ ሆነና አንጋፋዉ ሙዚቀኛ አያሌዉ መስፍን የት ይሆን? የሙዚቃዉን መድረክ ተዉዉ እንዴ?

    ስለአገር ፍቅር ስለፍትህ፤ ስለአንድነት ስለፍቅር አዚሟል

    አዘጋጆች፦ አዜብ ታደሰ እና ተስፋለም ወልደየስ (ዶይቸ ቬለ)
    —–
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    አርቲስት አያሌዉ መስፍን


    Semonegna
    Keymaster

    አውታር የተባለውን የሙዚቃ መተግበሪያ ለማዘጋጀት 5 ዓመታት የወሰደ ሲሆን ዕውቁን የሙዚቃ አቀናባሪ ኤልያስ መልካን ጨምሮ የተለያዩ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ባለሙያዎች በዝግጅቱ ላይ ተሳትፈዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)–በኢትዮጵያውያን ሙዚቀኞች፣ መተግበሪያ በማዘጃጀት ላይ የተሰማሩ (app developers) እና ኢትዮ ቴሌኮም የረዥም ጊዜ ጥረት በኋላ በሞባይል ስልክ የኢትዮጵያን ሙዚቃዎች ማግኘት የሚያስችል አዲስ መተግበሪያ ይፋ ተደርጓል።

    ኤልያስ መልካ፣ ጆኒ ራጋ፣ ዳዊት ንጉሡ እና ኃይሌ ሩትስ በጋራ የመሰረቱት አውታር መልቲ ሚዲያ ከሌሎች የሙዚቃ ባለሙያዎች እና ኢትዮ ቴለኮም ጋር በመሆን ጥቅም ላይ እንዲውል ያዘጋጁት አውታር የሙዚቃ መተግበሪያ (music app) ዓርብ፣ ግንቦት 23 ቀን 2011 ዓ.ም. በይፋ ሥራ ጀምሯል።

    አውታር የተባለውን የሙዚቃ መተግበሪያ ለማዘጋጀት 5 ዓመታት የወሰደ ሲሆን ዕውቁን የሙዚቃ አቀናባሪ ኤልያስ መልካን ጨምሮ የተለያዩ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ባለሙያዎች በዝግጅቱ ላይ ተሳትፈዋል።

    በዝግጅቱ ላይ የተሳተፉት ባለሙያዎች እንደሚሉት ከሆነ አውታር መተግበሪያ ሁሉንም የኢትዮጵያ ሙዚቃ ዘውጎችና ቋንቋዎች ይሸፍናል። ከመተግበሪያው ላይ አንድ ዘፈን ለማውረድ 4 ብር ከ50 ሳንቲም የሚጠይቅ ሲሆን አንድ አልበም ለማውረድ ደግሞ 15 ብር ያስከፍላል ተብሏል።

    የኢትዮጵያ የፊልም ፖሊሲ የማስፈጸሚያ ሰነድ እንደሚያስፈልገው ተጠቆመ

    “አዲሱ አመተግበሪያ ኢትዮጵያውያን የፈለጉትን ሙዚቃ በፈለጉት ጊዜና ቦታ በእጅ ስልኮቻቸው በኢንተርኔት አማካይነት ለመግዛት ያስችላቸዋል” ይላል ኤልያስ መልካ።

    መተግበሪያውን የሠሩት ባለሙያዎች እንደሚሉት የዚህ ሥራ ዋና ዓላማ ሙዚቃዎቹን በመፍጠር ሂደት ለሚሳተፉ ሁሉ ገቢን ለማሳደግ ነው።
    ገቢን ለማሳደግ ሲባል ለአንድሮይድ ስልክ ተጠቃሚዎች ከተዘጋጀው ከዚህ መተግበሪያ ላይ የሚወርዱትን ሙዚቃዎች ለሌሎች ማጋራት እንዳይቻል መደረጉም ታውቋል።

    ከሙዚቃ ሥራዋ በተጨማሪ በተለያዩ ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ንቁ ተሳትፎ የምታደርገው ድምፃዊት ፀደኒያ ገብረማርቆስ፥ አውታር የሙዚቃ መተግበሪያ ይፋ መደረግ እና የኢትዮጵያ ሙዚቃዎችን ለመሸጥ እንደ አማራጭ መቅርቡን በጽኑ ከሚደግፉት መካከል አንዷ ነች።

    ሰዎች ዘመናዊ ስልክ መያዝ በመጀመራቸው፣ ኢንተርኔት አጠቃቀማችንም ከፍ እያለ በመምጣቱ እንደዚህ ዓይነት የመሸጫ መንገድ ማስለመዱ መልካም መሆኑን ትገልፃለች።

    ከህመሜ እስከ ስደቴ ከጎኔ ላልተለየው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ለመገናኘት አበቃን – አርቲስት ፋሲል ደመወዝ

    ድምጻዊት ፀደኒያ እስካሁን ሥራዎቿን ወደ አውታር ወስዳ በእናንተ በኩል ይሸጥልኝ ብላ ባትሰጥም፤ አገልግሎቱ ከተጀመረ ግን ይህንን ለማድረግ ዓይኗን እንደማታሽ ትናገራለች።

    ብዙ ሰዎች በአንድ ሲዲ ውስጥ ያሉ ሥራዎችን በአጠቃላይ ስለማይወዱት “እያለፉ ነው የሚያደምጡት” የምትለው ድምጻዊት ፀደኒያ፥ ግዴታ አስራ ምናምን ዘፈኖች መግዛት አይጠበቅባቸውም ትላለች።

    ይህ አዲስ መተግበሪያ አንድ ሰው የሚፈልጋቸውንና የሚመርጣቸውን ዘፈኖች ብቻ መርጦ የመግዛት ዕድል ስለሚሰጥ ተመራጭ መገበያያ መንገድ ነው ስትል ሀሳቧን ታጠናክራለች።

