Search Results for 'አዲስ አበባ'

Home Forums Search Search Results for 'አዲስ አበባ'

Viewing 15 results - 361 through 375 (of 495 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – STEMpower የተሰኘ መቀመጫውን USA (ሳሌም፥ ማሳቹሴትስ፣ አሜሪካ) ያደረገ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሒሳብ ትምህርቶችን በዩኒቨርሲቲዎች እየረዳ የሚገኝ ሲሆን በአገራችን 13 ማዕከላትን ከፍቶ በትብብር እየሠራና እየረዳ ይገኛል።

    ድርጅቱ የድጋፍ አድማሱን በማስፋት በኢትዮጵያ ተጨማሪ 10 ማዕከላትን (ሰባት ማዕከላትን በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች፣ ሶስቱን በተለያዩ ከተሞች እ.አ.አ. በ2019) ለመክፈት ከኢፌዴሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም ከሰባቱ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የትብብር ስምምነት የካቲት 14 ቀን 2011ዓ.ም. ተፈራርመዋል።

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ሂሩት ወልደማርያም (ፕ/ር) STEMpower ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ትምህርቶችን ለማበልጸግ እያደረገ ያለውን ትብብር በማመስገን፥ ዩኒቨርሲቲዎችም ዕድሉን በመጠቀም በአግባቡ ማዕከላቱን ማሳለጥ እንደሚጠበቅባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

    አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በማስተማሪያ ክፍሎቹ ውስጥ ዲጂታል ሰሌዳዎችን መጠቀም ጀመረ።

    የሳንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር) በበኩላቸው ለሰባቱ ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚዳንቶች (አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲአዲግራት ዩኒቨርሲቲአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲጅማ ዩኒቨርሲቲ እና ወሎ ዩኒቨርሲቲ) ማዕከሉን በመጠቀም በአካባቢዎቻቸው ያሉትን የማኅበረሰብ ችግሮች መፍታት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

    የSTEMpower አስተባባሪ ዳይሬክተርና ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ቅድስት ገብረአምላክ፥ “STEMpower ከየት ወዴት?” በሚል ርዕስ ከድርጅቱ አመሠራረት ጀምሮ ዓላማውን፣ አሁን ያለበት ሁኔታ እና የወደፊት ዕቅድ አጭር ማብራሪያ ለተሳታፊዎቹ አቅርበዋል። ለወደፊትም ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በስፋት እንደሚሠሩ ፣ በ2040 የበለጸገች ኢትዮጵያን ማየት እንደሆነ ገልጸዋል።

    አገራችን ኢትዮጵያ የራሷን የሆነ ጥንታዊ ታሪክና ባህል ያላት አገር እንደመሆኗ ድርጅቱ በማኅበራዊ ሳይንስ ላይም ትኩረት እንዲያደርግ ከተሳታፊዎቹ አስተያየት ተሰንዝሯል።

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ማዕከሎቹ በከፍተኛ ትምህርት እና በሳይንስ ትምህርቶች አከባቢ የሚስተዋሉትን ችግሮች በመቅረፍ የአገሪቱን ብልጽግና ከማረጋገጥ ረገድ መልካም ሁኔታ እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    STEMpower


    Semonegna
    Keymaster

    ድሬዳዋ (ሰሞነኛ)– ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ያስተማራቸውንና ያሰለጠናቸውን የሕክምና ኮሌጅ ዕጩ ዶክተር ምሩቃንን እና የአርክቴክቸር ትምህርት ክፍል ዕጬ ምሩቃንን በዛሬው እለት የካቱት 16 ቀን 2011 ዓ.ም በደማቅ ሥነስርዓት አስመረቀ።

    የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በኪነ-ሕንጻ በመደበኛ የትምህርት መርሃግብር ለ5 ዓመታት አስተምሮ ካስመረቃቸው 36 የኪነ-ሕንጻ ተማሪዎች መካከል 12ቱ ሴቶች ናቸው። ከኪነ-ሕንጻ ተመራቂዎች በተጨማሪ ዩኒቨርሲቲው የሕክምና ኮሌጅ ለ3ተኛ ጊዜ በሕክምና ዘርፍ ያስተማራቸውን 17 ተማሪዎችንም በሕክምና ዶክተር አስመርቋል።

    የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለፓን አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ ማሰገንቢያ የሚውል አስር ሚሊዮን ብር ለገሰ

    የገጠሩን ህብረተሰብ ጤና በመጠበቅ ምርታማነትን ለማሳደግና በኮንስትራክሽን ዘርፍ ያሉ ክፍተቶችን ለማረም ምሩቃን ተግተው መስራት እንዳለባቸው በምርቃት ሥነ-ስርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ኢብራሂም ዑስማን አሳስበዋል። ከንቲባ ኢብራሂም ዑስማን ለተመራቂዎቹ ዲግሪና በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች የተዘጋጀውን ልዩ ሽልማትና ዋንጫ አበርክተዋል።

    ከንቲባው ባስተላለፉት መልዕክት፥ ተመራቂዎች የቀሰሙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥና በቁርጠኝነት በመስራት በሀገሪቱ የተጀመረውን ተስፋ ሰጪ የለውጥ እንቅስቃሴ ከዳር ለማድረስ ተግተው ሊሠሩ ይገባል በማለት ተናግረዋል። በተለይ ተመራቂ ሐኪሞች የገጠሩን ህብረተሰብ ጤና በአስተማማኝ መንገድ በመጠበቅ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ለማድረግ ታች ህብረተሰቡ ድረስ ወርደው መስራት እንደለባቸው አሳስበዋል።

    ከንቲባው አክለውም፥ “የኪነ-ሕንፃ ተመራቂዎች የሀገራችን ቀደም የኪነ-ሕንፃ ጥበብን ከዘመናዊው ጥበብና ዕውቀት ጋር በማዋሃድ በሀገሪቱ እየተስፋፋ ያለውን የዘርፉን ዕድገት ማስቀጠል አለባቸው” ብለዋል።

    ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን ያስተላለለፉት የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ያሬድ ማሞ በበኩላቸው ሁለቱም ሙያዎች ለሀገሪቱ የዕድገት ጉዞ መሳካትና ለማህበረሰቡ መለወጥ የጎላ ጠቀሜታ እንዳላቸው ተናግረዋል።

    በኦሮሚያ ክልል አቦካዶ አምራች ገበሬዎች የተሻሻሉ ዘሮችን በመጠቀም ምርታቸውን ማሳደግ ችለዋል

    የሕክምና ባለሙያዎች ሰብዓዊ ርህራሄና ታታሪነትን ተላብሰው በሕክምና ዘርፍ ልዩ አሻራ ማስቀመጥ እንዳለባቸው በመጠቆም፥ “የሕክምና ባለሙያዎች በቸልተኝነት ሳቢያ የታመሙ ሰዎች በእጃቸው እንዳይጠፉ ምንግዜም ተጠንቀቁ” በማለት አሳስበዋል። በተጨማሪም፥ “የኪነ-ሕንፃ ተመራቂዎች በሀገሪቱ ዕድገት ላይ ትልቅ ሚና መጫወት ይገባቸዋል” ብለዋል።

    የኢትዮጵያ አርክቴክቶች ማኅበር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ዘርዓይ መስፍን በበኩላቸው በምረቃው ላይ ተገኝተው በከፍተኛ ማዕረግ ለተመረቁት ተማሪዎች ሽልማት ሰጥተዋል። የኪነ-ሕንፃ ተመራቂዎች እስከ መጨረሻ በመማርና እውቀትን በማካፈል ከፊታቸው የሚጠብቃቸውን ግዳጅና ብሩህ ተስፋ ለማሳካት ትኩረት ሰጥትው መንቀሳቀስ እንደለባቸው አሳስበዋል።

    ከተመራቂ ሐኪሞች መካከል 3 ነጥብ 8 ውጤት በማምጣት በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቀው ዶ/ር አቤል ወልደጊዮርጊስ በየትኛውም የሀገሪቱ የገጠር ዳርቻ በመጓዝ ወገኖቹን ለመርዳት ዝግጁ መሆኑን ተናግሯል። “ይህም በሕክምናው መስክ የተቸገሩትን ወገኖችን የመርዳት የልጅነት ህልሜ እውን ለማድረግ ያግዘኛል” ብሏል።

    በኪነ-ሕንፃ ዘርፍ 3 ነጥብ 5 ውጤት በማምጣት በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቀችው ወጣት ትርሲት ታምራት በሀገሪቱ እየጎለበተ ባለው የኪነ-ህንፃ ዘርፍ ሙያዊ እውቀቷን በመጠቀም አንዳች አሻራ ለማስቀመጥ መዘጋጀቷን ተናግራለች።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ


    Semonegna
    Keymaster

    የነዋሪዎች የዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት መዘመን በመታወቂያ ማጭበርበርን ለመቀነስ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ሲታመንበት፤ መታወቂያ አሰጣጡ ደረጃውን የጠበቀና በአሻራ የተደገፈ እንደሆነም ተጠቁሟል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) አዲስ አበባ ዲጂታል የነዋሪዎች መታወቂያ በሚቀጥለው ሳምንት መጨረሻ መስጠት እንደምትጀምር የከተማዋ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ አስታወቀ። በኤጀንሲው የነዋሪዎች አገልግሎት ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ መሐመድ አብዱራሂም ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንዳሉት ተቋሙ አገልግሎቱን ለማዘመን እየሠራ ነው።

    አዲሱ የዲጂታል መታወቂያ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አገልግሎቱ የሚጀመር ሲሆን ለዚህም በቂ መታወቂያ ካርዶች መዘጋጀታቸውን ነው አቶ መሐመድ ያነሱት። በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የአዲሱ መታወቂያ አሰጣጥ ጥንካሬና ድክመት ታይቶ በቀጣይ በሁሉም ክፍለ ከተማ ወረዳዎች መስጠት ይጀመራል ብለዋል። አዲሱ መታወቂያ የብሔር ማንነትና የትውልድ ቦታ የሚገልጽ ይዘት የሌለው ሲሆን በአንጻሩ የደም ዓይነት እንዲጠቀስ መደረጉም ተገልጿል።

    የልደት፣ የጋብቻ፣ የፍቺና የሞት ወሳኝ ኩነት ምዝገባዎች ከሐምሌ 30 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ በአንድ ማዕከል የሶፍትዌር ምዝገባ በዘመናዊ መልኩ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን የአጄንሲው የመረጃ ቅበላና ማስረጃ አቅርቦት ዳይሬክተር አቶ አንተነህ ካሳ ተናግረዋል። ሆኖም የነዋሪዎች አገልግሎት በተበታተነ መልኩና በወረቅት ላይ የተመሠረተ እንደነበር ያነሱት አቶ አንተነህ፥ አሁን አገልገሎቱን ዲጂታል ለማድረግ እየተሠራ ነው ብለዋል።

    በችግሮች የተተበተበው የ አዲስ አበባ ከተማ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (condominium houses) ግንባታና አሰጣጥ ጉዳይ

