Search Results for 'ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ'

Home Forums Search Search Results for 'ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ'

Viewing 15 results - 16 through 30 (of 30 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    በምክክር በድረኩም የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አዲሱ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሐብታሙ አበበ ዩኒቨርሲቲውን በታታሪነት፣ በታማኝነት እና በቅንነት በማገልገል ዩኒቨርሲቲውን የልሂቃን ተቋም እና የመጀመሪያ ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ ለማድረግ ተግተው እንደሚሠሩ ገልጸዋል።

    ሆሳዕና ከተማ (ሰሞነኛ)– ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ለአራት ወራት ያህል ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንትነት መረጣ ሲያካሂድ ቆይቶ፥ ለመጨረሻ ዙርም ዶ/ር ሐብታሙ አበበ፣ ዶ/ር ኑሪ ላፌቦ እና ዶ/ር አብርሃም አለማየሁ አልፈው ነበር። ከእነዚህ ሦስት ዕጩ ተወዳዳሪዎች መካከልም ዶ/ር ሐብታሙ አበበ በአጠቃላይ ውጤት 69.57% በማስመዝገብ ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንትነት ብቁ መሆናቸውን አስመስክረው፣ የኢፌዴሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚያዝያ 24 ቀን 2011 ዓ.ም. ለዩንቨርሲቲውና ለሚመለከታቸው ቢሮዎች በፃፈው ደብዳቤ ዶ/ር ሐብታሙ አበበን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ሆነው ተሹመዋል።

    የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ዶ/ር ሐብታሙ አበበ ለፕሬዝዳንትነት ሲወዳደሩ ያቀረቡትን የዩኒቨርሲቲውን የእድገት ስልታዊ ዕቅድ (University’s Development Strategic Plan) በይበልጥ ለማስገንዘብ እና በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የላቀ ታታሪነት፣ ትብብር እና ስኬታማ የመማር ማስተማር፣ የምርምር እና የማኅበረሰብ አገልግሎት ስኬቶችን ለማስመዝገብ የሚያስችላቸውን የመጀመሪያ ዙር ምክክር ከማኅበራዊ ሳይንስ፣ ንግድ እና ምጣኔ ሀብት (Business and Economics)፣ ከግብርናና ከተፈጥሮ ሀብት ኮሌጆች እና ከሕግ ትምህርት ቤት ጋር ግንቦት 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምረዋል።

    በምክክር በድረኩም ፕሬዝዳንቱ ዩኒቨርሲቲውን በታታሪነት፣ በታማኝነት እና በቅንነት በማገልገል ዩኒቨርሲቲውን የልሂቃን ተቋም እና የመጀመሪያ ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ ለማድረግ ተግተው እንደሚሠሩ በመግለጻቸው ከተሰብሳቢ መምህራን አድናቆት ከመቸራቸውም በላይ በጋራ ራዕያቸውን ለማሳካት ተግተው አብረዋቸው እንደሚሠሩ መምህራኑ ቃል ገብተውላቸዋል።

    ፕሬዝዳንቱ እያደረጉት ያለውን የምክክር መድረክ ቀጥለው ግንቦት 6 ቀን 2011 ዓ.ም. በዩንቨርሲቲው ዱራሜ ካምፓስ፣ ግንቦት 7 ቀን በዋናው ካምፓስ ምህንድስና (Engineering)፣ ጤና እና የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ (Natural and Computational Sciences) ኮሌጆች፣ በመጨረሻም ግንቦት 8 ቀን በዩንቨርሲቲው የንግስት እሌኒ መሐመድ መታሰቢያ ሆስፒታል እና ከዩኒቨርስቲው የአስተዳደር ሠራተኞች ጋር እእንደሚቀጥል ታውቋል።

    ዶ/ር ሐብታሙ አበበ በሐምሌ ወር 2011 ዓ.ም. አንድራ ፕራዴሽ (Andhra Pradesh) ግዛት (ደቡም ምስራቃዊ ህንድ) ውስጥ ከሚገኘው አንድራ ዩኒቨርሲቲ (Andhra University) የዶክትሬት ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።

    ምንጭ፦ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ሐብታሙ አበበ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መፃሕፍት ኤጀንሲ አሠራሩን ለማዘመን የሚያግዙ ሀሳቦች ላይ ከእንግሊዝ ቤተ መዛግብት ኃላፊዎች ጋር ምክክር አደረገ።

    በምክክሩ የቤተመዛግብት እና ቤተ መፃሕፍት አያይዝን ለማዘመን በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የእንግሊዙ አቻ ተቋም ልምድ ምን እንደሆነ ያወያየ ምክክር ሚያዚያ 29 ቀን 2011 ዓ.ም. በኤጀንሲዉ የቪዲዮ ኮንፈረንስ አዳራሽ ተካሄደ። ለውይይቱ መክፈቻ የኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ የኩኖአምላክ መዝገቡ ለእንግዶቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ ኢትዮጵያ የብዙ መዛግብቶች መገኛና ባለቤት ብትሆንም እንኳን ያላትን ሀብት ለራሷም ለዓለምም ለማበርከት የዘመናዊ ቴክኖሎጂ እጥረት እንዳለባት በማንሳት ይህንን ክፍተት የእንግሊዝ ቤተ መዛግብት የቴክኖሎጂ ሽግግር እገዛ አንዲያደርግላቸዉ ጠይቀዋል።

    በመቀጠል በእንግሊዝ ቤተ መዛግብት የኤሲያና የአፍሪካ የመዛግብት ስብስብ ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ሊዊሳ ኤሌና ሜንጎሊ (Luisa Elena Mengoni, Head of Asian and African Collections at the British Library) እንዳሉት በሁለቱ ሀገራት ዉስጥ ያሉ ተመራማሪዎች፣ ደራሲያን፣ እንዲሁም ሌሎች ፀሐፍት የእርስ በእርስ የልምድ ልዉዉጥ እንዲያደርጉ መንገዱን ማመቻቸት ለስነ-ፅሑፍ እድገት አስፈላጊ እንደሆነ ተናግረዋል።

    አቶ ክርስቲያን ጄንሰን (Kristian Jensen) የእንግሊዝ ቤተ መዛግብት ኃላፊ እንዲህ አይነት የምክክር መድረኮች ክፍተቶችን ለመለየትና መፍትሔ ለማበጀት እንደሚጠቅሙና ቀጣይነት እዲኖራቸዉ በተለይም የሥነ-ፅሑፍ ታሪኳ ከአክሱም ዘመነ መንግስት ጀምሮ ረጅም ዘመን ያስቆጠረ እንደ ኢትዮጵያ ያለች ሀገር ቤተ መፅሐፍቷና ቤተ መዛግብቷን በማዘመን ረገድ የእንግሊዝ ቤተመዛግብት እንደሚያግዝ ተናግረዉ፥ ኃላፊዉ የማይክሮ ፊልም (የመፅሐፍት ላይ ፅሑፎችን ወደ ሶፍት ኮፒ የሚቀይር መሣሪያ) በእርዳታ መስጠቷ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር በዶ/ር ሂሩት ካሳዉ በኩል ለኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ለአቶ የኩኖአምላክ መዝገቡ ርክክብ ከተደረገ በኋላ ባህላዊ የቡና ጠጡ ሥነ-ስርዓት ተከናዉኖ ዝግጅቱ ተጠናቋል።

    ምንጭ፦ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ቤተ መዛግብት


    Semonegna
    Keymaster

    የሳይንስና ክፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዶ/ር ጀማል አባፊጣ ከሚያዚያ 11 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ አዲሱ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነዉ እንዲያገለግሉ መርጧቸዋል። ዶ/ር ጀማል ዩኒቨርሲቲው ውስጥ እ.ኤ.አ ከ2003 ጀምሮ በተለያዩ የሥራ ቦታዎች አገልግለዋል።