    መተግበሪያው የተሠራው ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር በመተባበር ሲሆን ቴሌኮሙ የትርፍ ተጋሪ እንደሚሆንም ተነግሯል።

    ምንጭ፦ ቢቢሲ አማርኛ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    Awtar አውታር


    Semonegna
    Keymaster

    በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በተካሄደው የሰላም ንቅናቄ ላይ ከተለያዩ ቦታዎች የመጡ እና በተለያዩ ሙያዎች ላይ የተሰማሩ የአገራችን ታዋቂ ሰዎች ስለ ሰላም እና በሰላም እጦት ምክንያት የሚከሰቱ አስከፊ ጉዳቶች ለታዳሚው አቅርበዋል።

    ወልቂጤ (ሰሞነኛ)– “ጥበብ ለሰላም” በሚል መሪ ቃል በጉራጌ ዞን ከሚገኙ 17 ወረዳዎችና ከ4 ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ የአገራችን ታዋቂ የኪነ ጥበብ ሰዎች፣ አመራሮች፣ የሲቪል ሰርቪስ (civil service) ሠራተኞች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በወልቂጤ ከተማ ትልቅ ስብሰባ/ውይይት በድምቀት ተካሂዷል።

    በዚህም ዞን አቀፍ የሰላም ንቅናቄ የአገራችን ታዋቂ ሰዎች (በጥቂቱ ለመጥቀስ ያህል ደራሲና መምህር ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፣ ደራሲ እንዳላጌታ ከበደ፣ ደራሲ ህይወት ተፈራ፣ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት ዳይሬክተር ጀነራልና የሙዚቃ ሀያሲው አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት እና ደራሲ ተስፋዬ ጎይቴ ስለ ሰላም እና በሰላም እጦት ምክንያት የሚከሰቱ አስከፊ ጉዳቶች ለታዳሚው አቅርበዋል። የሁሉም የመቋጫ ሀሳብ የአገራችን ህዝቦች አጥር ሳይገድባቸው በብሔር፣ በዘር፣ በጎሳ፣ በሀይማኖትና በመሳሰሉ ከፋፋይ ጉዳዮችን ትተው በአንድነትና በሰብዓዊነት ስሜት ተዋደውና ተቻችለው እንደቀድሞው አብረው ሊኖሩ እንደሚገባ ነው።

    በዚህ ታላቅ የሰላም ንቅናቄ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ጀማልና የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ወ/ሮ መሠረት አመርጋ ሰላም ለሁሉም ጉዳዮች መሠረት መሆኑ እና ሰላም በሌለበት ምንም ሊኖር እንዳማይችል ገልፀው የዞኑ ህዝብ በሙሉ ለሰላም ዘብ መቆም እንዳለባቸው አሳስበዋል።

    “ጥበብ ለሰላም” በሚል በተካሄድው በዚህ መርሀግብር ታዋቂ የአገራችን ደራሲያን፣ የጉራጌ ዞን የባህል ኪነት ቡድን፣ ከወልቂጤና ከቡታጅራ ከተማ አስተዳደሮች የኪነ ጥበብ ክበባት የተውጣጡ አማተር ኪያንያን ድንቅ የሙዚቃ፣ ድራማና የሥነ ግጥም ሥራዎቻቸውን አቅርበዋል። እንዲሁም በሱዑዱ አብደላ የተሳሉ ድንቅ የሥነ ስዕል ሥራዎቹን አቅርቧል። የ11ኛ ክፍል ተማሪ ይዘዲን የፈጠራ ሥራዎች በመድረኩ ከቀረቡ ሥራዎች ይገኝበታል።

    በመጨረሻም ለፕሮግራሙ መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የዞኑ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ያዘጋጃቸው ባህላዊ ስጦታዎች፣ የማበረታቻ ሽልማትና የምስጋና የምስክር ወረቀት አበርክቷል።

    ምንጭ፦ የጉራጌ ዞን አስተዳደር የሕዝብ ግንኙነት ቢሮ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ጥበብ ለሰላም መድረክ በጉራጌ ዞን


    Anonymous
    Inactive

    ሃገራዊውን የግብር ንቅናቄ በደቡብ ክልል ለማስቀጠል በአዲስ አበባ ከተማ የሩጫ ውድድር ሊካሄድ ነው
    —–

    አዲስ አበባን ጨምሮ በአማራና በትግራይ ክልሎች የተጀመረውን የግብር ንቅናቄ በማስቀጠል በአዲስ አበባ ከተማ የሩጫ ውድድር ሊያካሂድ መሆኑን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

    የገቢዎች ሚኒስትር ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግላጫ እንዳስታወቁት÷ “ግብር ለሃገሬ “ በሚል መሪ ቃል የካቲት 10 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ የሩጫ ውድድር እንደሚካሄድ ገልጸዋል፡፡

    ሚኒስትሯ የግብር ንቅናቄው በሀገር አቀፍ ደረጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው የተናገሩት፡፡

    ሁሉም የሚሳተፍበት የእምዬን ለእምዬ በሚል መርህ የስዕልና የሙዚቃ ድግስ የካቲት 17 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚካሄድም ተናግረዋል፡፡

    ሚኒስትሯ በሀገሪቱ ግብር መክፈል ከነበረባቸው ዜጎች መካከል 60 በመቶ ያህሉ ብቻ እንደሚከፍሉ ገልጸዋል፡፡

    ደረሰኝ ከመስጠትና ከመቀበል ጋር በተያያዘም እስካሁን የግንዛቤ ችግሮች መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡

    በሚኒስቴሩ በግብር ማጭበርበርና ስወራዎች ላይ በተደረገ ክትትል ከ2 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷልም ነው ያሉት።

    ሃገሪቱ ከግብር ስወራና ማጭበርበር ጋር በተያያዘ 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ማጣቷንም አንስተዋል።