    የነዋሪዎች የመታወቂያ አገልግሎትን ማዘመን ከከተማ አስተዳደሩ ቁልፍ ሥራዎች አንዱ መሆኑን የጠቀሱት አቶ መሐመድ ለዚሁ ሥራ በጀት ተመድቦለት ዝግጅት መጠናቀቁንም ተናግረዋል። የነዋሪዎች መታወቂያ አገልግሎት መዘመን በመታወቂያ ማጭበርበርን ለመቀነስ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ያነሱት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፥ መታወቂያ አሰጣጡ ደረጃውን የጠበቀና በአሻራ የተደገፈ እንደሆነም ጠቁመዋል። ደኅንነቱ የተጠናከረ የነዋሪዎች መረጃ ምዝገባ ሶፍትዌር፣ የመታወቂያ ማተሚያና የአሻራ መቀበያ መሳሪያዎች መዘጋታቸውንም ተናግረዋል።

    አገልግሎቱ የኢንተርኔት አቅርቦትን የሚፈለግ በመሆኑ የኔትወርክ መቆራረጥ እንዳያጋጥም የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር እየሠሩ ነውም ብለዋል። ነባሩ መታወቂያ በዲጂታል ሙሉ ለሙሉ እስኪቀየር ድረስ የወረቀት መታወቂያ አሰጣጡ እንደማይቋረጥም አቶ መሐመድ ገልጸዋል።

    በጉለሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ 3 ነዋሪ አቶ ልዑልሰገድ በላይ እስካሁን ያለው መታወቂያ አሰጣጥ ዘመናዊ አይደለም፤ መታወቂያውም ኤሌክትሮኒክ አለመሆኑ በቀላሉ ለብልሽት ይዳረጋል ይላሉ። ከተማ አስተዳደሩ አሁን የዲጂታል መታወቂያ መስጠት ልጀምር ነው ማለቱ እንዳስደሰታቸው የተናገሩት አቶ ልዑል ሰገድ፥ በፍጥነት ተግባራዊ በማድረግም ማጭበርበርን መቀነስ ይግባል ብለዋል።

    የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት የከተማዋን የትራንስፖርት ችግር መፍታት ያልቻለው ለምን ይሆን?

    የዲጂታል መታወቂያ ሊጀመር መሆኑ ፋይዳው የላቀ መሆኑን የተናገሩት የዚሁ ወረዳ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ውዱ አሰፋ፥ አንድ ሰው የነዋሪነት መታወቂያ አንድ ጊዜ ብቻ እንዲያወጣ በማድረግ የተለያየ መታወቂያ በማውጣት የሚሠሩትን ወንጀል ያስቀራል ብለዋል። በተለይ የጣት አሻራ እና የአይን አሻራ የሚወስድ ቴክኖሎጂ የሚጠቀም መሆኑ አገልግሎቱን ለማዘመን፣ ለህጋዊ ማስረጃዎች ተዓማኒነት ፋይዳው የላቀ መሆኑን ነው ያነሱት።

    በጉለሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ አንድ ነዋሪ ኮማንደር መሀመድ ሁሴን አዲስ የሚጀመረው መታወቂያ የብሔር ማንነትን ስለማያካትት የብዙ ሰዎችን ጥያቄ እንደሚመልስ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ መታወቂያው እንበለጸጉት ሀገራት ደረጃውን የጠበቀና ማንም በቀላሉ በሀሰተኛ መንገድ ሊያዘጋጀው የማይችል መሆኑም ሌላው መልካም ጎኑ ነው ሲሉም ገልጸፀዋል።

    በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሁለት የወሳኝ ኩነት ምዝግባና ነዋሪዎች አገልግሎት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መልዓከ ብርሃኑ፥ የነዋሪዎችን አገልግሎት የማዘመን ሂደቱ የግብዓት እና የሠራተኛ እጥረትን ከመቅረፍ መጀመር አለበት ነው ያሉት። የከተማው ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ በቅድሚያ ብቁ የሰው ኃይል፣ ግብዓትና ምቹ የቢሮ ሁኔታ ፈጥሮና አሟልቶ ወደ አገልግሎት እንዲገባም ጠይቀዋል። የነዋሪዎች አገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ ማዘመን ሰው ሠራሽ ስህተቶችን ለመቀነስ፣ ወንጀሎችን ለመከላከል እንደሚያግዝም ተናግረዋል።

    የወሳኝ ኩነት ምዝግባ የነዋሪዎች አገለግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ መሐመድ አብዱራሂም በየወረዳዎቹ የነዋሪዎች አገልግሎትን ለማዘመን ሠራተኞች በተለያየ ዙር እየሰለጠኑ መሆኑን አክለው አስታውቀዋል። በማዕከል ደረጃ አዲስ ለሚጀምረው የነዋሪዎች አገልገሎት አሰጣጥ 20 ብቁ የመረጃ እና ግንኙነት ቴክኖሎጂ (ICT) ባለሙያዎች ከመደበኛ ሠራተኞች በተጨማሪ ተመድበዋል ነው የተባለው።

    ምንጭ፦ ኢዜአ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የዲጂታል መታወቂያ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርን የግንባታ አፈፃፀም በፌዴራል ዋና ኦዲተር የተደረገ የክዋኔ ኦዲት መሠረት በማድረግ ይፋዊ ስብሳባ ጥር 27 ቀን 2011 ዓ.ም. አካሂዷል። በስብሰባው ቋሚ ኮሚቴው የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የ11 ዩኒቨርሲቲዎች የግንባታ ፕሮጀክት በተጠና ዕቅድ ላይ ያልተመራ እንደነበረ ገልጿል።

    በኦዲት ሪፖርቱ ግንባታዎቹ በምዕራፍ ተከፋፍለው መቼ እንደሚሠሩ፣ እያንዳንዱ ሥራ ምን ያህል ወጪ እንደሚጠይቅና በአጠቃላይ በመሪ ዕቅድ መሠረት ተግባራዊ ባለመደረጉ በግንባታው ሊሟሉ የሚገቡ የግብዓት፣ የቤተ ሙከራና የመፅሐፍት ግዥ ማሟላት እና የካሣ ክፍያ በተገቢው ሁኔታ መፈፀም አለመቻሉ ተገልጿል።

    በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የ11 ዩኒቨርሲቲዎች የግንባታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ደስታ በሰጡት ምላሽ ግንባታዎቹ የ5 ዓመት መሪ ዕቅድ ቢያዘጋጁም በዕቅዱ መሠረት ለማከናወን የበጀት እጥረት በመኖሩ በዕቅዱ መሠረት መፈፀም እንዳልተቻለ፤ የግብዓትና የቤተ ሙከራ እቃዎችን የመንግሰት ግዢና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በወቅቱ ባለማቅረቡ የተፈጠረ ችግር መሆኑን ገልፀው፥ እንደመፍትሔ ተማሪዎች ወደ አጎራባች ዩኒቨርሲቲዎች ሄደው የቤተ ሙከራ ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረገ እንደሚገኝ እና የካሣ ክፍያን በተመለከተ ክልሎች የተከፋዮችን ዝርዝር በተሟላ ሁኔታ አደራጅተው የማይልኩና ለተከፋዮቹም በቀጥታ በአካውንታቸው እንዳይገባ የተለያዩ ምክንያቶችን በማስቀመጥ ክፍያው እነሱ በፈለጉት አግባብ መፈፀሙን ተናግረዋል።

    የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለፓን አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ ማሰገንቢያ የሚውል አስር ሚሊዮን ብር ለገሰ

    ለዲዛይን መጣጣምና ቁጥጥር ለሚሠሩ አማካሪዎች ክፍያ በበጀት ብር 28,600,000.00 የተያዘ ሲሆን ከአማካሪ ድርጅቱ ጋር ውል ሲፈራረሙ ብር 117,668,636.09 በመሆኑ ብር 89,068,636.09 (311%) በብልጫ መዋዋሉ የኦዲት ግኝቱ አመልክቷል።

    አማካሪዎች ክፍያን በተመለከተ በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዲኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ተጨማሪ ምላሽ 28 ሚሊዮን ብር በ2008 ዓ.ም. /ለአንድ ዓመት/ ብቻ ለሚከናወን ግንባታ የተገመተ እንደሆነ እና ብር 117 ሚሊዮን ግንባታው በሚቆይባቸው አጠቃላይ ዓመታት የተቀመጠ ወጪ መሆኑን ተናግረዋል።

    ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የሚሠራቸው የግንባታ ሥራዎች ውጤታማ ይሆኑ ዘንድ ከፌዴራል፣ ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደሮች ጋር ተቀናጅቶ መሥራት የሚጠበቅበት ቢሆንም ቅንጅት ባለመፈጠሩ ምክንያት የውሃ፣ የመብራትና የስልክ አገልግሎት ችግር ማጋጠሙን፣ የካሣ ክፍያ ተፈፅሞላቸው ከይዞታቸው ያልተነሱ መገኘታቸውን እና በደምቢ ዶሎ፣ በወራቤ፣ በራያ፣ በመቅደላ፣ በአምቦና ቦንጋ ዩኒቨርሲቲዎች ለካሣ ክፍያ በበጀት ለግንባታ ተነሽዎች 100 ሚሊዮን ተይዞ የነበረ ቢሆንም ተከፍሎ የተገኘው 215,071,377.16 መሆኑንና ይህም ክፍያ የብር 115,071,377.16 ብልጫ ያለው መሆኑ ተገልጿል።

    ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅት ከመፍጠር አንጻርም ከክልልና ከከተማ አስተዳደሮች ከፍተኛ ድጋፍና ትብብር በተለያየ ሁኔታ እንደተደረገላቸው፤ የሚመለከታቸውን አካላትን ማወያየታቸውንና አስፈላጊ ክፍያዎችንም ለአገልግሎት አቅራቢ ተቋማት መፈፀማቸውን ገልፀው ነገር ግን በተለይም የኤሌክትሪክ አገልግሎት አስካሁን በተሟላ ሁኔታ ሊያገኙ አለመቻላቸውን የተቋሙ ኃለፊዎች ተናግረዋል።

    በኦሮሚያ ክልል አቦካዶ አምራች ገበሬዎች የተሻሻሉ ዘሮችን በመጠቀም ምርታቸውን ማሳደግ ችለዋል

    በመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ የ3,210,218.24 ብር የካሣ ክፍያ ሰነድ ማስረጃ ሳይኖረው መከፈሉን፤ በወራቤ ዩኒቨርሲቲ የግንባታ ሳይት 17 አባወራዎች የግንባታ ካሣ ቢከፈላቸውም አለመነሳታቸው፤ በራያ ዩኒቨርሲቲ የግንባታ ፕሮጀክት ለሚገኙ 35 ካሣ ተከፋዮች ክልሉ በመጀመሪያ አጥንቶ ካፀደቀው ብር 7,347,757.30 ውስጥ ብር 4,049,779.00 በመቀነስ ብር 3,279,978.30 ብቻ የከፈለና ለሌሎች በጥናቱ ውስጥ ለሌሉ 6 ተነሺዎች ብር 399,706.32 ካሣ መከፈሉ በኦዲት ግኝቱ ተገልጿል።