    ጅማ (ሰሞነኛ) – ጅማ ዩኒቨርሲቲ ለፕሬዝዳንትነት ቦታ ብቃቱና ፍላጎት ያላቸዉ አመልካቾች እንዲወዳደሩ ጥር 24 ቀን 2011 ዓ.ም. በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ባወጣዉ ግልጽ ማስታወቂያ መሠረት አመልካቾች መረጃቸዉን በማስገባት በተለያዩ ደረጃዎች ዉድድር ሲካሄድ መቆየቱ ይታወሳል::

    በምርጫ ሂደቱም ከ250 በላይ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት የዩቨርሲቲዉ ሴኔት እና የሥራ አመራር ቦርድ መጋቢት 7 ቀን 2011 ዓ.ም. የቃለ-መጠይቅ ፓናል በማካሄድ ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንትነት የተወዳደሩና ማጣሪያዎችን አልፈው የደረሱ 9 ዕጩዎችን በመገምገም 5 ዕጩዎችን ለዩኒቨሲቲዉ የሥራ አመራር ቦርድ አስተላልፏል።

    የዉድድሩ ሂደት የተመራዉ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣዉ መስፈርት ሲሆን፤ ሂደቱን ለመምራት አምስት ሰዎችን የያዘ ኮሚቴ ተቋቁሞ በየደረጃዉ ግምገማ ሲያካሄድ ቆይቷል። ኮሚቴዉ ከቦርድ አባላት፣ ከሴኔት አባላት፣ ከተማሪ፣ ከመምህራን እና ከአስተዳደር ሠራተኞች ተወካይ የተዉጣጣ ሲሆን የዉድድር ማስታወቂያ ከማዉጣት ጀምሮ ለዩኒቨርሲቲዉ የሥራ አመራር ቦርድ ጉባዔ የሂደቱን ዉጤት እስከ ማሳወቅ ድረስ በትጋት ሲሠራ ቆይቷል።

    በዚሁ መሠረት የዩኒቨርሲቲዉ የሥራ አመራር ቦርድ ሚያዚያ 02 ቀን 2011 ዓ.ም. ባካሔደው ልዩ ጉባዔ 3 ዕጩዎችን (ዶ/ር ጀማል አባፊጣ፣ ፕሮፌሰር አርጋዉ አምበሉ እና ዶ/ር ናቃቸዉ ባሹን) በዕጩነት ለሳይንስና ክፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አቅርቧል:: የሳይንስና ክፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርም ዶ/ር ጀማል አባፊጣን ከሚያዚያ 11 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ አዲሱ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነዉ እንዲያገለግሉ መርጧቸዋል።

    ዶ/ር ጀማል አባፊጣ የዩኒቨርሲቲዉ ነባር መምህር እና ተመራማሪ ሲሆኑ በተለያዩ ደረጃዎች በዩኒቨርሲቲውና ከዩኒቨርሲቲው ውጭ በሃላፊነት ያገለገሉና በአሁኑም ወቅት የማኅበረሰብ አገልግሎት ቢሮ ዳይሬክተር ሆነዉ እያገለገሉ ይገኛሉ። ዶ/ር ጀማል አባፊጣ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በስታቲስቲክስ (BSc in Statistics)፣ የሁለተኛ ዲግሪያቸውንም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ (MA in Economics)፣ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ደግሞ በደቡብ ኮርያ ቻንችኦን ከተማ ከሚገኘው ካንግዎን ናሽናል ዩኒቨርሲቲ (Kangwon National University; Chuncheon, South Korea) በግብርና ግብዓቶች ምጣኔ ሀብት (Agricultural Resources Economics) አግኝተዋል።

    ስለ ዶ/ር ጀማል አባፊጣ የትምህርት ዝግጅትና የሥራ ልምድ ይህን ማስፈንጠርያ በመጫን ሙሉ መረጃ ማግኘት ይችላሉ።

    ምንጭ፦ ጅማ ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ጀማል አባፊጣ


    Semonegna
    Keymaster

    የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኪነ-ሕንፃ (አርክቴክቸር) ትምህርት ክፍል ዘንድሮ ተማሪዎች ሲያስመርቅ ሦስተኛው ሲሆን፥ 22 ወንዶች እና 7 ሴቶች በድምሩ 29 ተማሪዎች ለምረቃ በቅተዋል።

    ባህር ዳር (ሰሞነኛ)– ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የመሬት አስተዳደር ኢንስቲትዩት ስር የሚገኘው የኪነ-ሕንፃ (አርክቴክቸር) ትምህርት ክፍል ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ለሶስተኛ ጊዜ አስመረቀ።

    የዩኒቨርሲቲው መሬት አስተዳደር ዳይሬክተር ዶ/ር በላቸው ይርሳው ዓለሙ ለተመራቂ ተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት ተመራቂዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያገኙትን የቀለም እና የተግባር ትምህርት ወደ ተግባር የሚተረጉሙበት እና ከራሳችው አልፎ ህብረተሰባቸውን የሚያገለግሉበት ጥሩ አጋጣሚ በመሆኑ በከፍተኛ ኃላፊነት ስሜት እንዲሠሩ ይጠበቃል ብለዋል። የኪነ-ሕንፃ ትምህርት ትዕግስት እና ፈጠራ የሚጠይቅ በመሆኑ ተመራቂ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያሳደጉትን የፈጠራ ክህሎት የበለጠ አጎልብተው እራሳቸውን ጠቅመው ማኅበረሰቡን እንዲያገለግሉበት አሳስበዋል።

    ዶ/ር በላቸው አክለውም የኪነ-ሕንፃን ሙያ የሚጠይቅ ሥራ የሚሠሩ የፌዴራል፣ የክልል የግልም ሆነ የመንግስት መሥሪያ ቤቶች ከፍተኛ ሃብት እና ዕውቀት ፈሶባቸው የሰለጠኑ ተመራቂዎችን በአግባቡ ሊጠቀሙባቸው ይገባል ብለዋል።

    ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዶክተሮችን አስመረቀ

    የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ እንደተናገሩት፥ የሚገነቡት ከተሞች ብሎም አገራት የሚመስሉት የኪነ-ሕንፃ ባለሙያዎችን በመሆኑ ለከተሞች ውበት፣ የኑሮ ምቹነት፣ ቀጣይነት፣ ወጭ ቆጣቢነት የራሳቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ፕሬዝዳንቱ ቀጥለውም አሁን ትልቅ የኪነ-ሕንፃ ጥበብ የሚታይባቸው የአገራችን ቅርሶች የመፈራረስ አደጋ የተጋረጠባቸው ጊዜ ሲሆን መታደግ የሚቻለውም በዕውቀት እና በጥበብ በመሆኑ ተመራቂዎች ያላቸውን ዕውቀት እና ጥበብ በተቋርቋሪነት መንፈስ በመጠቀም ከመፍረስ እንዲታደጓቸው አሳስበዋል።

    ዶ/ር ፍሬው ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት፥ ተመራቂ ተማሪዎች የኢትዮጵያን ቅርሶች፣ መልክዓ-ምድሮች፣ እንስሳት፣ እጽዋት እና ሌሎች የተፈጥሮ ሃብቶች ሌሎች የሌሏቸው መለዮወቻችንን የንድፋቸው ማስጌጫ መጠበቢያ ቅመም በማድረግ እንዲጠቀሙባቸው አሳስበው ዓለም ከደረሰበት እድገት አንጻርም ዘመኑን የዋጀ ንድፍ መሥራት እንደሚገባቸው ተናግረው፤ ከሁሉም በፊት ግን ህሊናቸውን እና ፈጣሪያቸውን ዳኛ አድርገው የሙያ ሥነ-ምግባር በተላበሰ መልኩ እንዲሠሩ በአጽንኦት መክረዋል። በመጨረሻም ተመራቂዎች በሙያቸው ስኬታማ በመሆን የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲን ብሎም የውድ አገራቸውን ስም የበለጠ በበጎ እንዲታወቁ የበኪላቸውን ያደርጉ ዘንድ አደራ ብለዋል ።