    ኤፍ.ቢ.ሲ

    Anonymous
    Inactive

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ግጭት ላለባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አርአያ ነው — አፈ ጉባዔ ኬሪያ ኢብራሂም
    —–

    በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ያለው ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ሌሎች ግጭት ላለባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አርአያ እንደሆነ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ገለፁ።

    በዞኑ ያለው ሰላምና መረጋጋት በተምሳሌትነት የሚጠቀስ መሆኑን አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም ተናግረዋል።

    በደቡብ ብሔር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ውስጥ የሚገኙ 16 ብሄረሰቦች የተሳተፉበት የባህል ፌስቲቫል ጥር 27 ቀን 2011 ዓ.ም. በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ተካሄዷል።

    ፌስቲቫሉ በዞኑ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀ ሲሆን “ባህላዊ እሴቶች ለአብሮነትና ለልማት” በሚል መሪ ቃል ነው የተካሄደው።

    አፈ ጉባዔዋ ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም በፌስቲቫሉ መክፈቻ ላይ እንደገለጹት፤ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ያለው ሰላምና መረጋጋት ለመማር ማስተማር ስራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተ በመሆኑ ለሌሎች ግጭት ላለባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አርአያ ነው።

    በርካታ ብሄረሰቦች የሚኖሩበት ዞኑ በአካባቢው ያለው ሰላምና መረጋጋት በአገር አቀፍ ደረጃ በተምሳሌትነት የሚጠቀስ ነውም ብለዋል።

    በዩኒቨርሲቲው የተካሄደው ፌስቲቫል በዞኑ ያለውን ቋንቋ፣ ባህልና ታሪክ ለማስተዋወቅ የሚረዳ መልካም ተግባር እንደሆነም ተናግረዋል።

    እንዲሁም የዞኑን ባህልና እሴቶች ለሌሎች አካላት ለማሳወቅ የጀመራቸው የጥናትና ምርምር ስራዎች ወሳኝ መሆናቸውን አንስተዋል።

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ እንዳሉት፤ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ አካባቢያዊ ጥናትና ምርምሮች ወሳኝ ሚና ያላቸው በመሆኑ አገር በቀል እውቀትን ለተማሪዎችና ለኀብረተሰቡ ለማሳወቅ ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የጀመረው ጥናትና ምርምር ያለው ፋይዳ የጎላ ነው።

    ዩኒቨርስቲው በሳይንስና ቴክኖሎጂ በመደገፍ በተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ለሚማሩ ተማሪዎች በኮምፒዩተር አማካይነት የሚሰጠውን መጽሕፍ አቅርቦት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አሳስበዋል።

    ዩኒቨርሲቲው በዞኑ ባህልና እሴቶች ላይ ለሚካሄዱ ጥናትና ምርምሮች የልህቀት ማዕከል በመሆን ማገልገል እንዳለበት ፕሮፌሰር አፈወርቅ ጠቁመዋል።

    የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ገብሬ ይምቲሶ በበኩላቸው ከዚህ በፊት በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ ብሄረሰቦች የሚያስተዋውቅ ፌስቲቫል ባለመካሄዱ የብሔረሰቦቹን ባህልና እሴት በማስተዋወቅ ረገድ የሚፈለገው ያህል አልተሰራም ብለዋል።

    በዚህም ምክንያት ዩኒቨርሲቲው የሚጠበቅበትን ማህረሰባዊ አገልግሎት ለኀብረተሰቡ አለመስጠቱን ተናግረዋል።

    ዘንድሮ የባህል ፌስቲቫሉ ለመጀመሪያ ጊዜ መዘጋጀቱ 16ቱ ብሔረሰቦች እርስ በርስ እንዲተዋወቁና የባህል ልውውጥ እንዲያደርጉ ምቹ አጋጣሚ የፈጠረ በመሆኑ ወደፊት ቀጣይነት ባለው መልኩ እንደሚካሄድም አመልክተዋል።

    የፌስቲቫሉ ዓላማ በዞኑ የሚገኙ ብሔረሰቦችን ከማቀራረብ ባሻገር ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የመጡ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የ16ቱን ብሔረሰቦች ቋንቋ፣ ባህልና እሴት እንዲያውቁ ማድረግ እንደሆነም ገልጸዋል።

    እንዲሁም በዞኑ ግጭቶች ሳይከሰቱ የአገር አንድነትና ሰላም ለማስጠበቅ ወሳኝ ሚና እንዳለውም ፕሮፌሰር ገብሬ አስረድተዋል።

    በፌስቲቫሉ የዞኑ ብሔረሰቦች የምግብ፣ የሙዚቃና የዕደ-ጥበብ ስራዎች ለእይታ የቀረቡ ሲሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ተገኝተዋል።

    የደቡብ ኦሞ ዞን በባህል ብዝሃነት የሚታወቅና በበርካታ የውጭ አገር ዜጎች የሚጎበኝ አካባቢ ነው።

    የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት

    Semonegna
    Keymaster

    ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ አዲስ ያወጣው “ሲያምሽ ያመኛል” የተሰኘው የሙዚቃ አልበም አስራ አንድ ዓመታትን እንደፈጀ፤ በግጥም፣ በዜማ እና በቅንብር ከአስራ ሦስት ባለሙያዎች በላይ እንደተሣተፉበት እና ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ፈሰስ እንደተደረገበት ተዘግቧል።

    አዲሰ አበባ (ሰሞነኛ) – በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የተወዳጁ ድምፃዊ ጎሳዬ ተስፋዬ አምስተኛ ሙሉ የአልበም ሥራው የሆነውና “ሲያምሽ ያመኛል” የተሰኘው የሙዚቃ አልበም ታህሳስ 26 ቀን 2011 ዓ.ም. በኢትዮጵያና በመላው ዓለም በገበያ ላይ ውሏል።