    የካሣ ክፍያ በበጀት ከፀደቀው ሊቀነስ የቻለው ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በዕቅድ ያስቀመጠውን የካሣ ተመን እንዲቀንሱ በተሰጣቸው ትዕዛዝ መሠረት መፈፀሙን፤ ካሣ ተከፍሏቸው ከተነሱ በኋላ እንደገና ተመልሰው የሚሠፍሩ ነዋሪዎችን በተመለከተም ተነሺዎች ካሣው አንሶናል፣ ተተኪ ቦታ አልተሰጠንም የሚሉና ሌሎች ምክንያቶችን በማንሳት ተመልሰው የሚሠፍሩ መሆኑን አቶ ሰለሞን ደስታ አስረድተዋል።

    የዩኒቨርስቲዎች ፕሮጀክቶች ግንባታ ለባለይዞታዎች ካሣ ተከፋዮች የግል አካውንታቸው ማስገባት እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስቴር ያወጣው መመሪያ ቢገልፅም መመሪያው ተጥሶ ለ468 ባለይዞታዎች ለራያ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ ተነሺዎች በጥቅል በደደቢት ብድርና ቁጠባ ሂሣብ ቁጥር ውስጥ እንዲገባ መደረጉ፤ በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ ተነሺዎች ለፍቼ ማዘጋጃ ቤት አገልግሎት መምሪያ፣ ለቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ ተነሺዎች ከፋ ዞን ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት መምሪያ ግዥ፣ ክፍያና ንብረት አስተዳደር እና ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ ተነሺዎች በእንጅባራ ከተማ አስተዳደር ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት አጠቃላይ ብር 79,925,769.02 እንዲገባ መደረጉ እና እስከ ህዳር 29/2009 ዓ.ም ድረስ ገንዘቡ ያልተወራረደ መሆኑ ግኝቱ አመልክቷል።

    The Yellow Movement AAU: Speaking up for women and girls – empowering women (Ethiopia)

    ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በሰጡት ምላሽ ካሣ ለባለይዞታዎቹ እንዲከፈል መመሪያ ተዘጋጅቶ በመመሪያው መሠረት ለተነሺዎች ካሣ እንዲከፈል ቢታቀድም ክልሎች በአንድ ጊዜ ገንዘቡ ለተነሺዎች ቢሰጣቸው በዘላቂ አኗኗራቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል በሚልና በሌሎች ምክንያቶች በተነሺዎች በአካውንታቸው ገቢ አለመደረጉን ገልፀዋል።

    የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አባላት በሰጡት አስተያየት ሚኒስቴር መ/ቤቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር አቅዶና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተቀናጅቶ የመሥራት ውስንነት መኖሩን፤ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ አለመደረጉን ገልፀው የግለሰቦች የካሣ ክፍያ ሚኒስቴር መ/ቤቱ በወጣው መመሪያ መሠረት በየግል አካውንታቸው ገቢ ሊደረግ እና የግንባታ ፕሮጀክቶች ከአከባቢው ማህበረሰብ ጋር በተገቢ መጠን ውይይት ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

    ክቡር አቶ ገመቹ ዱቢሶ የፌዴራል ዋና ኦዲተር በሰጡት አስተያየት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የ11 ዩኒቨርሲቲዎችን ለመገንባት ሲያስብ በዕቅዱ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን በተገቢ ሁኔታ ያለየ መሆኑን፤ ከፌዴራልና ከክልል አካላት ጋር ከፍተኛ የቅንጅት ችግር መኖሩን፤ ከግብዓት ጋር በተያያዘ በየዩኒቨርሲቲዎቹ ግቢ ሜዳ ላይ ሣር እየበቀለባቸው ያሉ ግብዓቶች እስካሁንም በመኖራቸው ትኩረት ተሰጥቶ ሊሠራ እንደሚገባ፤ የካሣ ክፍያዎች በተቀመጠው መመሪያ መሠረት ሊፈፀም እና ክፍያዎቹ ለባለመብቶቹ መድረሱን ሚኒስቴር መ/ቤቱ ሊያረጋግጥ እንደሚገባ አሳስበዋል።

    የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ መሐመድ የሱፍ በኦዲት ግኝቱ የታዩ ችግሮችን በዕቅድ መፍታትና ማረም እንደሚገባ ጠቅሰው ችግሮቹ በሌሎች ተመሳሳይ ግባታዎች እንዳይደገሙ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በትኩረት መሥራት እንዳለበት አሳስበዋል።

    ምንጭ፦ የፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የ11 ዩኒቨርሲቲዎች የግንባታ ፕሮጀክት


    Anonymous
    Inactive

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በኪነ ህንፃ ሲያስመርቅ ዘንድሮ ለሦስተኛ ጊዜ ሲሆን፥ ዘንድሮ የተመረቁት 18 ወንዶችና 16 ሴቶች በአጠቃላይ 34 የኪነ ህንፃ ሙያተኞች መሆናቸውን በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ ተገልጿል።

    ጎንደር (ሰሞነኛ)–የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለአምስት ዓመት ተኩል በኪነ ህንፃ ትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ቅዳሜ፥ የካቲት 9 ቀን 2011 ዓ.ም. በባችለር ዲግሪ (BSc in Architecture) አስመረቀ።

    በምረቃ ሥነ ስርአቱ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት ያስተላለፉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደሳለኝ መንገሻ፥ ዩኒቨርሲቲው በኪነ ህንፃ የትምህርት ዘርፍ ዘንድሮ ተማሪዎችን ሲያስመርቅ ለሦስተኛ ጊዜ መሆኑን ገልፀዋል።

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአሁኑ ወቅት በቴክኖሎጂ የትምህርት መስኮች ከ5 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያሰለጠነ እንደሚገኝ የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ፥ ቅዳሜ ዕለት የተመረቁት 18 ወንዶችና 16 ሴቶች በአጠቃላይ 34 የኪነ ህንፃ ሙያተኞችም በሀገራችን የሚታየውን የህንፃ ጥበብ ችግር ለማስተካከልም ሆነ በሙያው የሚታየውን የሰለጠነ የሰው ኃይል ለመቅረፍ እንዲተጉ አሳስበዋል።

    የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለፓን አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ ማሰገንቢያ የሚውል አስር ሚሊዮን ብር ለገሰ

    የጎንደር ከተማ ም/ከንቲባ ዶ/ር ሙሉቀን አዳነ በምርቃቱ ሥነ ስርዓት ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው የተመራቂዎቹ የምርቃት ዕለት የልጅነት ዘመን አብቅቶ ለሀገር ብቁ የሆነ የኪነ ህንፃ ባለሙያ የሚሆኑበት ዕለት እንደሆነ አስገንዝበዋል። ከዚህ በኋላም ተመራቂዎቹ ሀገሪቱ ለረዥም ዓመታት የምትጠራበትና የምትታወስበትን የኪነ ህንፃ ጥበብ እንደሚያበረክቱ እምነታቸውን ገልፀዋል።

    ተመራቂዎቹም በሙያቸው ሀገራቸውን ለማገልገል የገቡትን ቃል ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

    ከዩኒቨርሲቲው ዜና ጋር በተያያዘ የዩኒቨርሲቲው ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የማኔጅመንትና የህዝብ አስተዳደር ት/ቤት “በወቅታዊ የፖለቲካ ለውጥ ዘላቂነት ላይ የምሁራን ሚና” (‘The Role of Academicians in Sustaining the Current Political Reforms’) በሚል ርዕስ ዙሪያ ከካቲት 6 እስከ 7 ቀን 2011 ዓ.ም. ኮንፈረንስ አካሂዷል።

    በዕለቱ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ደሳለኝ መንገሻ፣ በጠቅላይ ሚኒስቴር ፅ/ቤት የመሰረተ ልማትና የከተማ ልማት አማካሪ ዶ/ር አምባቸው መኮንን፣ የጎንደር ከተማ ም/ከንቲባ ዶ/ር ሙሉቀን አዳነ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ፖለቲከኛ ፕ/ር መረራ ጉዲና፣ ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ ደራሲና የታሪክ ተመራማሪው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ የጎንደር ከተማ የልማትና የሰላም ሸንጎ አባላት የዩኒቨርሲቲው ም/ፕሬዚዳንቶች፣ ዲኖች፣ መምህራን፣ ተማሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

    Anonymous
    Inactive

    100 የአሊያንስ ትራንስፖርት አውቶቢሶች ከስራ ታገዱ
    —–
    አንድ መቶ ያህል የአሊያንስ ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ንብረት የሆኑ የከተማ አውቶቡሶች ከስራ ታገዱ፡፡ አውቶቡሶቹ የታገዱት በባንክ የብድር አከፋፈል ስርዓት ላይ በተፈጠረ አለመግባባት እንደሆነም ታውቋል፡፡

    ባለፈው ረቡዕ ከሰዓት በኋላ የአሊያንስ ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር የቦርድ ሰብሳቢና አባላት በጌትፋም ሆቴል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር አክሲዮን ማህበሩ በገባው ውል መሰረት ብድሩን በየወሩ ለመክፈል በአገሪቱ ላይ የተፈጠረው ፖለቲካዊ አለመረጋጋት፣ አውቶቡሶቹ የሚያስፈልጋቸውን የመለዋወጫ እቃ ከውጭ ለማስመጣት በነበረ የውጭ ምንዛሬ እጥረትና ተያያዥ ችግሮች እንቅፋት በመሆናቸው በውል መሰረት መክፈል አለመቻላቸውንና በዚህም ምክንያት አበዳሪያቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መቶዎቹ አውቶቡሶች ስምሪት ላይ እንዳይውል ከጥር 28 ጀምሮ እግድ ማውጣቱን ተናግረዋል፡፡

    ከ2500 በላይ ባለ አክሲዮኖች እና ከ600 በላይ ሰራተኞች ያሉት አሊያንስ ትራንስፖርት አክሲዮን ማኅበር፤ በ2005 ዓ.ም 25 ያህል አውቶቡሶችን በመግዛት የከተማ ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የገለፁት የቦርድ ሰብሳቢው ዶ/ር አዲል አብደላ፣ መንግሥት በ2008 ዓ.ም 500 ያህል የከተማ አውቶቡሶች በግል አንቀሳቃሾች ወደ አዲስ አበባ ገብተው በአዲስ አበባና በዙሪያው ላሉ ከተሞች አገልግሎት እንዲሰጡ የቀረጥ ነፃና የብድር አቅርቦት ባመቻቸበት ወቅት 300 ያህል አውቶቡሶች እንዲገዙ ከመንግስት ፈቃድ ማግኘታቸውን አስታውሰዋል፡፡

    ይሁን እንጂ በወቅቱ የነበራቸው አቅም ከ100 አውቶቡሶች በላይ ማስመጣት ባለመቻሉ መቶዎቹን ብቻ በብድር ገዝተው ወደስራ እንዲሰማሩ መደረጉን ገልፀው ባንኩ የ6 ወር የእፎይታ ጊዜ ቢሰጣቸውም አውቶቡሶቹ ወደ አገር ገብተው ከማለቃቸው በፊት የእፎይታ ጊዜው እንዳለቀና አውቶቡሶቹ በቅጡ ስራ ሳይጀምሩ ባንኩ ብድር ክፈሉ በማለቱ ከሌሎች በጀቶችም ከሌላም እያመጡ መክፈል መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡
    “መቶዎቹ አውቶቡሶች የመንግስት ፕሮጀክቶችና ራሱ መንግስት ታሪፍ ያወጣላቸው እንጂ በንግድ ታሪፍ የሚሰሩ አይደሉም” ያሉት የአክሲዮን ማህበሩ የቦርድ አባላት በአሁን ጊዜ የትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ለባንኩ ደብዳቤ በመፃፍ፣ ጉዳዩን የሚያጣራ ኮሚቴ በማቋቋምና ራሳቸውም ከባንኩ ጋር በመወያየት ጉዳዩን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

    ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ

    Semonegna
    Keymaster

    ዘመን ባንክ እንደ ይሁዳ – (ኤርሚያስ አመልጋ – ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት)
    (አጽንቼ ያቆምኩትን ባለውለታውን ዞሮ የወጋው ዘመን ባንክ)

    ከ20 ዓመታት የአሜሪካ ቆይታ በኋላ ወደ አገር ቤት ተመልሼ በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ ስሥራ እንደመቆየቴ፣ የሥራዬ ባህሪ ከባንኮች ጋር ያገናኘኝ ነበርና አዘውትሬ ወደተለያዩ የአገሪቱ ባንኮች እሄድ ነበር። ሁሉም ባንኮች ግን፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የማይጠቀምና የደንበኞችን ፍላጐት በተቀላጠፈ መልኩ የማያረካ፣ ኋላቀር የባንክ አሠራር ይዘው ነበር የማገኛቸው።

    በ2001 ዓ.ም. በባንኩ ዘርፍ ላይ ጥናት ካደረግኩ በኋላ፣ በወቅቱ በተለያዩ የአገሪቱ ባንኮች የሚታየውን ኋላቀር የባንክ አሠራር ወደ ጐን በመተው፣ ለአገሪቱ አዲስ የሆነና ባደጉት አገራት የሚሠራበት ዘመናዊ አሠራር የሚከተል በአይነቱ የተለየ ባንክ ለማቋቋም ወሰንኩ።

    የማቋቁመው ባንክ ከዚህ ቀደም በአገሪቱ የነበሩ ባንኮች ከሚሰጡት የተለየ ቀልጣፋና ዘመናዊ አሠራር የሚከተል እንዲሆን በማሰብም፣ አቅም ላላቸው ደንበኞች ብቻ ትኩረት በመስጠት፣ ከዚህ በፊት በአገሪቱ ባልተለመደ መልኩ በአንድ ቅርንጫፍ ብቻ አገልግሎት መስጠት የሚቻልበት አዲስ የባንክ አሠራር ቀየስኩ። ባንኩ በአንድ ቅርንጫፍ ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ቢሆንም፣ የባንኩ ባለሙያዎች ደምበኞች ያሉበት ቦታ ድረስ ሄደው የሚያገለግሉበትና ተደራሽነት ያለው አዲስ አሠራር እንዲኖር በማድረግ አገልግሎቱ በቅርንጫፍ እጥረት እንዳይስተጓጎል ተጨማሪ በቴክኖሎጂ የታገዙ የአገልግሎት አሰጣጥ ዘዴዎችን ተግባራዊ አደረግኩ።

    ዘመን ባንክ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 1.1 ቢልዮን ብር ማትረፉንና ይህም ከባለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ15.3 መቶ ብልጫ እንዳለው አስታወቀ

    ወደ አክሲዮን ሽያጭና ባንኩን ወደማቋቋም ገባሁ። የአክሲዮን ሽያጩን በአግባቡ ለማከናወንና የሚፈለገውን ያህል ገንዘብ ለመሰብሰብ የባንኩን አጠቃላይ አደረጃጀት፣ የአገልገሎት አሰጣጥና የሥራ ዕቅድ በተመለከተ ለባለሃብቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን በተደጋጋሚ በማዘጋጀት ሰፊ ማብራሪያ በመስጠት በከፍተኛ ጥረትና መስዋዕትነት ከ3 ሺህ በላይ ከሚሆኑ ባለአክሲዮኖች 150 ሚሊዮን ብር ያህል አሰባሰብኩ።

    ዘመን ባንክን ለማቋቋም የጀመርኩት ጥረት በተለይ በብሔራዊ ባንክ ተደጋጋሚ እንቅፋቶች ገጥመውት ነበር። ያም ሆኖ ግን፣ በከፍተኛ መስዋዕትነት ፈተናዎችን ሁሉ ለማለፍ ተጋሁ። ከእልህ አስጨራሽ ቢሮክራሲና ኢፍትሃዊ ጣልቃገብነት በኋላም፣ ተሳካልኝና ዘመን ባንክን ወደ ሥራ አስገባሁት።

    ዘመን ባንክ በአገሪቱ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ የራሱን አዎታዊ ተፅዕኖ የፈጠረ ስኬታማ ባንክ ለመሆን ቻለ። ይዟቸው በመጣቸው አዳዲስ የባንክ አሠራሮች ቀልጣፋና ዘመናዊ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ዘመን ባንክ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ነው የብዙዎችን ቀልብ መሳብና በርካታ ደንበኖችን ማፍራት እንዲሁም ትርፋማ መሆን የቻለው። ለረጅም አመታት አገልግሎት በመስጠት ከሚታወቁት ሌሎች ነባር ባንኮች ተርታ ለመሰለፍ ጊዜ አልወሰደበትም። በአንድ ቅርንጫፍ ብቻ በዓመት ከታክስ ውጭ 120 ሚሊዮን ብር አትርፏል። ዘመን ባንክ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተጐናፀፈው ተጨባጭ ስኬት ብዙዎችን ማስገረሙን ቀጥሏል።

    ዘመን ባንክ በተቋቋመ በሦስተኛው ዓመት…

    በዘመን ባንክ የመመሥረቻ ጽሁፍና የመተዳደሪያ ደንብ ላይ፣ ከባንኩ ዘጠኝ የቦርድ አባላት መካከል ስድስቱ በየሶስት አመቱ መቀየር እንዳለባቸው በግልጽ ተቀምጧል። በዚህም መሰረት በሦስተኛው ዓመት ላይ፣ ከነባር የቦርድ አባላት ስድስቱን ለመቀየር ዝግጅት ማድረግ ጀመርን። እኔም የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ እንደመሆኔ፣ መቀየር አለባቸው ብዬ ያሰብኳቸውን ስድስት የቦርዱ አባላት መርጬ፣ ደንቡና አሠራሩ በሚፈቅደው መሰረት ለባለአክስዮኖች እንዲያጸድቁት አቀረብኩ። የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤም፣ ግለሰቦቹ ከቦርድ አባልነታቸው እንዲነሱ ወሰኑ።

    ብርሃን ባንክ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 410 ሚልዮን ብር ማትረፉን አስታወቀ

    ይሄን ተከትሎ ነው ነገር መበላሸት የጀመረው። በእኔ ጠቋሚነት ከቦርድ አባልነታቸው ከተነሱት ስድስት ሰዎች መካከል ሁለቱ ከአባልነታቸው በመነሳታቸው እጅግ በጣም ተበሳጩ። ከእነዚህ ግለሰቦች በተጨማሪ ለችግሩ መፈጠርና መባባስ መሪ ተዋናይ የሆነ አንድ ልዩ ቂም ያለውና የ500 ሺህ ብር አክሲዮን የገዛ ባለአክሲዮንና ተወካዩ ተጨመሩበት። ይህ ግለሰብ በዘመን ባንክ የምስረታ ዘመን፣ የግሉን ህንጻ እጅግ በተጋነነ ዋጋ ለባንኩ ለማከራየትና 36 ሚሊዮን ብር ያለአግባብ ወደ ኪሱ ሊያስገባ ሲሞክር፣ ዕቅዱን ስላከሸፍኩበት ቂም ይዞ ሊያጠቃኝ ደፋ ቀና ሲልና ባንኩን ሲበጠብጥ የኖረ ሰው ነው። ሌሎቹ ሁለቱም፣ በባንኩ የቦርድ አባልነታቸው የሚያገኙትን ጥቅማጥቅም በማጣታቸው ክፉኛ የተናደዱ ናቸው። እነዚህ ሰዎች በባንኩ ምስረታ ወቅት ስለተፈጸሙ ነገሮች የሚያውቁትን መረጃ መሰረት በማድረግ ነው ሊያጠቁኝ የተዘጋጁት።

    ነገሩ እንዲህ ነው…

    በአገሪቱ ሕግ መሰረት፣ አንድን ባንክ ለማቋቋም ከባለአክሲዮኖች የሚሰበሰበው ገንዘብ በቀጥታ በዝግ የባንክ አካውንት ውስጥ ነው የሚቀመጠው። የተሰበሰበውን ገንዘብ ማንቀሳቀስና ባንኩን ለማደራጀት በሚያስፈልጉ ሥራዎች ላይ ማዋል የሚቻለው፣ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ከሰጠ በኋላ ብቻ ነው። ፈቃድ እስኪሰጥ ድረስ ምንም መሥራት አይቻልም። ገንዘቡ እስኪለቀቅ ጠብቆ መደበኛ የባንክ ሥራ ለመጀመር ደግሞ፣ ቢያንስ ተጨማሪ የሁለት ዓመት ጊዜ ይፈጃል። እኔ ግን ብሔራዊ ባንክ ለዘመን ባንክ ፈቃድ እስኪሰጥና በዝግ ሂሳብ የተጠራቀመው የባንኩ ገንዘብ እስከሚለቀቅ ድረስ ሥራዎች እንዲጓተቱ አልፈለግኩም። በመሆኑም ለባንኩ ምስረታው የሚያስፈልጉ ወጪዎችን ከራሴ ገንዘብ ለመሸፈን ወስኜ፣ አርባ ሚሊዮን ብር የሚደርስ ገንዘብ ከራሴ ወጪ በማድረግ፣ አጠቃላይ ባንኩን በቁሳቁስና በሰው ሃይል የማደራጀት ሥራ ሠራሁ። ብሔራዊ ባንክ ብዙ ጊዜ ፈጅቶ ፈቃድ በሰጠን በቀናት ውስጥ ነበር፣ ዘመን ባንክን በቀጥታ ወደ ሥራ ያስገባሁት። ይህን በማድረጌም የዘመን ባንክ ባለአክሲዮኖች ሌላ የማንም ባንክ ባለአክሲዮን ያላገኘውን የሁለት ዓመት ትርፍ ጥቅም አስገኝቻለሁ።

    ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩት፣ በቅን ልቦና ተነሳስቼ በዘመን ባንክ ምስረታ ወቅት የራሴን ገንዘብ እያወጣሁ ሥራዎችን ስሠራ እንደነበር የሚያውቁትና በእኔ ጠቋሚነትና በጠቅላላ ጉባኤው ውሳኔ ከቦርድ አባልነታቸው የተሰናበቱት ግለሰቦች እና ተባባሪያቸው ከአመታት በኋላ ይህን ሁኔታ መሰረት አድርገው የግሌን ጥቅም ለማሳደድ ያደረግኩት ነገር አስመስለው ብሔራዊ ባንክ ሄደው በመክሰስ ሊበቀሉኝ ወሰኑ። በባንኩ ምስረታ ወቅት ህጋዊ አካሄድን ባልተከተለ መልኩ የተለያዩ ሥራዎችን ስሠራ እንደነበርና በሕግ ልጠየቅ እንደሚገባ ለብሔራዊ ባንክ አመለከቱ።