    በምረቃ በርሃግብሩ የተገኙት አርክቴክት አበበ ይመኑ የረዥም ጊዜ የህይወት ተሞክሯቸውን እና የሥራ ልምዳቸውን ለተመራቂዎች ያቀረቡ ሲሆን፥ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በትምህርት ክፍል ደረጃ የሚሠሩት የተማሪዎች ፕሮጀክቶች ደረጃቸው ከፍ እንዲል መሠራት እንዳለበት ጠቁመው፥ በተጨማሪም በሙያው ትልቅ ስም ያላቸው አርክቴክቶች ያላቸውን የሥራ ልምድ፣ የፈጠራ ችሎታቸውንና ክህሎት ማካፈል የሚችሉበት መርሃግብር ቢዘጋጅ ጥሩ እንደሆነ ተናግረዋል። አቶ አበበ ይመኑ በመጨረሻም የኪነ-ሕንፃ ትምህርት በባህሪው የተለየ ክህሎት እና የተለየ ከባቢያዊ ሁኔታ የሚፈልግ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል።

    በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ከፍተኛ ውጤት ላመጡ እና ከ1ኛ-5ኛ ለወጡ ተማሪዎች ሽልማት ተስጥቷል። ከሴቶች ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበችው ተማሪ ቃልኪዳን ጥበቡ እንዲሁ ሽልማት የወሰደች ሲሆን ተማሪ በረከት ምትኩ 3.76 በማምጣት የከፍተኛ ማዕረግ የወርቅ ተሸላሚ ሆኗል።

    የዘንድሮው ምርቃት በትምህርት ክፍሉ ሦስተኛው ሲሆን 22 ወንዶች እና 7 ሴቶች በድምሩ 29 ተማሪዎች ለምረቃ በቅተዋል። በዕለቱ በተማሪዎቹ የተሠሩ የኪነ-ሕንፃ ንድፎች አውደ ርዕይ በመርሃ ግብሩ ለተገኙ ተሳታፊዎች እና ተመራቂ ቤተሰቦች ተጎብኝተዋል።

    ምንጭ፦ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኪነ-ሕንፃ ትምህርት ክፍል


    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት በቅርቡ ዋና ካምፓሱን በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፍቼ ከተማ በምድረግ ከተመሠረተው ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ጋር አብሮ ለመሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መለሰ ማርዮ እና የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገናናው ጎንፌ ጥር 8 ቀን 2011 ዓ.ም. በኢንስቲትዩቱ አዳራሽ እውቀትን ለማሸጋገር፣ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በጋራ ለማከናወን የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል።

    የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መለሰ ማርዮ በስምምነት ፊርማው ላይ ባደረጉት ንግግር እንዳስታወቁት የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና የምርምር ተቋማት ጋር አብሮ ሊያሠራው የሚችል ስምምነቶችን በመፈራረም የተለያዩ ተግባራትን ለማከናወን መቻሉን ገልጸዋል። ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በዱረም ስንዴ ላይ በተሠራው ሥራ ከፍተኛ ምርት የሚሰጥና ድርቅን መቋቋም የሚችል ውጤት መገኝቱን፤ ከጎንደር ዩኒቨረሲቲ ጋር በመተባበር በደን ልማት ላይ እየተሠራ መሆኑን እና ከዲላ ዩኒቨረሲቲ ጋርም በመተባበር ለምርምርና ለቱሪስት መስህብ የሚውል የቦታኒክ ጋርደን ግንባታ ሥራ ከተከናወኑ ተግባራት መካከል የሚጠቀሱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

    VIDEO: Ethiopia: After mandatory preparations, Selale University accepts incoming students

    የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገናናው ጎንፌ በበኩላቸው ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በቅርብ ጊዜ ሥራ የጀመረ፣ እየሰፋ የሚሂድና ለግብርና እና የአካባቢ ጥበቃ ልዩ ትኩረት የሚሰጥ ነው። የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ካለው መልካአ ምድራዊ አቀማመጡ ጋር በተያያዘም በእንስሳት ዝርያ አጠባበቅ በተለይም የተለያዩ ዝርያዎችን በማዳቀል ለአዲስ አበባ ከተማ 50 በመቶ የሆነውን የወተት ምርት የሚያቀርበው የሰላሌ አርሶ አደርን ተጠቃሚ ለማድረግ ከኢንስቲትዩቱ ጋር አብረው ለመሥራት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

    ዶ/ር ገናናው አክለውም ስምምነቱ የወረቀት ላይ ስምምነት ብቻ እንዳይሆን ለማድረግና የብዝሀ ሕይወት ጥበቃ ሥራዎችን ለሕብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ከመማር ማስተማር ሥራው ጎን ለጎን የአካባቢውን ማሕበረሰብ ተጠቃሚ የማድረግ ሥራ ለማከናወን ዩኒቨርሲቲው መዘጋጀቱን ገለጸዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦  

    የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት


    Semonegna
    Keymaster

    የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ያዘጋጁት የዘንድሮው ውድድር ለ2ኛ ጊዜ የተካሄደ ሲሆን፥ በባለፈው ዓመት የተመረጠችው ወ/ሪት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በአማራ ክልል በተካሄደው የቁንጅና ውድድር ላይ ተሳትፋ 3ኛ ደረጃ መውጣቷም ተገልጿል።

    ደብረ ብርሃን (ሰሞነኛ)– በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ‹‹ቱሪዝም ለአካባቢ እንክብካቤና ለማኅበረሰብ አቅም መጎልበት›› በሚል መሪ ቃል ሲከበር የቆየው የቱሪዝም ሳምንት ጥር 24/2011 ዓ/ም የቁንጅና ውድድር በማካሄድ ተጠናቀቀ።

    በውድድሩም ወ/ሪት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ያብፀጋ አይነኩሉ ከሁለተኛ ዓመት የሎጅስቲክና ሰፕላይ ቼን ማኔጅመንት (Logistics and Supply Chain Management) ትምህርት ክፍል ተመርጣለች። በሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ኤልሳቤጥ ደስታ የ3ኛ ዓመት የባዮቴክኖሎጂ (Biotechnology) እና በሦስተኛነት ደረጃ ተማሪ ትንሳኤ ፀጋዬ አንደኛ ዓመት የሳይኮሎጂ (Psychology) ትምህርት ክፍል እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።

    VIDEO: The Yellow Movement AAU: Speaking up for women and girls – empowering women (Ethiopia)

    የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዘዳንት ተወካይ ዶ/ር ጌትነት አሸናፊ በፕሮግራሙ መዝጊያ ላይ ተገኝተው እንደገለጹት የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ከሳምንት በፊት ጀምሮ በዩኒቨርስቲው ግቢና ውጪ ያለውን አካባቢ በማጽዳት ለሌሎች ምሳሌ የሚሆኑ ተግባራት በማከናወን የቆዩ መሆናቸውን በመግለፅ ላደረጉት በጎ ተግባር ምስጋና አቅርበዋል።