    አራተኛ አልበሙን “ሳታመሃኝ ብላ” በሚል ርዕስ ካወጣ ከ11 ዓመታት በኋላ ለአድናቂዎቹ ያቀረበው ይህ አዲስ አልበም፥ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበት አከፋፋዩ “ሪቮ ኮሚዩኒኬሽንና ኢቨንት” መግለጹን ሳምንታዊ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ዘግቧል።

    በኢትዮጵያ ሙዚቃ ተጽዕኖ ፈጣሪ ከሚባሉትትና የላቀ እውቅናን ከተጎናጸፉት ድምፃዊያን አንዱ የሆነው የድምፃዊ ጎሳዬ ተስፋዬ አዲስ አልበም፣ ለረጅም ጊዜ በጉጉት ሲጠበቅ የቆየ ሲሆን፥ ደረጃውን የጠበቀና የተዋጣለት አልበም ለማድረግ ሲባል 11 ዓመታትን መፍጀቱንና ግጥምና ዜማቸው ተሠርተው ከተጠናቀቁ ከ40 በላይ ሥራዎች ውስጥ 15ቱ ተመርጠው በዚህ አልበም መካተታቸውን አከፋፋዩ ጨምሮ ገልጿል።

    አማርኛ ሙዚቃ፦ ድምጻዊ እሱባለው ይታየው — ዘፈን ማሞቂያ አይደለም

    በዚህ አዲስ አልበም ላይ ከተሳተፉ እውቅ የሙዚቃ አቀናባሪዎች መካከል አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ፣ ካሙዙ ካሳአቤል ጳውሎስ፣ መኮንን ለማ (ዶክተሬ)፣ ሚካኤል ኃይሉ (ሚኪ ጃኖ) እና ሱልጣን ኑሪ (ሶፊ) እንደሚገኙበት የገለፀው አከፋፋዩ፥ በግጥምና ዜማውም ከዚህ ቀደም በሠሩት ሥራ አንቱታን ያተረፉት አለምፀሐይ ወዳጆ፣ ይልማ ገ/አብ፣ ሀብታሙ ቦጋለ፣ ቢኒያም መስፍን (ቢኒባና)፣ አለማየሁ ደመቀ፣ መሰለ ጌታሁን እና ራሱ ጎሳዬ ተስፋዬ ተሳትፈውበታል ተብሏል።

    በአገራዊ፣ በማኅበራዊ እና በፍቅር ዙሪያ የሚያጠነጥኑ 15 ሙዚቃዎችን ያካተተው “ሲያምሽ ያመኛል” አልበም ሪከርድ የተደረገው በአሜሪካ ኒው ዮርክ ሲቲ ሲሆን ጥራትና ደረጃውን የጠበቀና ዘመኑ ያፈራው የሪከርዲንግ ቴክኖሎጂ አሻራ ያረፈበት መሆኑም ታውቋል።

    ጎሳዬ ተስፋዬ ከዚህ ቀደም “ሶፊ”፣ ከሌሎች ድምፃዊያን ጋር “ቴክ ፋይቭ”፣ ከአለማየሁ ሂርጶ ጋር “ኢቫንጋዲ” እና በ1999 ዓ.ም ለብቻው የሠራውን “ሳታመሃኝ ብላ” የተሰኙ የሙዚቃ አልበሞችን ለአድናቂዎቹ ማቅረቡ ይታወሳል።

    ◌ ሲያምሽ ያመኛል አልበምን በዲጂታል ለመግዛት: CD Baby Siyamish Yamegnal by Gossaye Tesfaye

    ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ጎሳዬ ተስፋዬ

    Semonegna
    Keymaster

    ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ የያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ከተከፈተበት ከ1959 ዓ.ም. ጀምሮ ተቋሙንም በመምራት እንዲሁም ታላላቅ ባለሙያዎችን በማፍራት ለሙዚቃ ዕድገት አስተዋፅዖው የጎላ መሆኑን ለተሳታፊዎች አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት አውስቷል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)–በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ሥር ያለው የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ የሥነ-ጥበባት ማዕከል 40ኛ የጥበብ ውሎ መድረኩን ቅዳሜ ኅዳር 8 ቀን 2011 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ አካሒዷል።

    በዝግጅቱ ላይ የዕውቁ ኢትዮጵያዊ የሙዚቃ ሰው የፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ ሕይወትና ሥራዎች ላይ ውይይት እየተደረገ ተደርጓል። ሥራዎቹን እና ሕይወቱን አስመልክቶ የሙዚቃ ባለሙያ እና በቅርቡ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት ዳይሬክተር ጀነራል ሆኖ የተሾመው አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት የውይይት መነሻ ጥናት አቅርቦ በታዳሚዎች ውይይት ተካሂዶ ነበር።

    “ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ <ባለዋሽንቱ እረኛ>(The Shepherd Flutist)  በተሰኘ ታላቂ ሥራ የኢትዮጵያን መልክ በረቂቅ ሙዚቃ ያሳዩ ናቸው” በማለት አቶ ሠርፀ የገለጿቸው የሙዚቃውን ረቂቅነት በመጥቀስ ሲሆን፤ ፕሮፌሰር አሸናፊ የያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ከተከፈተበት ከ1959 ዓ.ም. ጀምሮ ተቋሙንም በመምራት እንዲሁም ታላላቅ ባለሙያዎችን በማፍራት ለሙዚቃ ዕድገት አስተዋፅዖው የጎላ መሆኑን ለተሳታፊዎች አውስቷል።

    በሙዚቃ ላይ ከሠሯቸው ከበርካታ የምርምር ሥራዎቻቸው ውስጥ “Roots of Black Music” የተሰኘው መጽሐፋቸው በብዙ የዓለማችን የሙዚቃ አጥኚዎች የተዘነጉ (የተዘለሉ) የአፍሪካ/የምሥራቁ ዓለምን የሙዚቃ ስልትና ፍልስፍናን አጉልተው ለተቀረው ዓለም ያሳዩበት እንደሆነም አቅራቢው አብራርተዋል።