    ወጋገን ባንክ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት አንድ ቢልዮን ብር ማትረፉንና ይህም ከባለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ49 መቶ ብልጫ እንዳለው አስታወቀ

    ‘አቶ ኤርሚያስ ዘመን ባንክን ሲያቋቁም የግል ገንዘቡን ተጠቅሟል። የተለያዩ የባንኩ ሥራዎችን ያሠራ የነበረው ጨረታ ሳያወጣና የጥቅም ግጭት በሚያስከትል መልኩ ነበር። የአክሰስ ካፒታልም የዘመን ባንክም ሃላፊ ከመሆኑ ጋር በተያያዘም፣ የጥቅም ግጭት የሚያስከትል አሠራር ይከተል ነበር ወዘተ…’ የሚሉ ውንጀላዎችን በዝርዝር በመግለጽ፣ ጉዳዩ ተጣርቶ አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድብኝ የሚጠይቅ ማመልከቻ ለብሔራዊ ባንክ አስገቡ።

    የግለሰቦቹ አቤቱታ ለብሔራዊ ባንክ ትልቅ አጋጣሚ ሆነለት። ዱሮም በሄድኩበት ሁሉ እየተከተለ እንቅፋት ሲፈጥርብኝ የኖረውና እንቅስቃሴዬን ለመግታት ሰበብ ሲፈልግ የነበረው ብሔራዊ ባንክ፣ የግለሰቦቹን ማመልከቻ በደስታ ነበር የተቀበለው። ይህን ተከትሎም፣ መጋቢት 6 ቀን 2003 ዓ.ም. በጻፈው ደብዳቤ በዘመን ባንክ የምስረታ ወቅት አንዳንድ ወጪዎች የተደረጉት የጥቅም ግጭት በሚያስከትል መልኩ እንደነበር የሚጠቁሙ ምልክቶች ስለተገኙ በወቅቱ የተደረጉ የፋይናንስ እንቅስቃሴዎች በሙሉ በባንኩ በሚሾም ኦዲተር እንዲመረመር መወሰኑን ገለጸ። ይህም ብቻ አይደለም፤ ጉዳዩ ተጣርቶ እስኪጠናቀቅ ድረስም፣ እኔን ከዘመን ባንክ የቦርድ አባልነቴ በጊዚያዊነት እንዳገደኝ አሳወቀኝ።

    ብሔራዊ ባንክ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት የተጀመረውና አንድ ዓመት ያህል ፈጅቶ የተጠናቀቀው የኦዲት ምርመራ ሪፖርት ግን፣ በዘመን ባንክ ምስረታ ወቅት ያከናወንኩት ሥራ እንደተባለው የጥቅም ግጭት የሚያስከትል እንዳልነበር አረጋገጠ። የግል ገንዘቤን ወጪ አድርጌ ባንኩን ሳቋቁም፣ የግሌን ተጠቃሚነት ለማስጠበቅ ያከናወንኩትና በሕግ የሚያስጠይቀኝ ምንም አይነት ወንጀል እንዳልሠራሁ መሰከረ።

    ደቡብ ግሎባል ባንክ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 142 ሚልዮን ብር ማትረፉን አስታወቀ

    የኦዲት ሪፖርቱ በባንኩ ምስረታ ወቅት ተጠያቂ የሚያደርገኝ ህገወጥ ተግባር እንዳልፈጸምኩ ቢያረጋግጥልኝም፣ ብሄራዊ ባንክ ግን ከዘመን ባንክ አመራርነቴ በጊዚያዊነት እንድነሳ የጣለብኝን እገዳ ሊያነሳልኝ አልፈቀደም። የግለሰቦችን ውንጀላ መሰረት አድርጎ የወሰደብኝ እርምጃ አግባብነት የሌለው መሆኑን የሚያሳይና በአፋጣኝ ወደ ሥራዬ እንድመለስ የሚጠይቅና “የዘገየ ፍትህ እንደተነፈገ ይቆጠራል” የሚል ርዕስ ያለው ጽሁፍ አዘጋጅቼ በፎርቹን ጋዜጣ ላይ አወጣሁ። ጽሁፉ በጋዜጣው ላይ በወጣ በሁለተኛው ቀን ግን፣ ከዘመን ባንክ አመራርነት ብቻም ሳይሆን ከማንኛውም የአገሪቱ ባንክ የቦርድ አባልነት እስከመጨረሻው መታገዴን የሚገልጽ ደብዳቤ ከብሔራዊ ባንክ ደረሰኝ።

    40 ሚሊዮን ብር ያህል ገንዘብ ከግሌ ወጪ አድርጌ ባንኩን በማቋቋሜ፣ ወንጀል ሠራህ ተባልኩ። የሠራሁት ወንጀል መኖሩ በገለልተኛ አካል በኦዲት እንዲጣራ ተደረገ፣ የኦዲት ምርመራው ውጤት ወንጀል አለመሥራቴን አረጋገጠ። ብሔራዊ ባንክ ግን፣ ወንጀል አለመሥራቴን ቢያረጋግጥም እኔን ከመቅጣት ወደኋላ አላለም። ራሱ ከሳሽ ራሱ ፈራጅ የሆነውን፣ ባለሙሉ ስልጣኑን ብሔራዊ ባንክ በፍርድ ቤት ለመክሰስና መብትን ለማስከበር ህጉ አይፈቅድልኝም። ስለዚህ ብሔራዊ ባንክን ከስሼ መብቴን ለማስከበር ከመሞከር ይልቅ፣ የደረሰብኝን ግልጽ በደል ለመንግስት ማሳወቅ እንዳለብኝ ተሰማኝ። የተፈጠረውን ነገር በሙሉ በዝርዝር ገልጬ፣ አቤቱታዬን በደብዳቤ መልክ ለቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ላክሁ።

    ደብዳቤውን ከላክሁ ከቀናት በኋላ፣ በወቅቱ በጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ የመንግስት ተቋማት ድጋፍና ክትትል ሃላፊ የነበሩ ግለሰብ፣ በጉዳዩ ዙሪያ ሊያወያዩኝ እንደሚፈልጉ በመግለጽ ወደቢሯቸው አስጠሩኝ። ደስተኛ ሆኜ ወደቢሯቸው ሄድኩ። ጉዳዩን ከስር መሰረቱ አብራራሁላቸው፤ ዘመን ባንክን ለመመስረት ካሰብኩበት ጊዜ ጀምሮ ብሔራዊ ባንክ የፈጠረብኝን ችግሮች፣ ያደረሰብኝን በደልና በተደጋጋሚ ያስተላለፈብኝን ኢፍትሃዊ ውሳኔዎች በዝርዝር አቀረብኩላቸው። ከሰውዬው ጋር ሰዓታትን የፈጀ ውይይት ካደረግኩ በኋላ ግን፣ ፍትህን ፍለጋ ወደቢሯቸው መምጣቴ ከንቱ ድካም መሆኑን የሚያሳይ ምላሽ ሰጡኝ።

    “አቶ ኤርሚያስ በሆነው ነገር ሁሉ እናዝናለን። አንተን ለማጥቃት ተብሎ የተደረገ ነገር የለም። አንተ የምትሠራቸው ሥራዎች ለአገር ምን ያህል ጠቀሜታ እንዳላቸውና ፈር ቀዳጅ እንደሆኑ እናውቃለን። አንተ ተራ ነጋዴ እንዳልሆንክም እናውቃለን። ተቋማትን ነው የምትገነባው። ሥራዎችህን እና ጥረትህንም እንደግፋለን። ያው እንደምታውቀው ግን፤ ታዳጊ አገር ውስጥ ነው ያለነው። አንዳንዴ መሆን የሌለባቸው ነገሮች ይሆናሉ። በአንተ ላይ የተፈጸመው ነገር ትክክል እንዳልሆነ ይገባናል። ችግሩ በጊዜ ሂደት ይፈታል ብለን እናምናለን። ስሜትህ ሳይነካ፣ ጠንክረህ ሥራህን እንድትቀጥል ነው የምንፈልገው። ከዚህ ውጭ ግን፣ በብሔራዊ ባንክ ስልጣንና ሃላፊነት ውስጥ ጣልቃ ገብተን አስተያየት ለመስጠትም ሆነ ውሳኔውን ለማስቀየር ይከብደናል” የሚል ምላሽ ሰጡኝ።

    ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 658.7 ሚልዮን ብር ማትረፉን አስታወቀ

    ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍዬ ካቋቋምኩትና ወደትርፋማነት ካሸጋገርኩት ዘመን ባንክም ሆነ፣ አዳዲስ አሠራሮችን አስተዋውቄ ተጨባጭ ለውጥ ከፈጠርኩበት የአገሪቱ የባንክ ኢንዱስትሪ በዚህ መልኩ ያለአግባብ ተገፍቼ እንድወጣ ተደረግኩ። ከዘመን ባንክ አመራርነቴም ከባንኩ ዘርፍም እንድወጣ የተላለፈብኝ ውሳኔ ቢያሳዝነኝም፣ ሌላ የተሻለ ሥራ እንደምጀምርና ነባር ሥራዎችን አጠናክሬ እንደምቀጥል ስለማውቅ ብዙም ትኩረት አልሰጠሁትም – ፊቴን ወደሌሎች ሥራዎች አዞርኩ።

    በዘመን ባንክ መሥራችነቴ ማግኘት የሚገባኝን ጥቅም አለማግኘቴን ያስታወስኩት እንኳን፣ ባንኩ ሥራ በጀመረ በሶስተኛው ዓመት ላይ ነበር። በዘመን ባንክ የመመስረቻ ጽሁፍ አንቀጽ 7 ላይ በግልጽ እንደተቀመጠው፣ የባንኩ መሥራቾችና አደራጆች በመጀመሪያዎቹ 3 አመታት ባንኩ ከሚያገኘው የተጣራ ትርፍ 10 በመቶ የመሥራችነትና የአደራጅነት ጥቅም ያገኛሉ። እኔም የባንኩ መሥራች እንደመሆኔ ከሶስቱ አመታት ትርፍ ይህን ድርሻ ማግኘት ይገባኝ ነበር። በወቅቱ ዋነኛ ትኩረቴ የነበረው ባንኩን ወደላቀ ደረጃ ማሸጋገር እንጂ የግል ገንዘብ በማሳደድ ላይ ስላልነበር፣ ከመጀመሪያውም ሆነ ከሁለተኛው ዓመት የባንኩ ትርፍ ላይ የመሥራችነት ድርሻዬን ተከታትዬ አልተቀበልኩም። ሶስተኛው ዓመት ላይ ግን፣ ቢያንስ ያለፉትን ሁለት አመታት የመሥራችነት የትርፍ ድርሻ አስልቶ እንዲከፍለኝ ለባንኩ ጥያቄ አቀረብኩ።