    የቱሪዝም ማኔጅመንት የትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ አብርሃም ኪዳኔ እንደገለፁት የዘንድሮው ውድድር ለ2ኛ ጊዜ የተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው፥ በባለፈው ዓመት የተመረጠችው ወ/ሪት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በአማራ ክልል በተካሄደው የቁንጅና ውድድር ላይ ተሳትፋ 3ኛ ደረጃ በመውጣቷ በርካታ ሽልማቶችን ያገኘች መሆኗን ተናግረዋል።

    በመጨረሻም ለጓሳ ማኅበረሰብ ጥብቅ ስፍራ መታሰቢያነት ‹‹ቱሪዝም ለአካባቢ እንክብካቤና ለማህበረሰብ አቅም መጎልበት›› በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የቱሪዝም ሳምንት 8 /ስምንት/ ተወዳዳሪዎችን ያሳተፈው የቁንጅና ውድድር ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ የወጡትን አሸናፊዎችን በመምረጥና እውቅና በመስጠት በዓሉ ተጠናቋል።

    ምንጭ፦ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል


    Semonegna
    Keymaster

    ባለቤት አልባ ውሾችን ከማስወገዱ ተግባር ጎን ለጎን በከተማዋ ያሉ ውሾችን የቤት ለቤት ምዝገባ በማከናወን የባለቤትነት ማረጋገጫ በየወረዳው እየተሰጠ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገልጿል። በዚህም፣ ህብረተሰቡ ለሚመለከተው አካል እያሳወቀ ችግሩን በጋራ መቅረፍ እንደሚገባም ጥሪ ቀርቧል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 7ሺህ 8 መቶ ባለቤት አልባ ውሾችን ማስወገዱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።

    በከተማ አስተዳድሩ አስተዳደር የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ የከተማ ግብርና ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አሰግድ ኃ/ጊዮርጊስ ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) እንደተናገሩት በከተማዋ እየተበራከቱ የመጡ ባለቤት አልባ ውሾችን ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ለማስወገድ በጋራ እየሠራ ነው። ባለቤት አልባ ውሾቹ በህብረተሰቡ ላይ የሚደርሱትን የጤና ስጋት ችግር ለመቅረፍ እየሠራ መሆኑንም አስተባባሪው አቶ አሰግድ ገልፀዋል።

    በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ ከከተማው ውበትና መናፈሻ፣ የጽዳት አስተዳደር፣ ጤና ቢሮ እንዲሁም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እስካሁን 7ሺህ 8 መቶ ውሾችን ማስወገድ መቻሉንም ተመልክቷል። በየቦታው ተንጠባጥበው የሚገኙ ባለቤት የሌላቸው ውሾችን የማስወገዱ ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉንም አቶ አሰግድ ተናግረዋል።

    ቪዲዮ፦ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተለያዩ የቆሻሻ መጣያ የነበሩ ቦታዎችን በማጽዳትና አረንጓዴ በማድረግ፣ እንዲሁም የተለያዩ አትክልቶችን አልምቶ በመሸጥ ራሳቸውን የሚያስተዳድሩ ወጣቶች

    በተጨማም በከተማዋ ያሉ ውሾችን የቤት ለቤት ምዝገባ በማከናወን የባለቤትነት ማረጋገጫ በየወረዳው እየተሰጠ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገልጿል። በዚህም፣ ህብረተሰቡ ለሚመለከተው አካል እያሳወቀ ችግሩን በጋራ መቅረፍ እንደሚገባም ጥሪ ቀርቧል።

    በአንፃሩ ባለቤት አልባ ውሾችን በማስወገዱ ሂደት ከአንድ ወር በላይ ጊዜ የመድሃኒት አቅርቦት እጥረት እንደገጠመውም አስተዳደሩ ገልጿል። በዚህም፣ በፌዴራል ደረጃ የመድሃኒት ፈንድ መድሃኒቱን እስኪያቀርብ እየተጠበቀ መሆኑንና አቅርቦቱ እንደተሟላ ባለቤት አልባ ውጮችን የማስውገዱ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል ሲል ዘግቧል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕረሽ ድርጅት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ባለቤት አልባ ውሾች - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር


    Semonegna
    Keymaster

    የከተማዋን የቱሪዝም ዕድገት ከፍ ለማድረግ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ምኒልክ ሃውልቶችን የከተማ አስተዳደሩ ኅብረተሰቡን በማሳተፍ ያስገነባል። ስለሆነም የሁለቱ ታላላቅ መሪዎች ሃውልት በከተማዋ እንዲቆም እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ከ6 መቶ ዓመታት በላይ ባስቆጠረችው የድሮዋ ደብረ ኤባ የዛሬዋ ደብረ ብርሃን ከተማ ለዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሃውልት ሊቆምላቸው እንቅስቃሴ መጀመሩን ከተማ አስተዳደሩ አስታውቋል።

    የከተማዋ ምክትል ከንቲባ እና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ብርሃን ገብረሕይወት ጥር 9 ቀን 2011 ዓ.ም. አዲስ አበባ ላይ በሰጡት መግለጫ ደብረ ብርሃን ከተማን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የከተማ አስተዳደሩ እየሠራ ነው፤ ከተማዋን የኮንፈረንስ ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግም ከተማ አስተዳደሩ ባዛሮችን በተለያዩ ጊዚያት እንደሚያካሂድ ተገልጿል።

    የከተማዋን የቱሪዝም ዕድገት ከፍ ለማድረግ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ምኒልክ ሃውልቶችን የከተማ አስተዳደሩ ኅብረተሰቡን በማሳተፍ ያስገነባል። ስለሆነም የሁለቱ ታላላቅ መሪዎች ሃውልት በከተማዋ እንዲቆም እንቅስቃሴ እየተደረገ ነውም ተብሏል።

    ደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ በከተማዋ ለሚኖሩ ዜጎች የተለያዩ የሥራ ዕድሎችን ፈጥሯል

    ከተማ አስተዳደሩ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እየሠራ እንደሆነም አስታውቋል። ደብረ ብርሃን ከተማ በዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ መመሥረቷ ይታወቃል።

    አጼ ዘርአ ያዕቆብ

    አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስትክብረ እግዚ እ.ኤ.አ. በ1399 ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮው ፈታጃር ክፍለ ሀገር ተወለዱ። የነገሡበትም ዘመን እ.ኤ.አ. ከ 1434 እስከ 1468 (እስከሞቱበት ጊዜ) ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው።

    ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ

    ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ከአባታችው ከሸዋው ንጉሥ ኃይለ መለኮት ሣህለ ሥላሴና ከእናታቸው ወይዘሮ እጅጋየሁ ለማ አድያም እ.ኤ.አ. ነሐሴ 17 ቀን 1844 ደብረ ብርሃን አካባቢ አንጎለላ ከሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ በአንጎለላ መቅደላ ኪዳነ ምኅረት ቤተ ክርስቲያን ክርስትና ተነሱ። የነገሡበትም ዘመን እ.ኤ.አ. ከ 1889 እስከ 1913 (እስከሞቱበት ጊዜ) ነበር። ያረፉትም ተዓካ ነገሥት ለማርያም ወደብረ መንክራት ስዕል ቤት ኪዳነ ምኅረት ገዳም (አዲስ አበባ) ነው።

    ምንጭ፦ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሃውልት


    Semonegna
    Keymaster

    ባህር ዳር (ኢዜአ)–ከቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በመውጣት በባህር ዳር ከተማ የተጠለሉ የአማራ ክልል ተወላጅ ተማሪዎች ለቀረቡላቸው አማራጮች ከመስማማት ይልቅ የጸጥታ ችግር እየፈጠሩ በመሆኑ ከተማውን ለቀው እንዲወጡ የከተማው ከንቲባ አሳሰቡ።