    በውይይቱም ከተሳታፊዎች የኢትዮጵያ ሙዚቃ በዘመናት መካከል የመድመቅና መልሶ የመደብዘዝ ችግር ከምን የመነጨ እንደሆነ ጥያቄ የቀረበ ሲሆን፥ “ዋናው ችግር በተለያዩ ምክንያቶች የኢትዮጵያ ሙዚቃ ተቋም ፈርሷል፤ እሱን መልሶ መገንባት የቤት ሥራችን ነው” ብለዋል አቶ ሠርፀ። አክለውም የኢትዮጵያ የሙዚቃ ትምህርት ሥርዓት ከተመሠረተበት ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ከምዕራባውያን የሙዚቃ ሥርዓተ-ትምህርት ነፃ መውጣት ያለመቻሉም ሌላ ምክንያት እንደሆነ አቅራቢው ጠቅሰዋል።

    ውይቱን የመሩት የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ የሥነጥበባት ማዕከል ዳይሬክተር አቶ እንዳለጌታ ከበደ በበኩላቸው ለኢትዮጵያ ሥነ ጥበብ ማደግ ብርቱ ጥረት ያደረጉ የጥበብ ሰዎችን ፈለግ እና ሥራዎቻቸውን ለተተኪው ትውልድ ለማውረስ በሁሉም አካላት ጥረት መደረግ አለበት ብለዋል።

    ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት 8 ቀን 1930 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው፣ እናታቸው ደግሞ ወ/ሮ ፋንታዬ ነከሬ ያባሉ ነበር። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ቢሆኑም ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እናታቸውን በሞት አጥተዋል።

    ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (አሁን ኮከበ ጽባሕ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት የሚባለው) ካጠናቀቁ በኋላ ከሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከዚያም ወደ አሜሪካ በማቅናት ኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ሮቸስተር፣ ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት (University of Rochester’s Eastman School of Music) በ1954 ዓ.ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ በመመለሰ የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤትን መሥርተዋል። የትምህርት ቤቱም የመጀመሪያው ዳይሬክተር ከመሆናቸውም ባሻገር በመሆን ሙዚቃን ከማስተማሩ ባሻገር አገልግለዋል። በተጨማሪም በአዲስ አበባ የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ.)፣ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር።

    በድጋሚ ለከፍተኛ ትምህርት ወደ አሜሪካ ተመልሰው፣ ኮነቲከት ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው ዌስልያን ዩኒቨርሲቲ (Wesleyan University) በ1961 ዓ.ም የማስትሬት፣ እንዲሁም በ1963 ዓ.ም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ምዕራባዊ ባልሆኑ ሙዚቃዎች ምርምር (ethnomusicology) አግኝተዋል።

    ከሙዚቃው መምህርነትና ተመራማሪነት ባሻገር ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ ደራሲም ነበሩ። እ.ኤ.አ በ1964 ዓ.ም ኮንፌሽን (Confession)፣ እ.ኤ.አ በ1982 ዓ.ም ሩትስ ኦፍ ብላክ ሙዚክ (Roots of Black Music) የሚሉ መጻሕፍትን ያሳተሙ ሲሆን፣ በሙዚቃ ላይ ያተኮሩ በርካታ ጽሁፎችን፥ በተለይም ደግሞ በአፍሪካ-አሜሪካውያን ባህልና አኗኗር ላይ ለሚያተኩረው “The Chronicler” ለተሰኘው መጽሔት ጽፈዋል።

    በአሜሪካ ፕሮፌሰር አሸናፊ ኑሯቸው ፍሎሪዳ ክፍለ ሀገር በሚገኘው ፍሎሪዳ ስቴት ዩኒቨርሲቲ (Florida State University) የሙዚቃ ኮሌጅ ውስጥ በመምህርነት የሠራ ሲሆን፣ ተቀማጭነቱን እዚያው አሜሪካ ያደረገውናታዋቂውን የኢትዮጵያ ምርምር ካውንስልን (Ethiopian Research Council) በዳይረክተርነት መርቷል።

    ፕሮፌሰር አሸናፊ ከመጀመሪያ ኢትዮጵያዊ ባለቤታቸው (ወ/ሮ እሌኒ ገብረመስቀል) እና ሁለተኛ ባለቤታቸው (አሜሪካዊ) አራት ልጆችን (ሦስት ሴቶችና አንድ ወንድ) ልጆችን አፍርተዋል። ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ የ60ኛ የልደት በዓላቸው ዕለት በመኖሪያ ቤታቸው ግልጽ ባልሆነ ምክንያት ሞተው የተገኙ ሲሆን፤ ምናልባትም የራሳቸውን ሕይወት ሳያጠፉ እንዳልቀሩ ብዙዎች ይገምታሉ።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ
    PHOTO: Ethiopian Academy of Sciences

    Semonegna
    Keymaster

    ከህመሜ እስከ ስደቴ አብሮኝ ለታመመውና በመንፈስ አብሮኝ ለተሰደደው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ለመገናኘት አበቃን –  የባህል ሙዚቃ አቀንቃኙ አርቲስት ፋሲል ደመወዝ በባሕር ዳር ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አቀባበል ላደረጉለት ወዳጆቹ እና አድናቂዎቹ

    ባሕር ዳር (አብመድ)– ላለፉት ስድስት ዓመታት ኑሮውን በአሜሪካ ያደረገውና የባህል ሙዚቃ አቀንቃኙ አርቲስት ፋሲል ደመወዝ ባሕር ዳር ገብቷል። በባሕር ዳር ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስም አድናቂዎቹ አቀባበል አድርገውለታል።