    ዘመን ባንክ በ2002 ዓ/ም በ2003 ዓ/ም በድምሩ ብር 92,634,690.00 /ዘጠኛ ሁለት ሚሊዩን ስድስት መቶ ሰላሳ አራት ሺ ስድስት መቶ ዘጠና/ ማትረፉ በውጭ ኦዲተሮች በተረጋገጠው መሰረት፣ የዚህ ገንዘብ አስር በመቶ እና የውጭ ኦዲተሮች ባንኩ ማትረፉን ካረጋገጡበት ቀን ጀምሮ ከሚታሰብ ዘጠኝ መቶ ወለድ ጋር በድምሩ 10,359,105.69 /አስር ሚሊዩን ሶስት መቶ ሃምሳ ዘጠኝ ሺ አንድ መቶ አምስት ብር ከ69/100/ እንዲከፈለኝ ነበር የጠየቅኩት። የወቅቱ የዘመን ባንክ የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤና ቦርድ፣ ይህ ክፍያ እንዲፈጸምልኝ ወሰነ። የሚገርመው ነገር ግን፣ አሁንም የብሔራዊ ባንክ ኢፍትሃዊ በደል አልቀረልኝም። ብሔራዊ ባንክ ለኤርሚያስ ይከፈል ያላችሁትን ክፍያ አልቀበለውም፤ የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤና የቦርድ ውሳኔ የተላለፈበትን ቃለ-ጉባኤም አላጸድቅም አለ። ዘመን ባንክም ይህን የብሔራዊ ባንክ ውሳኔ መሰረት በማድረግ ክፍያውን እንደማይፈጽምልኝ አስታወቀኝ።

    እዚህ ላይ ዝም ማለት አልፈለግኩም። ዘመን ባንክን በፍርድ ቤት ለመክሰስና በመሥራችነቴ ማግኘት የሚገባኝን ክፍያ በሕግ ለማግኘት ወስኜ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ መሰረትኩ። የከፍተኘው ፍርድ ቤት ግን ግንቦት 3 ቀን 2009 ዓ/ም ክሱን ውድቅ አደረገው። ይህን ውሳኔ በመቃዎም ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ጠየቅኩ። ፍርድ ቤቱም የከፍተኛው ፍርድ ቤትን ውሳኔ በመሻር የሚገባኝ ገንዘብ እንዲከፈለኝ መጋቢት 18 ቀን 2009 ዓ/ም ወሰነልኝ። ዘመን ባንክ በዚህ ውሳኔ ላይ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሟል በማለት የሰበር አቤቱታ ለፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አቤቱታ ቢያቀርብም፣ ፍርድ ቤቱ ግን የተፈጸመ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የለም ሲል ውድቅ አደረገው።

    ዳሽን ባንክ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 1.14 ቢልዮን ብር ማትረፉን አስታወቀ

    በፍርዱ መሰረት ክፍያው እንዲፈጸምልኝ ለፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የአፈጻጸም አቤቱታ ባቀረብኩት መሰረት ባንኩ ክፍያውን እንዲፈጽም ሲጠየቅ ግን፣ ክፍያውን ሊፈጽምልኝ አልፈለገም። ይልቁንም የተለያዩ ምክንያቶችን እየደረደረና ሌሎች የጥቅም ግጭት ጥያቄዎችን እያነሳ፣ አዳዲስ ክርክሮችን መፍጠሩን ተያያዘው። አልፎ ተርፎም በእኔ ላይ አዲስ የወንጀል ክስ በመመስረት የተወሰነው ገንዘብ እንዲታገድና እንዳይከፈለኝ አደረገ። ባንኩ የመሰረተብኝ አዲሱ ክስ አሁንም ተጨማሪ የጥቅም ግጭት ነበረ የሚል ክስ ነበር። የቀረበብኝ ክስ የወንጀል ክስ መሆኑ ደግሞ እጅግ በጣም የሚገርምም የሚያሳዝንም ነበር።

    የራሴን ገንዘብ አውጥቼ፣ ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍዬ፣ ብዙ ፈተናዎችንና እንቅፋቶችን አልፌ ያቋቋምኩትና በአጭር ጊዜ ውስጥ ትርፋማ ያደረግኩት ዘመን ባንክ፣ ለውለታዬ እውቅና መስጠትና ስሜን በክብር ማውሳት ባይሆንለት የሚገባኝን ጥቅም ለመከልከል በእኔ ላይ ያልተገባ ክስ መመስረቱ በእጅጉ አሳዝኖኛል።

    የአገሪቱ የባንክ ኢንዱስትሪ ለዘመናት ከኖረበት ኋላቀር አሠራር ተላቅቆ በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ አሠራር እንዲዘረጋ በማስቻል ረገድ ፈር ቀዳጅ ሥራ ሰርቻለሁ። ለዘመን ባንክ እዚህ ደረጃ መድረስ ቁልፍ ሚና ተጫውቻለሁ። ገንዘቤን፣ እውቀቴንና ልምዴን ሳልሰስት በመገበር፣ ባንኩንም ባለአክሲዮኖችንም በተለየ ሁኔታ ትርፋማ አድርጊያለሁ። የባንኩ ኢንዱስትሪ ተዋንያንም ሆኑ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ውለታዬን ሲዘክሩት ይኖራሉ። የዘመን ባንክ ባለአክሲዮኖችም ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ለሠራሁት ሥራ እውቅና ሲሰጡኝ ኖረዋል። በቅርቡ አዲስ አበባ ውስጥ ያጋጠመኝ ድንገተኛ ነገር ለዚህ ጥሩ ማሳያ ሊሆን ይችላል።

    አንድ ማለዳ ከወዳጄ ጋር ወደነበረኝ ቀጠሮ እየሄድኩ እያለ፣ መንገድ ላይ አንድ የማላውቀው ሰው ስሜን ጠርቶ አስቆመኝ። ሰላምታ እንኳን ሳይሰጠኝ፣ በደስታ ስሜት ውስጥ ሆኖ አቀፈኝ። በግለሰቡ ድርጊት እየተገረምኩ እያለ፣ በስሜት ተውጦ ምክንያቱን ነገረኝ። ‘አቶ ኤርሚያስ… አንተ አታውቀኝም፤ ከአመታት በፊት ዘመን ባንክን ስታቋቁም ተገናኝተን ነበር። ስለምታቋቁመው ባንክ ማብራሪያ ስትሰጥ ሰምቼ፣ ባንኩ አትራፊ እንደሚሆን በመተማመን በ50 ሺህ ብር አክሲዮን ገዛሁ። ያኔ በ50ሺ ብር የገዛኋት የዘመን ባንክ አክሲዮን፣ ዛሬ ሚሊዬነር አድርጋኛለች… አንተ ባታውቀኝም፣ ባለሃብት ያደረግከኝ ባለውለታዬ ነህ! …’ እያለ ደጋግሞ አመሰገነኝ። ከዘመን ባንክ ያተረፍኩት ነገር፣ በሄድኩበት ሁሉ የሚያጋጥመኝ ይህን መሰሉ የሰዎች ፍቅርና አድናቆት ነው።

    አዋሽ ባንክ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 1.96 ቢልዮን ብር ማትረፉን አስታወቀ

    ለአመታት ብዙ ነገር የከፈልኩለት ዘመን ባንክ ግን፣ የከፈልኩለትን መስዋዕትነት ከንቱ ሊያስቀረውና የሚገባኝን ጥቅም ሊያሳጣኝ አሁንም ቆርጦ ቆሟል። ወርቅ ያበረከትኩለት ዘመን ባንክ፣ ጠጠር ሊመልስልኝ ደፍሯል። በቅንነት የፈጸምኩትን ተግባር የግል ጥቅሜን ለማሳደድ ያደረግኩት ዝርፊያ በማስመሰል፣ ያለሥራዬ የወንጀል ክስ መስርቶብኛል። ከአገር እንዳልወጣ ሳይቀር አሳግዶኛል። ፍርድ ቤት የዘመን ባንክን መሰረተቢስ ክስ ተቀብሎ የሚያስተላልፈው ውሳኔ ምንም ይሁን ምን፣ ዘመን ባንክ ግን ትልቅ ክህደት እንደፈጸመብኝ ህዝቡ ሊያውቀው ይገባል።

    ዘመን ባንክ የፈጸመብኝን ክህደት በአደባባይ ላወጣው የወሰንኩት፣ የሚገባኝን ጥቅም አለማግኘቴ አንገብግቦኝ አይደለም። የእኔ ጥያቄ የገንዘብ አይደለም – የፍትህ እንጂ። ህይወቴ በዘመን ባንክ 10 ሚሊዮን ብር የታጠረች አይደለችም። እጄ ላይ ያሉት ጅምር ሥራዎችና የሚያንቀሳቅሱት ገንዘብ፣ ከዘመን ባንክና ከነፈገኝ 10 ሚሊዮን ብር ጋር የሚወዳደሩ አይደሉም። ሰበብ እየፈለገ ሲያስረኝና ሲፈታኝ የኖረው መንግስት፣ ባልተሳተፍኩበት አስቂኝ የሙስና ወንጀል እጄን ይዞ ወደ ቂሊንጦ ላከኝ እንጂ፣ በረቀቀ ቴክኖሎጂ የሚከወንና ለአገሪቱ አዲስ የሆነ ግዙፍ ቢዝነስና ኢንቨስትመንት ወደ አገሪቱ ለማስገባት መንገድ ላይ ነኝ።

    በስተመጨረሻም፣ መላው ህዝብ ዘመን ባንክ በእኔ ላይ የሠራውን ግፍና በደል እንዲያውቅልኝ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ጥሪዬን እያስተላለፍኩ፤ ባንኩ የመሰረተብኝን ሃሰተኛ የወንጀል ክስ አንስቶ የሚገባኝን የመሥራችነት መብት እንዲያከብርልኝ ለማስቻል በማደርገው ጥረት ውስጥ ሁሉም ከጎኔ እንዲቆም እጠይቃለሁ!