    የከተማዋ ከንቲባ አቶ ሙሉቀን አየሁ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ከቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የመጡ ተማሪዎች የከተማው ህዝብ ባደረገላቸው ድጋፍና እንክብካቤ ከታህሳስ 19 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ በከተማው መቆየታቸውን አስታውሰዋል።

    የከተማው ህዝብና ወጣቶች የመኝታ ፍራሽ፣ የምግብ አቅርቦትና አልባሳትን በመደገፍ ያልተቆጠበ ወገናዊ ድጋፍ ቢያደርግም ከጥር 6 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ጀምሮ ከተጠለሉበት በመውጣት የከተማውን ጸጥታ እያወኩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

    “በዛሬው ዕለትም ተመሳሳይ ሁከት በመፍጠር የቱሪዝም ከተማ የሆነችውንና በሰላማዊነቷ የምትታወቀውን የባህር ዳር ከተማ ሲረብሹና ጉዳት ሲያደርሱ ውለዋል” በማለት ጥር 7 ቀን ተናግረዋል።

    “ድንጋይ በመወርወር ጉዳት ማድረስ፣ የመኖሪያ ቤቶች፣ ሆቴሎችና ሌሎች የአገልግሎት ሰጭ ተቋማት እንዲዘጉና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴው እንዲስተጓጎልም አድርገዋል” ብለዋል።

    ችግሩ በመባባሱ የከተማው ሰላም እየታወከ በነዋሪዎችና በንብረት ላይ የሚደርሰው ጉዳት መቀጠል ስለሌለበት ከተማውን ለቀው ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረው የከተማው ወጣቶች ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር በመተባበር ላደረጉት የማረጋጋት ጥረትም ምስጋና አቅርበዋል።

    የከተማ አስተዳደሩ የሰላም ግንባታና የህዝብ ደህንነት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘውዱ ዘለቀ በበኩላቸው “ተማሪዎቹ ከከተማው አልፈው በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፔዳ፣ ፖሊና ሰላም ካምፓሶች በመግባት ረብሻ እንዲፈጠር አድርገዋል” ብለዋል።

    ከባህር ዳር ከተማ የሚወጣም ሆነ የሚገባ ስምንት በመኪና የተጫነ እህል በማራገፍ፣ ተሽከርካሪዎችን በመስበር፣ ቤቶችን በመደብደብ ከተማረ ሰው የማይጠበቅ ተግባር መፈጸማቸውንም አመልክተዋል።

    ተማሪዎቹ ጩቤ፣ የጭስ ቦንብ፣ የአደጋ መከላከያ ሄልሜትና ዱላ ጭምር በመያዝ አደጋ መፍጠራቸውን ጠቅሰው፤ የፀጥታ መዋቅሩ ከከተማው ሰላም ፈላጊ ወጣቶች ጋር በመተባበር ያለምንም ሰብዓዊ ጉዳት እንዲረጋጋ ከፍተኛ ጥረት ማድረጉን አስረድተዋል።

    “አሁን ላይ ለከተማዋ የሰላም መደፍረስ ምክንያት በመሆናቸው ከህዝቡ ጋር በመሆን የክልሉ መንግስት በሚሰጠው አቅጣጫ ለመሸኘት ሥራ እየተሠራ ነው” ብለዋል።

    ተማሪዎችን ለማግባባትና መፍትሄ ለመስጠት በከፍተኛ አመራሩ ተደጋጋሚ ውይይት ቢደረግም የቀረበላቸውን አማራጭ ባለመቀበል መግባባት ላይ መድረስ አለመቻሉን የገለፁት ደግሞ የክልሉ የሰላም ግንባታና የህዝብ ደህንነት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ገደቤ ኃይሉ ናቸው።

    ተማሪዎቹ ወደ ዩኒቨርሲቲው ተመልሰው መደበኛ ትምህርታቸውን እንዲጀምሩ አለበለዚያ ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲሄዱ ተደጋጋሚ ውይይት ቢደረግም ባለመስማማት ጥር 7 ቀን በኃይል በመጠቀም በአካባቢው የከፋ ችግር ለመፍጠር መሞከራቸውን ጠቁመዋል።

    በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ቀደም ሲል በተፈጠረ ግጭት የተፈናቀሉ የአማራ ክልል ተወላጅ ተማሪዎች ችግራቸው እስኪፈታ በጊዜያዊነት በባህር ዳር ከተማ መጠለላቸው ይታወሳል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች


    Semonegna
    Keymaster

    ጅማ ዩኒቨርሲቲ ባስገነባው የህክምና ማዕከል ምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ ለዓመታት ያስተማራቸውን 331 የህክምና ዕጩ ምሩቃን እና በተለያዩ መስኮች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 2ሺህ የድህረ ምረቃ መርሀ ግብር ተማሪዎችን ያስመርቃል።

    ጅማ (ሰሞነኛ)– ጅማ ዩኒቨርሲቲ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የፌድራልና የክልል መንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የህክምና ማዕከሉን ኅዳር 29 ቀን 2011 ዓም እንደሚያስመርቅ ተዘግቧል።

    የህክምና ማዕከሉ 800 (ስምንት መቶ) አልጋዎች ያሉት ሲሆን፥ በደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍል ከ20 ሚሊየን በላይ ሰዎች የህክምና አገልግፍሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው ተብሏል። ማዕከሉ እንደ ደቡብ ሱዳን ላሉ ጎረቤት ሀገራትም አገልግሎት ለመስጠት ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ መሆኑን ተነግሯል።

    ዩንቨርሲቲው ያስገነባው ይህ የህክምና ማዕከል በህክምና እና ጤናው ዘርፍ የምርምር፣ የማስተማሪያ፣ እንዲሁም የማኅበረሰብ አገልግሎቶችን ለመስጠት የሚያስችል መሆኑም ነው የተገለጸው። በዚህም ጅማ ዩኒቨርሲቲ በሀገሪቱ ከሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ሲነጻጸር ልቆ የሚታይበትን የማኅበረሰብ ተኮር (community-based) ትምህርትና ምርምር ይበልጥ ያገለብትለታል ተብሎ ይታመናል።

    Ethio-American Doctors Group (EADG): Building a regional healthcare system & medical tourism

    ዩንቨርሲቲው በህክምና ማዕከሉ የምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ ለዓመታት ያስተማራቸውን 331 የህክምና ዕጩ ምሩቃን እና በተለያዩ መስኮች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 2ሺህ የድህረ ምረቃ መርሀ ግብር ተማሪዎችን እንደሚያስመርቅም ታውቋል።

    በተመሳሳይ መልኩ ዩንቨርሲቲው ያስገነባው 40 ሺህ ያህል ተመልካቾችን ማስተናገድ የሚችለው ስታዲየም፣ ሲቭክ አዳራሽ፣ መንገዶችና ሌሎች የመሠረተ ልማት ሥራዎች ይመረቃሉ ተብሏል። የሲቪክ አደራሹ በርካታ ተሰብሳቢዎችን በአንዴ የሚያስተናግድና የተለያዩ ኮንፈረንሶችን በተመሳሳይ ጊዜ ለማካሄድ የሚያስችሉ የተለያዩ ክፍሎች እንዳሉትም ተነግሯል። ከዚህ ጋር ተያይዞ እንደተዘገበው ይህ የሲቭክ አዳራሽ ከተማዋን የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ ስለመሆኑም ነው የተገለጸው።

    ምንጭ፦ ኢቢሲ / ኤፍ.ቢ.ሲ. / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ጅማ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ማዕከል


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ ዓለም ከተማ የሞቱት ሁለቱ ተመራማሪዎች ወሰን ታፈረ እና ማንደፍሮ አብዲ የሚባሉ ሲሆን፥ ከባድ የመቁሰል አደጋ የደረሰበት የሜጫ ወረዳ ጤና መኮንን (የላቦራቶሪ ባለሙያ) የሆነው ኃይለየሱስ ሙሉ ይባላል።