    የሀገር ፍቅር ስሜቱ ከፍተኛ እና ያመነበትን የሚያቀነቅን እንደሆነ የሚነገርለት አርቲስት ፋሲል ደመወዝ በህዝቡ ዘንድ ተወዳጅ ነው። “ነፃነት በተነፈገው ህዝብ መካከል በኖርኩባቸው ዓመታት ከህመሜ እስከ ስደቴ አብሮኝ ለታመመውና በመንፈስ አብሮኝ ለተሰደደው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ለመገናኘት አበቃን” ያለው አርቲስት ፋሲል ከዚህ ጋር አያይዞም “መድረክ ላይ እንዳልዘፍን የተከለከልኳቸውን የሙዚቃ ስራዎቸን በዚህ ህዝብ ፊት ለማቅረብ በመታደሌ ደስተኛ ነኝ” ብሏል።

    በቀጣይ በተለያዩ ቦታዎች ተንቀሳቅሰህ ህዝብን የማግኘት ዕድል እንደሚኖረው በአቀባበሉ ላይ የተገኙ ጋዜጠኞች ላቀረቡለት ጥያቄ ምላሽ ሲሰጥ አርቲስቱ ከአሜሪካን ሀገር ወደ አገር ቤት ያመጡኝ አስተዋዋቂዎች (ፕሮሞተሮች) የሚያውቁት ሆኖ እስካሁን ባለኝ መረጃ በባሕር ዳር ከተማ አንድ የሙዚቃ ድግስ መኖሩን ነው በማለት ምላሽ ሰጥቷል።

    “ድግስ ጠርቻችኋለሁ” ያለው አርቲስት ፋሲል ደመወዝ ስለታገላችሁለት ነፃነት በነፃነት እንጫዎታለን ነው ያለው። በአርቲስቱ የአቀባበል ሥነ ስርዓት ላያ የተገኙት እማሆይ ፀሃይ ዓለሙ “ፋሲልን በስራዎቹ እና በሀገር ፍቅሩ እወደዋለሁ” መጣ ሲባል ስለሰማሁ እንኳን ለሀገርህ አበቃህ ለማለት ነው የመጣሁት በማለት ለየአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ጋዜጠኞች መልስ ሰጥቷዋል።

    በተመሳሳይ የቀድሞ ጓደኛው እና የሥራ ባልደረባው አርቲስት ቹቹ ምስጋናው ለፋሲል ያለው ፍቅር እና አክብሮት የተለየ መሆኑን ገልፆ “ለኢትዮጵያ ገና በርካታ ሥራዎችን የሚሠራ እና አሉ ከሚባሉ የባህል ሙዚቀኞች አንዱ በመሆኑ እንኳን ወደ ሀገሩ በሰላም ገባ” ሲል በአርቲስቱ መምጣት የተሰማውን ደስታ ገልጻል።

    የአርቲስት ፋሲል ደመወዝ እህት እስከዳር ደመወዝ በወንድሟ ወደ ሀገር መመለስ የተሰማት ደስታ ከፍተኛ መሆኑን ገልጻ በህመሙ እና በስደቱ ወቅት ከጎኑ ለነበረው ህዝብ ምስጋናዋን አቅርባለች።

    አርቲስት ፋሲል ደመወዝ በባሕር ዳር ስታዲየም ህዳር 1 ቀን 2011 ዓ.ም “ሀገሬ ኮንሰርት” በሚል መሪ ሃሳብ የሙዚቃ ሥራዎቹን ለህዝብ ያቀርባል ተብሎም ይጠበቃል ሲል የዘገበው አብመድ ነው።

    አርቲስት ፋሲል ደመወዝ ወደ አሜሪኣ ከተሰደደ በኋላም የሙዚቃ ሥራውን አድናቂዎቹ ያቀርብ የነበረ ሲሆን የተለያዩ ነጠላ ሙዚቃዎችን፣ እንዲሁም አማርኛ ሙዚቃ አድማጭ ዘንድ እጅግ ተቀባይነት ያገኘለትን “እንቆቅልሽ” የተሰኘ አልበም ሠርቷል። በአሜሪካ እና በካናዳ የተለያዩ ግዛቶችም እየተዘዋወረ የሙዚቃ ዝግጅቶች (ኮንሰርቶች) ላይ ከአድናቂዎቹ ጋር ተገናኝቷል። አሜሪካ ውስጥ ፍሎሪዳ ግዛት ካቀረበው ኮንሰርት ላይ የተቀነጨበውን እዚህ ጋር ይመልከቱ

    ምንጭ፦ የአማራ መገናኛ ብዙሀን ድርጅት (አብመድ)

    አርቲስት ፋሲል ደመወዝ

    Semonegna
    Keymaster

    “… እኛ እንደ ባለሞያ እንደ ወጣት ለሚፈጸሙ ነገሮች ቲፎዞ ልንሆን አንችልም። እገሌን እደግፋለሁ፣ እገሌን አስቀድማለሁ ሳይሆን… የምናየው የኛ አገር ነው። ካፌው አገርን ነው የሚመስለው።…” ምን ልታዘዝ ድራማ መሪ ተዋናይ ሚካኤል ታምሬ። “… ካፌ በተፈጥሮ ብዙ ሃሳብ ማስገባትና ማስወጣት ይፈቅዳል። እናም እንዲያ ማድረግ እፈልግ ነበር።…” የትዕይንቱ ጸሐፊና ዳይሬክተር በኃይሉ ዋሴ (ዋጄ)።

    (የአሜሪካ ድምጽ) – “ሳታየር” (ስላቅ) ከተሰኘው የጥበብ ዘርፍ የሚመደብ፣ ፈጥኖም የብዙዎች የተከታታዮቹን ቀልብ ለመሳብ እና ተወዳጅነት ለማትረፍ ጭምር የታደለ ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ ነው – “ምን ልታዘዝ!”

    በቀልዳ ቀልድ ለዛ የተዋበው ፖለቲካዊ ሥላቅ (political satire)፣ በሥነ ጽሁፍ፥ በመድረክ አለያም በሥዕላዊ ሥራዎች አማካኝነት በማኅበረሠብ ውስጥ እየታዩ ያሉ ማኅበራዊ ህጸጾችንና ክስረቶችን ለመንቀስና ለመተቸት የሚሳል የጥበብ ዘዬ ነው። ፈታ-ዘና ብለው እንዲከተሉት የሚፈቅደው ይህ የጥበብ ዘዬ ታዲያ በአጫጭር ትዕይንቶች ይሞላ እንጅ ከኮርኳሪነቱ ጋር ቀልጠፍ ያለው ቅብብል ጭብጡን በቅጡ ከታዳሚው ከማድረስ አያገደውም።

    ዘዬው በግለሰቦች የተፈጸሙ ድርጊቶችን ብቻ ሳይሆን በቡድኖች፣ አለያም በተቋማት፣ በአስተዳደርና በመንግስት ሲደረጉ የሚስተዋሉ ነገር ግን “ያልሆኑ” ጉዳዮች ይተቻል፤ ያጣጥላል።

    በሚያዝያ ወር 2010 ዓ.ም በፋና ቴሌቪዥን በየሳምንቱ እሁድ መተላለፍ የጀመርው ምን ልታዘዝ አስቂኝ የቴሌቪዥን ድራማ በኅብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ለማግኘት ብዙም ጊዜ አልፈጀበተም። ጥቅምት 13 ቀን 2011 ዓ.ም ግዮን ሆቴል በተከናወነው ስምንተኛው ለዛ የአድማጮች ምርጭ ሽልማት ላይ በምርጥ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ አሸናፊ ለመሆን ችሏል። በበኃይሉ ዋሴ (ዋጄ) እና ደመወዝ ጎሽሜ ተደርሶና ዳይሬክት ተደርጎ፣ በሁሰት ፊልም ፕሮዳክሽን ተሠርቶ የሚቀርበው ምን ልታዘዝ ጥቅምት 18 ቀን 2011 ዓ.ም ሁለተኛ ምዕራፉን ሲጀመር በመጀመሪያው ትዕይንት ላይ ታዋቂዋን አርቲስት ዓለምፀሐይ ወዳጆን በተጋባዥ ተዋናይነት (guest star) አሳትፏት ነበር።

    ምን ልታዘዝ

    ከምን ልታዘዝ ካፌ እንዝለቅ። የትዕይንቱ ጸሃፊና ዳይሬክተር በኃይሉ ዋሴ እና መሪ ተዋናዩ ሚካኤል ታምሬ እየጠበቁን ነው።

    ደራሲው በኃይሉ ዋሴ (ዋጄ) እና መሪ ተዋናዩ ሚካኤል ታምሬ ከአሜሪካ ድምጽ የአማርኛ ዝግጅት ክፍል ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ የመጀመሪያ ክፍል እዚህ ጋር በመጫን ያዳምጡ።

    ምን ልታዘዝ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ
    ደራሲና ዳይሬክተር፦ በኃይሉ ዋሴ (ዋጄ) እና ደመወዝ ጎሽሜ
    ረዳት ዳይሬክተር፦ ምትኩ በቀለ እና ዓለማየሁ አጅበው
    ሲኒማቶግራፊና ኤዲተር፦ ታምሩ ጥሩዓለም
    ተዋንያን፦ ሚካኤል ታምሬ፣ መስፍን ኃይለየሱስ፣ ሰለሞን ሙሄ፣ መስከረም አበራ፣ ዘቢባ ግርማ፣ ሰለሞን ተስፋዬ፣ አያሌው አስረስ
    ፕሮዳክሽን ማናጀር፦ ዓለማየሁ አጅበው
    ሙዚቃ፦ ታደለ ፈለቀ
    ግራፊክስ፦ ዘአማኑኤል አበራ
    ድምጽ፦ አግኝቻለሁ ምስጋና እና ናትናኤል ጌታቸው
    ፕሮዳክሽን አስተባባሪ፦ ግሩም ሽቶ እና ደመቀ አበራ
    ፕሮዲዩሰር፦ በኃይሉ ዋሴ (ዋጄ) እና አያልነህ ተሾመ
    ሁሰት ፊልም ፕሮዳክሽን ካሜን ፊልምስ

    ምን ልታዘዝ

    Semonegna
    Keymaster

    በኢትዮጵያውያን የኪነ ጥበብ አድናቂዎች ዘንድ ተወዳጅነት እያተረፈ የመጣው ለዛ የአድማጮች ምርጫ ሽልማት ዘንድሮ ለስምንተኛ ጊዜ ጥቅምት 13 ቀን 2011 ዓ.ም በሂልተን ሆቴል፣ አዲስ አበባ፣ እጅግ በደመቀ ሁኔታ ተከናውኗል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – በሀገራችን የሙዚቃ ታሪክ እጅግ መቀዛቀዝ፣ የሙዚቃ አልበምም ህትመት መፍዘዝ፣ ፊልም ሠሪዎችም ሥራዎቻችውን ተመልካቾች ፊታቸውን ባዞሩባቸው በዚያ ወቅት እንደ አንድ የኪነጥበብ አባልና የሚዲያ ባለሙያ አቅማቸው በፈቀደ የበኩላቸውን አስተዋጽዖ ለማበርከት፣ እንዲሁም አድማጭ ተመልካቹን ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ለማነቃቃት በማሰብ ነበር ጋዜጠኛ ብርሀኑ ድጋፌ እና ባልደረቦቹ በሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ላይ “ለዛ የአድማጮች ምርጫ ሽልማት” ሥነ ስርዓትን የየጀመሩት።