    አዲስ ዓለም፣ አማራ ክልል – በምዕራብ ጎጃም ዞን ጎንጂ ቆለላ ወረዳ ለምርምር ወደ አዲስ ዓለም ከተማ የሄዱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሶስተኛ (ዶክትሬት) ዲግሪ ተማሪዎች እና የሜጫ ወረዳ ጤና መኮንን በከተማው የሚኖሩ ግለሰቦች ባደረሱባቸው ጥቃት ሁለቱ ህይወታቸው ሲያልፍ፣ አንዱ ደግሞ የመቁሰል አደጋ ደርሶበታል። ሁለቱ የሞቱት ተመራማሪዎች ወሰን ታፈረ እና ማንደፍሮ አብዲ የሚባሉ ሲሆን፥ ከባድ የመቁሰል አደጋ የደረሰበት የሜጫ ወረዳ ጤና መኮንን (የላቦራቶሪ ባለሙያ) የሆነው ኃይለየሱስ ሙሉ ይባላል።

    የዶክትሬት ተማሪዎቹ አዲስ ዓለም ከተማ ውስጥ በሚገኝ አንድ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለምርምር የሚሆን የሽንትና የዓይነ ምድር ናሙና እየሰበሰቡ ባሉበት ወቅት ከዕለቱ ቀደም ብሎ በተለይም በማኅበራዊ ሚዲያዎች “ሦስት ተማሪዎች ሞቱ” በሚል በተነዛው ወሬ ተቆጥተው በመጡ የአካባቢው ወጣቶች በደረሰባቸው ከፍተኛ ጥቃት ሕይወታቸው ማለፉን የምዕራብ ጎጃም ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ አንማው ዳኛቸው ለአሜሪካ ድምፅ የአማርኛ ዝግጅት ክፍል ተናግረዋል።

    ከዚሁ ጋር በተያያዘ ቢቢሲ አማርኛ የጎንጂ ቆለላ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ደመቀ መላኩን ጠቅሶ እንደዘገበው “በተሳሳተ መልኩ ልጆቻችን የጤና ክትባት እየተሰጣቸው ነው፤ እየተመረዙብን ነው፤ ሊገደሉብን ነው” በሚል የተቆጡ ቁጥራቸው በርከት ያሉ የአካባቢው ግለሰቦች የዶክትሬት ተማሪዎቹ (ተመራማሪዎቹን) ወደነብሩበት የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ሄደዋል። የትምህርት ቤቱ የጥበቃ ሠራተኞች ሁኔታው ከአቅማቸው በለይ ሲሆን በአካባቢው በነበሩ ጥቂት የጽጥታ አስከባሪ አካላት (ፖሊሶች) ታግዘው ተመራማሪዎቹን ወደ ፖሊስ ጣቢያ እየወሰዷቸው ሳለ፥ በከተማው መናኸሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ጥቃቱ እንደደረሰባቸው ቢቢሲ አማርኛ ጨምሮ ዘግቧል።

    አዲስ ዓለም

    ግለሰቦቹ ያደረሱት ጥቃት በተማራማሪዎቹ ላይ ብቻ ሳይገታ ሁኔታው በፈጠረው ግርግር ለቤተ ክርስቲያን ህንፃ ግንባታ ግልጋሎት የሚውል ሲሚንቶ በራሳቸው መኪና ጭነው ወደ አካባቢው ተጉዘው የነበሩ ጥንዶች ንብረትም መቃጠሉን የአሜሪካ ድምፅ አቶ አንማው ዳኛቸውን ጠቅሶ ዘግቧል። አቶ አንማው ለአሜሪካ ድምፅ አክለው በሰጡት ማብራሪያ በዚህ ድርጊት ተሳትፈዋል በሚል የተጠረጠሩ 30 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን፣ ብሎም በተፈፀመው ድርጊት የአካባቢው ማኅበረሰብም ሆነ መንግሥት ማዘኑን እና በድርጊቱ ተሳትፈዋል የተባሉትን እየፈለጉ በቁጥጥር ስር የማዋሉ ሥራ መቀጠሉን ጠቁመዋል።

    ከቢቢሲ አማርኛ ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት የጎንጂ ቆለላ ወረዳ የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ አንተነህ በላይ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም በክልሉ ዋና ከተማ ባህር ዳር ውስጥ ለህፃናት ክትባት ሲሰጡ ሞቱ በሚል በተናፈሰ ወሬ ምክንያት መኪና መሰባበር፣ እንዲሁም በአንዳንድ ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት (መቁሰል) መድረሱን አስታውሰው አካባቢው ለባህር ዳር ከተማ ቅርብ በመሆኑ ይሄው መረጃ በመናፈሱ ጥቃቱ ሊፈፀም እንደቻለ አስረድተዋል። አቶ አንተነህ አክለው እንደተናገሩ ጥቃቱን ያደረሱት የ አካባቢ ተወላጆች መሆናቸውና አገር ሊጠቅሙ ምሁራን በራሳቸው ወገኖች በመገደላቸው የ አካባቢው ማኅበረሰብ መፀፀቱን፣ በድርጊቱ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን አጋልጦ መስጠት የጀመረውም ራሱ ህብረተሰቡ እንደሆነ ተናግረዋል።

    የአሜሪካ ድምፅ የአማርኛ ዝግጅት ክፍል ጋዜጠኛ ጽዮን ግርማ ከምዕራብ ጎጃም ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ አንማው ዳኛቸው ጋር ያደረገችውን ቃለ ምልልስ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

    Semonegna
    Keymaster

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ድረስ በ14 የትምህርት ክፍሎችን በመክፈት ተማሪዎችን እያስተማረ መሆኑንና የኒቨርሲቲው የትምህርት ክፍሎቹን ወደ 41 ለማሳደግ ዕቅድ ይዞ እየሠራ መሆኑንም የኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ተናግረዋል።

    ጂንካ፣ ደቡብ ኦሞ ዞን (ዋልታ) – ጂንካ ዩኒቨርሲቲ በ2011 ዓ.ም የትምህርት ዘመን 1ሺ 500 አዳዲስ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።

    የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ፕሮፌሰር ገብሬ ይንቲሶ ለዋልታ እንደገለጹት በዘንድሮ የበጀት ዓመት እና የትምህርት ዘመን የተማሪዎችን ቅበላ የተሳካ ለማድረግ በሁለት ዘርፍ የተከፈሉ ዝግጅቶች እየተካሄዱ ይገኛሉ።

    የኒቨርሲቲው የዘንድሮ ዓመትን የመማርና ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር የመምህራን ዝግጅትን ጨምሮ የተማሪዎች የአገልግሎት መስጪያ ተቋማት የሆኑት ቤተ መጽሐፍትና የመመዝገቢያ ሥፍራዎች በቴክኖሎጂ የታገዙ እንዲሆኑ የማስቻል ሥራዎች ተከናውነዋል ብለዋል ፕሬዚደንቱ።

    በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች አገልግሎት መስጪያ ህንጻዎች ግንባታ መዘግየታቸውን የገለጹት ፕሮፌሰር ገብሬ አዳዲስ ተማሪዎችን በጊዚያዊ የመጠሊያ ህንጻዎች እንዲገቡ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የዘንድሮ ዓመት የተማሪዎች የመግቢያ ቀንም እስካሁን አለመቆረጡን ፕሬዚደንቱ አያይዘው ገልጸዋል።

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ድረስ በ14 የትምህርት ክፍሎችን በመክፈት ተማሪዎችን እያስተማረ መሆኑንና የኒቨርሲቲው የትምህርት ክፍሎቹን ወደ 41 ለማሳደግ ዕቅድ ይዞ እየሠራ መሆኑንም ፕሬዚደንቱ አብራርተዋል።

    አዳዲስ የሚከፈቱት የትምህርት ዘርፎችም በደቡብ ኦሞ ዞን የሚታዩ የሙያ ክፍተቶችን ለመሙላት በሚያስችል መልኩ የሚከፈቱ መሆኑም ተገልጿል።

    የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ባለፈው ዓመት 1ሺህ 100 ያህል ተማሪዎችን የተቀበለ ሲሆን በዘንድሮ ዓመት 1ሺ500 አዳዲስ ተማሪዎችን በመቀበል በአጠቃላይ ተማሪዎችን 2ሺህ 600 ለማድረስ እየሠራ ይገኛል።

    በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል (ደብብሕክ)፣ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና ከተማ በሆነችው ጂንካ የሚገኘው ጂንካ ዩኒቨርሲቲ በ2010 ዓ.ም. በትምህርት ሚኒስቴር ስር ከተከፈቱት 11 አዳዲስ የሕዝብ ዩኒቨርሲቲዎች (public universities) አንዱ ነው።

    ምንጭ፦ ዋልታ

    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ

     

    Semonegna
    Keymaster

    ዩኒቨርሲቲው ለሠራተኞቹ ያስተላለፋቸው መኖርያ ቤቶች ስቱዲዮ፣ ባለ አንድ መኝታ፣ ባለ ሁለት መኝታ እና ባለ ሦስት መኝታ ሲሆኑ ሠራተኞቹ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በሠራተኝነት እስካሉ ድረስ ቤቶቹን በነጻ ይገለገሉባቸዋል።

    ነቀምቴ (ኢዜአ) – ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ከ37 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባቸውን መኖርያ ቤቶች ለሠራተኞቹ አስረከበ።

    የዩኒቨርሲቲው የመሠረተ ልማትና የሕንፃ ግንባታ ዳይሬክተር ዶክተር ደረጄ አደባ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው የመኖርያ ቤት ለሌላቸው ሠራተኞቹ የቤት ባለቤት ለማድረግ ያስገነባቸውን 134 መኖሪያ ቤቶች ትናንት አስረክቧል። ለመኖሪያ ቤቶቹ ከ37 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጉንም ገልጸዋል።

    ከዚህ በተጨማሪ በ1999 ዓ.ም በከተማ አስተዳደሩ የተጀመሩና በገንዘብ እጥረት ምክንያት ግንባታቸው የተቋረጡ 10 ሕንፃዎችን በመግዛት ሠራተኞቹን ተጠቃሚ ለማድረግ እየሠራ መሆኑን፥ ሕንጻዎቹ ሲጠናቀቁ 150 የሚሆኑ የተቋሙን ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለማድረግ የሚያስችሉ መሆናቸውንም ዶክተር ደረጄ አክለው ገልጸዋል።

    ዶክተር ደረጄ እንዳሉት መኖርያ ቤቶቹ ስቱዲዮ፣ ባለ አንድ መኝታ፣ ባለ ሁለት መኝታ እና ባለ ሦስት መኝታ ሲሆኑ ሠራተኞቹ በተቋሙ እስካሉ ድረስ ቤቶቹን በነጻ ይገለገሉባቸዋል።

    ከዩኒቨርሲቲው ሠራተኞቹ መካከል መምህር ተስፋዬ ፍቃዱ በሰጡት አስተያየት ተቋሙ በግል የኪራይ ቤት ሲንከራተቱ ይገጥማቸው ከነበረው ችግር እንደተፈታላቸው ተናግረዋል። በግል ተከራይቶ መኖር ብዙ አስቸጋሪ ሁኔታዎች እንዳሉት ገልጸው በአከራዩና በተከራይ መካከል ቅሬታ በተፈጠረ ቁጥር ይደርስባቸው በነበረው መጉላላት ይማረሩ እንደነበር ገልጸዋል።

    መምህር እሱባለሁ ዳባ በበኩላቸው የግል ቤት በተከራዩበት ወቅት ከውሃና መብራት ክፍያ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ጭቅጭቅና ግጭት ውስጥ ይገቡ እንደነበር አስታውሰዋል።

    በተመሳሳይ፦ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ እና ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛና በሶስተኛ ዲግሪዎች በርካታ መርሀ ግብሮችን ከፈቱ

    በአሁኑ ወቅት በዩኒቨርሲቲው በኩል የመኖሪያ ቤት ችግራቸው መፈታቱ የትምህርትና የምርምር ሥራቸውን ተረጋግተው ለማከናወን እንደሚያስችላቸው ጠቁመው በተቋሙ በኩል ለተደረገላቸው የመኖርያ ቤት ስጦታ መስጋናቸውን አቅርበዋል።

    መኖርያ ቤት ማግኘታቸው ከዚህ ቀደም ለግለሰብ ይከፍሉት የነበረውን የቤት ኪራይ ወጪ ከመቀነሱ ባለፈ ከሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር በማኅበራዊ ጉዳዮች እንዲተሳሰሩ የሚያደርግ መሆኑን የገለጹት ደግሞ መምህር ኤልያስ ቱጁባ ናቸው። መምህሩ እንዳሉት ሠራተኞች አንድ አካባቢ መሆናቸው ለትራንስፖርት አገልግሎትና ለኢንቴርኔት አገልግሎት ምቹ ሁነታ ከመፍጠር አኳያ ጠቀሜታው የጎላ ነው።

    ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ከዚህን ቀደም ከ19 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመኖርያ ቤት ሕንፃ በማስገንባት ከ60 በላይ ለሚሆኑ ሠራተኞቹ ማሰረከቡ የተቋሙን መረጃ ያሳያል።

    በየካቲት ወር 1999 ዓ.ም የተቋቋመው ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በአሁኑ ወቅት 82 በመጀመሪያ (bachelors)፣ በሁለተኛ (masters) እና በዶክትሬት ዲግሪዎች ተማሪዎችን እንደሚያስተምር የዩኒቨርሲቲው ድረ ገጽ ያስረዳል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    ወለጋ ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ፣ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በዶክትሬት ዲግሪ አዳዲስ የትምህርት መርሀ ግብሮችን ከፍተው ተማሪዎችን ይቀበላሉ።

    ደብረ ብርሃን/ባህር ዳር – ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በዘንድሮ (2011 ዓ.ም) የትምህርት ዘመን በመጀመሪያ ዲግሪ (bachelor degree) አራት በሁለተኛ ዲግሪ (master degree) አስራ ሁለት መርሃ ግብሮችን እንደሚከፍት አስታወቀ።

    የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ፕሮግራም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶክተር ጌትነት አሸናፊ ለኮሙኒኬሽን ጉዳዮች እንደገለጹት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በዘንድሮው የትምህርት ዘመን አስራ ስድስት አዳዲስ የትምህርት መርሀ ግብሮችን ይከፍታል።

    ዶክተር ጌትነት አሸናፊ እንዳሉት የትምህርት ክፍሎቹ ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያና ሁለተኛ ድግሪ ዲግሪ የሚሰጣቸውን የትምህርት መርሀ ግብሮች የመጀመሪያ ድግሪ ከ49 ወደ 53 እንዲሁም 34 የነበረውን የሁለተኛ ዲግሪ የትምህርት መርሀ ግብር ወደ 46 ከፍ ያደርገዋል ብለዋል።

    ከተመሠረተ 11 ዓመት የሞላው ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በአሁኑ ሰዓት ከ12 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በተለያዩ መስኮች እያስተማረ ይገኛል።