    በእርግጥ ኪነ ጥበብና ኢትዮጵያ ሀገራችን በባህላዊውም ሆነ በዘመናዊው መንገድ እጅግ ብዙ ዓመታትን ያስቆጠረ ቁርኝት ቢኖራቸውም ቅሉ የኪነ ጥበብ ሙያዉን እንደተከበረ ሙያ ባለሙያዉንም የተከበረ ሙያ እንዳለው ቆጥሮ ወቅት ጠብቆ በተገደበ የጊዜ ኡደት ለሙያውና ለባለሙያው ተገቢውን ዕውቅና፣ ብሎም ክብር የሚሰጥ ቋሚ ተቋም ባለመኖሩ ያለመኖሩን በማስገንዘብ የሥነ ስርዓቱ ሀሳብ ጠንሳሾች “ለምን እኛ የቻልነውን አናደርግም?” በሚል ነበር የኪነ ጥበብ ሰዎችን በዓመት አንድ ጊዜ እያሰባሰቡ ለማወያየት፣ በዓመቱ በሙያውና በሙያቸው ጉልህ አስተዋጽዖ ያደረጉትን “በጎ ሥራ ሠርታችኋል! ይበል!” ለማለት ለዛ የኤድማጮች ምርጫ ሽልማትን በ2003 ዓ.ም የጀመሩት።




    በ2003 ዓ.ም በተደረገው የመጀመሪያ ሽልማት ‘የዓመቱ ምርጥ ነጠላ ዜማ’፣ ‘ምርጥ ተዋናይት’፣ ‘የዓመቱ ምርጥ ተዋናይ’፣ ‘የዓመቱ ምርጥ ፊልም’ እና ‘የዓመቱ ምርጥ አልበም’ በሚሉ አምስት ዘርፎች (ዘውጎች) ኢትዮጵያውያን የኪነ ጠበብ ሰዎች ተመርጠው የተሸለሙ ሲሆን ሽልማቱም ያገኙትም ከያኒት ዘሪቱ ከበደ “አርቴፍሻል” በሚለው ነጠላ ሙዚቃዋ፣ ተዋናይት ሰሃር አብዱልከሪም “ያንቺው ሌባ” በተሰኘ ፊቸር ፊልም ላይ ባሳየችው ትወና፣ ጋሽ አበበ ባልቻ “ሄሮሺማ” በተሰኘ ፊቸር ፊልም ላይ ባሳየው ትወና፣ “ሄሮሺማ” ፊቸር ፊልም በምርጥ በፊልምነት፣ እንዲሁም ከያኒ ናትናኤል አያሌው (ናቲ ማን) በመጀመሪያው አልበሙ በአምስቱ የተዘረዘሩት ዘርፎች አሸናፊዎች ሆነው የሥነ ስርዓቱ የበኩር ተሸላሚዎች ሆኑ።

    በዚህ መልኩ የተጀመረው ለዛ የአድማጮች ምርጫ በየዓመቱ ከጥቅምት ወር ጀምሮ እስከ ሃምሌ ድረስ የሚወጡ የኪነ ጥበብ ሰዎችንና ሥራዎችን በአድማጮች ምርጫ አወዳድሮ ዕውቅና እየሰጠ፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተሳታፊዎችን እያበዛ፣ በባለሙያዉም፣ በመራጭነት በሚሳተፈውም ይሁን በየበይ ተመልካችነት በሚከታተለው ኢትዮጵያዊ ዘንድም ተወዳጅነት እያተረፈ ዘንድሮ ለስምንተኛ ጊዜ ጥቅምት 13 ቀን 2011 ዓ.ም በሂልተን ሆቴል፣ አዲስ አበባ፣ እጅግ በደመቀ ሁኔታ ተከናውኗል። ከሁለት ወራት በፊት በተካሔደው ዘጠነኛው አዲስ የሙዚቃ ፌቲቫል ላይ የዓመቱ ምርጥ አርቲስት ተብሎ የተሸለመው ድምጻዊ ሮፍናን ኑሪ በዚህ ሥነ ስርዓትም ላይ ተመሳሳይ ሽልማት፣ ሌሎች ሁለት ሽልማቶችን ጨምሮ አሸንፏል። በስምንተኛው ለዛ የአድማጮች ምርጫ ሽልማት፦

    ● ምርጥ ነጠላ ዜማ፦ “ጨረቃ” (ሮፍናን ኑሪ)፣
    ● ምርጥ አዲስ ድምፃዊ፦ ሮፍናን ኑሪ (“ነፀብራቅ” በተባለው የሙዚቃ አልበሙ)
    ● ምርጥ የሙዚቃ አልበም፦ ነፀብራቅ (ሮፍናን ኑሪ)
    ● ምርጥ የሙዚቃ ክሊፕ፦- የመጀመርያዬ (ናትናኤል አያሌው/ናቲ ማን):-
    ● ምርጥ ተዋናይት፦ አዚዛ አህመድ “ትህትና” በተሰኘ ፊቸር ፊልም ላይ ባሳየችው ትወና፣
    ● ምርጥ ተዋናይ፦ አለማየው ታደሰ “ድንግሉ” በተሰኘ ፊቸር ፊልም ላይ ባሳየው ትወና፣
    ● ምርጥ ፊልም፦ “ድንግሉ”
    ● ምርጥ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ፦ ምን ልታዘዝ?

    አሸናፊ ሆነው ተሸልመዋል። በዚህ ሥነ ስርዓት ላይ እጅግ ለበርካታ ሙዚቀኞች የዘፈን ግጥም በመስጠት በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ ስሙ እጅጉን ጎልቶ የሚታወቀው የሙዚቃ ግጥም ገጣሚ (lyricist) ይልማ ገብረአብ “የ2010 ዓ.ም የኪነ ጥበባ በለውለታ” ሆኖ ልዩ የክብር ሽልማት ተሸልሟል። ገጣሚ ይልማ ገብረ አብ ከአንድ ሺህ በላይ የሙዚቃ ግጥሞችን ጽፎ ለተለያዩ ድምጻውያን አበርክቷል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ለዛ የአድማጮች ምርጫ


Viewing 10 results - 16 through 25 (of 25 total)