    በተመሳሳይ ዜና ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2011 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በመጀመሪያ፣ በበሁለተኛ እና በዶክትሬት (doctorate) ዲግሪ በሚከፍታቸው 18 አዳዲስ የትምህርት መስኮች ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ። ዩኒቨርሲቲው በዚህ ዓመት ከ8 ሺህ 700 በላይ አዲስ ተማሪዎችን ለመቀበልም አስፈላጊው ዝግጅት ማድረጉም ተጠቁሟል።

    የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር እሰይ ከበደ ዛሬ ለኢዜአ እንዳስታወቁት ተቋሙ በአዲሱ የትምህርት ዘመን ከወቅቱ ጋር የሚሄዱ አዳዲስ የትምህርት መስኮችን በመክፈት አገራዊ እድገቱን በእውቀት ለማገዝ እየሠራ ነው።

    በተያዘው የትምህርት ዘመንም ሁለት የመጀመሪያ ዲግሪ፣ 12 የሁለተኛ ዲግሪና አራት የዶክትሬት ዲግሪ የትምህርት መስኮችን ከፍቶ 250 ተማሪዎችን ለመቀበል የሚያስችል ዝግጅት ማድረጉን ገልጸዋል።

    ዶክተር እሰይ እንዳሉት ህግ፣ መሬት አስተዳደር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ ጨርቃጨርቅ፣ ትምህርት፣ ፖለቲካል ሳይንስና የመሳሰሉት የትምህርት መስኮች አዲስ የሚከፈቱባቸው ናቸው። “የተሳካ የመማር ማስተማር ተግባር ለማካሄድም ቀደም ብሎ የሥርአተ ትምህርት ቀረጻ መደረጉንና የመምህራን ቅጥርም ሆነ ሌሎች አስፈላጊ ዝግጅቶች ተጠናቀዋል” ብለዋል።

    የኒቨርሲቲው በአፋን ኦሮሞ ትምህርትም በዚህ ዓመት አጋማሽ መደበኛ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር የሥርአተ ትምህርት ቀረጻ ሥራ ማካሄዱንና የመምህራን ቅጥር እየፈጸመ መሆኑን ዶክተር እሰይ አስታውቀዋል።

    ተቋሙ በህክምናው ዘርፍ የተሻለ እውቅት ያላቸው ባለሙያዎችን ለማፍራት በትኩረት እየሠራ መሆኑን ጠቁመው፣ “የተሻለ የማስተማርም ሆነ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት አዲስ የማስተማሪያ ሆስፒታል ገንብቶ የ170 መምህራንን በመቅጠር ላይ ነው” ብለዋል።

    ዩኒቨርሲቲው በመደባኛው የትምህርት መርሀግብር ብቻ ከመጀመሪያ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ከ8 ሺህ 700 በላይ አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ እንደሚያስተምርም ምክትል ፕሬዚዳንቱ አያይዘው ገልጸዋል።

    በተለይም እንደ ሀገርም ሆነ እንደ ዩኒቨርሲቲ እየወረደ የመጣውን የትምህርት ጥራት ለማስጠበቅ የተሻለ አቅም ያላቸውን መምህራን በመመደብ፣ ቤተ ሙከራዎችንና ቤተ መጻህፍትን በማደረጀት ጥራትን ለማምጣት እየሠራ መሆኑንም ገልፀዋል። ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ቆይታቸውን አጠናቀው ከመውጣታቸው በፊትም አጠቃላይ የጥራት መለኪያ ፈተና እንዲወስዱም እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል።

    ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በመደበኛውና መደበኛ ባልሆኑ የትምህርት መርሃ ግብሮች ዓመታዊ የተማሪ የቅበላ አቅሙ በአሁኑ ወቅት ከ50 ሺህ በላይ ደርሷል።

    ምንጭ፦ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ እና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ዶ/ር ጌትነት አሸናፊ (ፎቶ፦ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ)

    Semonegna
    Keymaster

    የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሠራ ነው

    ባሕር ዳር፦ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ የምርምር ሥራ ለመሥራት የሚሆን 54.8 ሄክታር መሬት ከመንግስት በስጦታ አግኝቶ ምርምር በማካሄድ ላይ ይገኛል። ለምርምር የሚሆነው ስፍራ በመርዓዊ ከተማ (ከባህር ዳር ከተማ በደቡባዊ አቅጣጫ 30 ኪሎ ሜትሮችን ርቃ የምትገኝ ከተማ) ዙሪያ በሚገኙ አራት ቦታዎች ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ለሙከራ የሚሆን ከዚህ ቀደም በአካባቢው በአርሶ አደሮች ያልተሞከሩ የጤፍ ዘር፣ የስንዴ ዘርና እንዲሁም የበቆሎ ዘር ተዘርቶ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና ጥሩ ምርትም እንደሚገኝበት በመስክ ጉብኝቱ የተገኙ ባለሙያዎች አስተያየታቸውን ሰጥተውበታል።

    የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ሰለሞን አዲሱ በአራቱም ቦታዎች ላይ የተሠሩ የምርምር ሙከራዎችን ለተጋባዥ እንግዶች ሲያስጎበኙ እንዳሉት የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ቦታውን ከተቀበለ በኋላ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ተግባር ለማስገባት ሲባል የመኪና መንገድ፣ ድንበር ማስወሰን፣ ዘርና ማዳበሪያ ግዥ የመሳሰሉ ሂደቶችን አልፈው ያልተሞከሩ የዘር አይነቶችን ለመሞከር ለአርሶ አደሩ በተሻለ መልኩ አምርቶ ለማሳየት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው ማህበረሰቡ ከዚህ ልማት በዘር አቅርቦት፣ በጉልበት እንዲሁም በመሳሰሉት መንገዶች የሚጠቀምበትን መንገድ እናመቻቻለን ብለዋል።

    ተመሳሳይ ዜና፦ Addis Ababa University receives over USD3.5 million award for Health Professional Education Partnership Initiative (HEPI) through the US government fund

    የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኑ ገድፍ በጉብኝቱ የተገኙ ሲሆን ይህ የምርምር ሥራ ከምርታማነት አንጻር ከአርሶ አደሩ በተለየ ሁኔታ ለውጥ ማምጣት አለበት፣ ተመራማሪዎቻችን የሚመራመሩበት፣ አዲስ የዘር ዝርያ /variety/ የሚወጣበት እንዲሁም የተለያዩ ተማሪዎች የምርምር ሥራቸውን በተግባር የሚሰሩበት የልህቀት ማዕከል /center of excellence/ መሆን ይገባዋል ብለዋል።

    አጠቃላይ 54.8 ሄክታር ከሚደርሰው መሬት ውስጥ በአራት የተለያዩ ቦታዎች ላይ ከተዘሩት የተለያዩ አዝዕርት ዘር የተዘራ ሲሆን ከዚህ ቦታ በተጨማሪ ያልተዘራበት ስምንት ሄክታር በመተው ተመራማሪዎች የምርምር ሥራቸውን እያካሄዱበት ይገኛሉ። በጉብኝቱ ወቅት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን፣ የአስተዳደር ሠራተኞች፣ የግብርና ባለሙያዎችና የዩኒቨርሲቲው አመራሮች የተገኙ ሲሆን የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተሰጠውን መሬት ወሰን በማስከበር እንዲሁም ዘላቂ እቅድ በማቀድ ከዚህ የምርምር ሥራ ማኅበረሰቡ የሚጠቀምበትን መንገድ ማመቻቸት አለበት ተብሏል።

    (በትዕግስት ዳዊት)
    ምንጭ፦ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

    የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፎቶ ምንጭ፦ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Viewing 15 results - 16 through 30 (of 30 total)