    ከከበረ ሰላምታ ጋር።
    ኤርሚያስ ጠቅል አመልጋ
    (የዘመን ባንክ መሥራችና የቀድሞ የቦርድ ሊቀመንበር)
    የካቲት 7 ቀን 2011 ዓ.ም.
    ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት
    አዲስ አበባ

    ኤርሚያስ አመልጋ እና ዘመን ባንክ


    Anonymous
    Inactive

    በአሜሪካ ሀገር የሚኖሩ የዲያሥፖራ ማህበር አባላት ስልጠና ሰጡ።
    —–

    በውጪ አገራት ዩኒቨርስቲዎች የሚያስተምሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሙሁራንና ተመራማሪዎች /TASFA/ በሚል ተደራጅተው ስልጠና እየሰጡ ይገኛሉ።

    ከ 08-10/06/2011 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ በአዲስ አበባ ከተማ ኦሮሞ ባህል አደራሽ የኢፌዲሪ የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር፣ የውሀ መስኖና ኢነርጂ ሚንስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የህግ ባለሙያዎች እና ከኦሮሚያ ትምህርት፣ ሲቢል ሰርቪስ እና ከተለያዩ ቢሮዎች ለሚሰሩ አመራሮችና ባለሙያዎች የፕሮጀክት ማኔጅሜት ስልጠና በመስጠት ላይ ናቸው።

    ፕሮግራሙን የከፈቱት የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት የሳይንስና አካዳሚክ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀኔራል ዶክተር ኤባ ሚጃና እያንዳንዳችን ያስተማረችንን ድሀ አገራችንን አቅማችን በፈቀደው ብድሯን ለመመለስ ተረባርበን መስራት አለብን ብለዋል።

    የማህበሩ አመራሮችና አባላትም በበኩላቸው በራሳቸው ፈቃድና ወጭ መጥተው ያለባቸውን የሙያ ግዴታ ለመወጣት እየሰሩ ሲሆን ይሄን ተግባር በማስፍት ስልጠናው በቴክኖጂ ታግዞ ኦንላይን ትምህርት ጭምር እንደሚሰጥ 1000 ሰልጣኞች ለማሰልጠን ከመንግስት ጋር በመተባበር በታቀደው መሰረትየዛሬው ለ4ኛ ዙር 400 ሰልጣኞች ናቸው ቀጣይም በተመሳሳይ እንሰራለን ማለታቸውን የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዘግቧል፡፡

    ምንጭ፦ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በ”ለሁሉ” የተለያዩ የክፍያ ማዕከላት የውሃ፣ መብራትና ስልክ ክፍያ ለመፈጸም ሄደው መጉላላት እየገጠማቸው መሆኑን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪች ገለጹ።

    በአዲስ አበባ 34 የሚሆኑ የውሃ፣ የመብራት፣ የስልክና ሌሎች የአገልግሎት መስጫ “ለሁሉ” ማዕከላት ያሉ ቢሆንም ሰሞኑን በአገልግሎት ፈላጊዎች ወረፋ ተጨናንቀዋል። ተገልጋዮቹ የወርሃዊ ክፍያቸውን ለመፈጸም ረዥም ሰልፍ በመያዝ እንግልትና መስተጓጎል እየገጠማቸው መሆኑንም ገልፀዋል።

    የኢዜአ ጋዜጠኛም ከ”ለሁሉ” አገልግሎት መስጫ ማዕከላት መካከል በፒያሳ ጊዮርጊስ፣ በአራት ኪሎና ለገሃር አካባቢ በሚገኙ የክፍያ ማዕከላት ተዘዋውሮ ችግሩ መኖሩን ተመልክቷል።

    አራት ኪሎ በሚገኘው የክፍያ ማዕከል የተገኙት ወይዘሮ አስካለ ኃይሌ እንደሚሉት ከተወሰኑ ወራት ወዲህ በከተማዋ ባሉ ብዙ የክፍያ ማዕከላት ወረፋና መጉላላት ተባብሷል።

    VIDEO: The newly established i-Pro Mobile Assembly Company in Dessie struggling to get building

    በአራት ኪሎ የ”ለሁሉ” የክፍያ ማዕከል ክፍያ ለመፈጸም የተገኙት ወ/ሮ ኤልሳቤት ግርማም በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እንዳላቸው ነግረውናል።

    በአራዳ ክፍለ ከተማ ኢትዮ-ቴሌኮም ጊቢ ውስጥ በሚገኘው “ለሁሉ” የክፍያ ማዕከል ክፍያ ለመፈጸም የተገኙ ተገልጋዮችም በመስተጓጎላቸው ምሬታቸውን ገልፀውልናል።

    ከጉለሌ ክፍለ ከተማ የመጡት ወ/ሮ ብስኩት ይጥና እና አቶ መስፍን ተገነውም የውሃና መብራት ክፍያ ለመፈጸም ማልደው ቢገኙም አገልግሎቱን ማግኘት እንዳልቻሉ ገልፀውልናል።

    አገልግሎት የሚሰጡ ሰራተኞች በቁጥር ጥቂት መሆናቸውና “ሲስተም የለም በማለት”፣ ከፍተኛ መጨናነቅ እየተፈጠረ መሆኑንም ጭምር ተገልጋዮቹ ገልፀዋል።

    በመሆኑም “ክፍያውን የሚያስፈጽሙልን አካላት ከቴክኖሎጂ ጋር በተጣመረ ቅልጥፍና ሊያስተናግዱን ይገባል” በማለትም ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

    ካነጋገርናቸው ተገልጋዮች መካከል ለሦስት ቀናትና ከዚያ በላይ ክፍያ ለመፈጸም እንደተመላለሱ ጠቅሰው ለችግሩ የሚመለከተው አካል አፋጣኝ መፍትሄ እንዲያበጅላቸው የጠየቁም አሉ።

    በፒያሳ ጊዮርጊስ አካባቢ የሚገኘው “ለሁሉ” ማዕከል ኃላፊ ወ/ሮ ጽዮን ዮሃንስን እንዲሁም የአራት ኪሎ ክፍያ ማዕከል ሃላፊ ወ/ሮ ወይንሸት ገብረጻዲቅ ችግሩ መኖሩን አምነዋል። ወ/ሮ ጽዮን እንደሚሉት ችግሩ የተፈጠረው ሌላኛው የአራዳ የክፍያ ማዕከል ዝግ በመሆኑ ነው።

    እንደ ወ/ሮ ወይንሸት ገለፃ ህብረተሰቡ በጊዜ የመክፈል ልማድ ስለሌለው ወደ መጨረሻው ቀን ክፍያው በሚፈጽምበት ወቅት አንዲህ ያለው መጨናነቅ ይፈጠራል ብለዋል።

    ኢዜአ በ”ለሁሉ” የክፍያ መፈጸሚያ ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት ከኃላፊዎች ምላሽ ለማግኘት ቢሞክርም “ከቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ሚኒስቴር ፍቃድ ያስፈልጋል” በማለት መላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ለሁሉ ክፍያ


    Semonegna
    Keymaster

    ግንባታው በሦስት ዓመት የጊዜ ገደብ ውስጥ የሚጠናቀቀው የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ከኦጋዴን ኢላላና ካሉብ (ሶማሊ ክልል) ተነስቶ ጅቡቲ ወደብ የሚደርስ ሲሆን ጅቡቲ ላይ ነዳጁ ይቀነባበራል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ኢትዮጵያ ለምትገነባው የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧ ከጅቡቲ ጋር ስምምነት ተፈራረመች።

    በኢትዮጵያ እና ጅቡቲ መንግስታት መካከል የተፈረመው ስምምነት ኢትዮጵያ ለምትገነባው የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧ በጅቡቲ ምድር ለማቀነባባሪያ የሚሆን መሬት ለማግኘትና ጥበቃ ለማድረግ የሚያስችል ነው።

    ስምምነቱን የፈረሙት በኢትዮጵያ የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር ሳሙኤል ኡርካቶ (ዶ/ር) ና በጅቡቲ የነዳጅና ተፈጥሮ ሃብት ሚኒስትር ሚስተር ዮኒስ አሊ ጒዲ ናቸው።

    760 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ማስተላለፊያ ቧንቧ ግንባታው 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር የሚፈጅ ሲሆን 700 ኪሎ ሜትር በኢትዮጵያ፣ 60 ኪሎ ሜትሩ ደግሞ በጅቡቲ ምድር የሚያልፍ ነው።

    ◌ ALSO: Ethiopia is ready to use Red Sea Ports of Assab and Massawa of Eritrea

    ግንባታው በሦስት ዓመት የጊዜ ገደብ ውስጥ የሚጠናቀቀው የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ከኦጋዴን ኢላላና ካሉብ (ሶማሊ ክልል) ተነስቶ ጅቡቲ ወደብ የሚደርስ ሲሆን ጅቡቲ ላይ ነዳጁ ይቀነባበራል።

    የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትሩ ዶ/ር ሳሙኤል ኡርካቶ ስምምነቱ የሁለቱን አገራት የረጅም ጊዜ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ግንኙነት እንደሚያጠናክረው ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እየገነባችው ያለው የተፈጥሮ ሃብት መጠቀሚያ መሠረተ ልማት የአገራቱን የጋራ ተጠቃሚነት የሚያጠናክር ነው ብለዋል። በከፍተኛ ድርድር ውሳኔ ያገኘው ይህ ስምምነት ዓለም አቀፍ መስፈርት ያሟላ መሆኑንም ዶ/ር ሳሙኤል አክለዋል።

    የጅቡቲው የነዳጅና ተፈጥሮ ሃብት ሚኒስትር በበኩላቸው ስምምነቱ የሁለቱን ወንድማማች አገራት የጋራ ተጠቃሚነት ስለሚያጎለብት ጅቡቲ ጥበቃውን ታጠናክራለች ነው ያሉት። የመሠረተ ልማት ግንባታው በጅቡቲ በማለፉ ከምታገኘው ጥቅም ባሻገር በርካታ ዜጎቿን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ገልጸዋል።

    የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧውን መቀመጫውን ሆንግ ኮንግ ከተማ ያደረገው ያቻይናው GCL-Poly ኩባንያ እንደሚገነባው ተጠቁሟል። GCL-Poly ኩባንያ የተቋቋመው እ.ኤ.አ በ1996 ሲሆን፥ በተለያዩ የኃይል ማመንጫ ግንባታዎች ላይ የተሰማራው ጎልደን ኮንኮርድ ሆልዲንግስ ሊሚትድ (Golden Concord Group Limited) የተባለው ግዙፍ ድርጅት ቅርንጫፍ (subsidiary) ነው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    [caption id="attachment_9717" align="aligncenter" width="600"]የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ PHOTO: Ethiopian Broadcasting Corporation[/caption]


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– ኢትዮ ቴሌኮም 980 ሺህ ብር የሚያወጣ የአምቡላንስ ድጋፍ ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አበረከተ። ድርጅቱ ሠራተኞቹን በማስተባበር አሁን ያበረከተውን አምቡላንስ ጨምሮ በተለያዩ ሰብዓዊ ተግባራት ድጋፍ ለመስጠት ከማኅበሩ ጋር በትብብር እንደሚሠራ አስታውቋል።

    የካቲት 4 ቀን 2011 ዓ.ም. በማኅበሩ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተካሄደው ርክክብ ሥነ ስርዓት ላይ የተገኙት አዲሱ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ዋና ፀሀፊ ዶ/ር መሸሻ ሸዋረጋ፣ ኢትዮ ቴሌኮም ላደረገው ድጋፍ ያላቸውን ምስጋና ገልጸው፥ ሌሎች ተቋማትም ይህንን አርአያ እንዲከተሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

    በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰብዓዊ ዕርዳታ ፈላጊ ወገኖች መኖራቸውንና እነዚህን ተደራሽ ለማድረግ ለስድስት ወር ብቻ 1.5 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የተናገሩት ዶ/ር መሸሻ፥ በዚህ ረገድ ያለውን ክፍተት ለመሙላት የማኅበሩ የበላይ ጠባቂና የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፕሬዚዳንት አስተባባሪነት የሚመራ ኮሚቴ በማቋቋም ለሰብዓዊ እርዳታ የሚውል ገንዘብ ለማሰባሰብ በዝግጅት ላይ እንገኛለን ብለዋል።

    NEWS: Ethio Telecom and Ethiopian Electric Power to cooperate in sharing transmission lines

    የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ት ፍሬህይወት ታምሩ በበኩላቸው፣ ሰብዓዊነት ትልቅ ተግባርና ኃላፊነት በመሆኑ የዚህ ዓላማ አጋር በመሆናችን ደስታ ይሰማናል ብለዋል። የተቋሙ ሠራተኞችም በየወሩ ከደሞዛቸው ከሚያደርጉት የአባልነት መዋጮ ባሻገር በበጎ ፈቃደኝነት በዓመት ሁለቴ የደም ልገሳ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። በሀገራችን ያለውን የሰብዓዊ እርዳታ ፍላጎት ማቃለል የምንችለው ስንተባበር በመሆኑ ተቋማት ማኅበራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ያሉት ወ/ት ፍሬህይወት ተቋማቸው ከማኅበሩ ጋር ተባብሮ በመሥራት በቀጣይም መሰል ድጋፎችን ማድረግ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

    የማኅበሩ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቦርድ አባልና የረጅም ዓመታት የቀይ መስቀል ቤተሰብ የሆኑት አርቲስት ፋንቱ ማንዶዬ፣ የኪነ ጥበብ ባለሞያዎች በሰብዓዊ ተግባር ላይ በመሰማራት የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

    ኢትዮ ቴሌኮም ከ20 ዓመት በፊት በ1000 ብር የድርጅት አባልነት መዋጮ ጀምሮ በየዓመቱ በማሳደግ ከ2008 ዓ.ም. ጀምሮ በዓመት ለማኅበሩ 100 ሺ ብር ድጋፍ የሚያደርግ ሲሆን ከ15000 በላይ ሰራተኞቹ ደግሞ የቀይ መስቀል መደበኛ አባል በመሆን በወር ከ30 ሺ ብር በላይ ድጋፍ ያደርጋሉ። በተጨማሪም የተቋሙ ሠራተኞች ማኅበር እንደተቋም አባል በመሆን በየዓመቱ የ50 ሺህ ብር ድጋፍ ያደርጋል።

    የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ከሚሰጣቸው ሰብዓዊ አገልግሎቶች መካከል ነፃ የ24 ሰዓት የአምቡላንስ አገልግሎት አንዱ ሲሆን በዓመት በአማካኝ በአንድ አምቡላንስ ለ3600 ሰዎች አገልግሎት ይሰጣል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ኢትዮ ቴሌኮም ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የአምቡላንስ ድጋፍ አበረከተ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትና የውጪ ምንዛሬ እጥረት ለሀገር በቀል የመድኃኒት እና የሕክምና መገልገያ አምራቾች እውነተኛ ፈተና መሆን አለመሆናቸው በገለልተኛ አካል ሊጠና ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት ኤጀንሲ ባለድርሻ አካላት ተናገሩ።

    ጥር 24 ቀን 2011 ዓ.ም ከሀገር ውስጥ አምራቾች በተደረገው ውይይት የ6 ወር የመድኃኒት አቅርቦት አፈፃፀም 25% መሆኑን ተከትሎ ለአቅርቦቱ ዝቅተኛ አፈፃፀም በተደጋጋሚ በምክንያትነት የሚሰጡት የውጭ ምንዛሪ እጥረትና የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ በገለልተኛ አካል ተጠንቶ ድጋፍ የሚያስፈልገውን በመደገፍ የሚያጭበረብረውን በማጣራት እርምጃ ሊወሰድበት ይገባል ሲሉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ገልፀዋል።

    ኤጀንሲው ለሀገር ውስጥ አምራቾች በቅድሚያ ክፍያ እንዲሁም 25 በመቶ ጨረታ ላይ እንዲወዳደሩ እንደሚደግፉ የተጠቀሱት አስተያየት ሰጪዎቹ አሁንም አምራቾች መድኃኒቶችን በበቂ መጠን ጥራት ማቅረብ አለመቻላቸው አጠራጣሪ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

    ◌ News: Humanwell Healthcare Group inaugurates Humanwell Pharmaceutical Ethiopia PLC in Chacha town

    እንደአስተያት ሰጪዎች ገለጻ ሀገር በቀል አምራቾች ኤጀንሲው የሚሰጣቸው የቅድሚያ ክፍያ ሒሳብ በአግባቡ ቃላቸውን ለመተግበር እያዋሉት መሆኑ ወይም ሌላ ዓላማ መዋሉ ሊጠና ይገባል ብለዋል። አክለውም የሚሰጠውን ገንዘብ ለሌላ የግል ንግድ እየተጠቀሙበት መሆኑን ጥርጣሬ እንዳላቸው ገልጸዋል።

    በተያያዘ ዜና የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች በአዳማ ከተማ የግማሽ ዓመት አቅድ አፈጻጸም ላይ እንዳሉት ሀገር በቀል የመድኃኒት አምራቾች ኤጀንሲው በሚያቀርበው ገንዝብ ለግል አቅራቢዎች ትርፍ ለማሳደድ እንደሚያውሉት መረጃ አለ ሲሉ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪም የሚደረገው ድጋፍ በአግባቡ የመያጠቀሙበት ከሆነ በሂደት እየለዩ እርምጃ ለወሰድ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

    ከዚሁ ውይይት በተጨማሪ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት ኤጀንሲ የጀመረውን ለውጥ ለማስቀጠል አቅርቦቱን የበለጠ ለማሻሻል ብቻውን መስራቱ ውጤታማ ሊያደርገው እንደማይችል የኤጀንሲው የግዥ ትንበያና ገበያ ጥናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብይ ክፍሎም አብራርተው የሀገር ውስጥ አምራቾቹ ሊያስቡበት እንደሚገባም አቶ አብይ አክለው ገልፀዋል።

    ◌ News: SanSheng Pharmaceutical PLC inaugurated in the Eastern Industry Zone in Dukem, Ethiopia

    የአገር ውስጥ አምራቾች አፈፃፀማቸውን መፈተሽ እንዳለባቸውና አፈፃፀማቸው ዝቅ ባለ ቁጥር በመድኃኒት እጦት የሚያልፈውን የሰው ሕይወት ሊያስቡ እንደሚገባ የመድኃኒትና የህክምና መሣርያዎች ግዢ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ጎይቶም ጊጋር ገልፀዋል።

    የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ሣሙኤል ኃይሉ በበኩላቸው በአሁኑ ሠዓት የመድኃኒት እጥረት እንደ ቀልድ የሚታይ ጉዳይ አይደለም ብለዋል።

    አቅርቦቱ ዝቅ እንዲል ካደረጉ ምክንያቶች መካከል የውጭ ምንዛሬና የመብራት መቆራረጥ በዋናነት በውይይቱ የተጠቀሱ ሲሆን ኤጀንሲው ይህን ለማስተካከል አፈፃፀማቸውን ለመለካት የሚያስችል ነጥቦችን የያዘ ረቂቅ ሰነድ (KPI) ቀርቦ የጋራ ማድረግ ተችሏል።

    በመጨረሻም ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ ከብሔራዊ ባንክ፣ የኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት መገኘታቸው በቀጣይ ችግሩን በመቅረፍ የሕብረተሠቡን የመድኃኒት ፍላጎት ለማሟላት ያስችላል ብለዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት ኤጀንሲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 

    የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት ኤጀንሲ


    Anonymous
    Inactive

    የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር በአዲስ አበባ የተለያዩ የጤና ተቋማትን ጎበኙ
    —–

    ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ እያደረገች ያለችው እንቅስቃሴ ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ መሻሻሎችን እያሳየ መምጣቱ ተገለፀ፡፡

    የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም በዛሬው እለት አዲስ አበባ የሚገኘውን የጃን ሜዳ ጤና ጣቢያ እና የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታልን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ በጃን ሜዳ ጤና ጣቢያ በቤተሰብ ጤና ቡድን በጤና ጣቢያው ባለሙያዎች ቤት ለቤት እየተሰጡ ያሉ የጤና አገልግሎቶችንም በተገልጋዮቹ ቤተሰቦች ቤት በመገኘት ጎብኝተዋል፡፡

    የጃንሜዳ ጤና ጣቢያ ዝቅተኛ ኢኮኖሚ ላላቸው ግለሰቦች ቤታቸው ድረስ በመሄድ በአይነቱ አዲስ የሆነ የህክምና ግልጋሎት የሚሰጥ ሲሆን ታካሚዎቹ ተጨማሪ ህክምና ካስፈለጋቸው ወደ ጤና ጣቢያው ሪፈር እንደሚያደርጋቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

    በቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ጉብኝታቸው መደሰታቸውን የገለፁት ዶ/ር ቴዎድሮስ ሆስፒታሉ የልብ ቀዶ ህክምና መጀመሩና በመመረዝ ህክምና ዙሪያ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ የሆስፒታሉን እመርታ እንደሚያሳይ ተናግረዋል፡፡

    “ጤና ለሁሉም” በሚለው የዓለም ጤና ድርጅት መርህ መሰረት የዓለም ጤና ድርጅት ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ዋናው ዳይሬክተሩ የተናገሩ ሲሆን የሀገሪቷ ከፍተኛ የጤና አመራሮች ለጤናው ዘርፍ ስርዓት መጠናከር የሰጡትን ትኩረት አድንቀዋል፡፡

    ምንጭ፦ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    “በርቱ! ባየሁት ነገር ተደስቻለሁ… የሥራ ፍላጎት ተነሳሽነት ለለውጥ ወሳኝ መሆኑን ከጴጥሮስ መረዳት እንችላለን” – የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ገብረየሱስ 

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ገብረየሱስ የካቲት 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተገኘተው የሥራ እንቅስቃሴን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

    በቆይታቸውም የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልና የቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ በጋራ ያስገነቡትን የልብ ህክምና ማዕከል፣ በሀገሪቱ ብቸኛና የመጀመሪያ የሆነውን የተመረዙ ሰዎች የሚታከሙበት የቶክሲኮሎጂ ህክምና ማዕከል እንዲሁም የእናቶችና ህጻናት የህክምና ከፍልን ዋና ዳይሬክተሩ ጎብኝተዋል።

    በሆስፒታሉ ፈጣን እድገት ተደስቻለሁ ያሉት ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የልብ ህክምና አገልግሎት መስጠት መጀመሩና በሀገሪቱ ካለው የህክምና እጥረት አኳያ ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልጸው ብዙም ትኩረት ያልተሰጠበት የመመረዝ ህክምና በሆስፒታሉ መሰጠቱም ይበል የሚያሰኝ ነው ብለዋል።

    ቪዲዮ፦ የኢትዮጵያዊያን-አሜሪካዊያን ዶክተሮች ቡድን እያስገነባ ያለው ግዙፉ ዓለምአቀፋዊ ሆስፒታል በአዲስ አበባ

    ሆስፒታሉ የሰሳንባ ነቀርሳ (ቲቢ) ህክምና ብቻ ይሰጥ እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር ቴዎድሮስ በአሁኑ ሰዓት አጠቃላይ መሠረታዊ የሆስፒታል አገልግሎቶችን መስጠት መጀመሩና የተወሰኑ የህክምና አገልግሎቶች ላይም የበለጠ ስፔሻላይዝድ ለማድረግ መሥራቱ በጣም እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል።

    ከዚህ ሌላም የሆስፒታሉ ሰራተኞች የሥራ ተነሳሽነትም በጣም እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል። ለሆስፒታሉ ፈጣን ዕድገትም ሁሉም የሆስፒታሉ ሠራተኞች ዋና ተዋናይ መሆናቸውን እንዳዩ ገልጸው በዚህም የሥራ ፍላጎት መኖር ለለውጥ ወሳኝ መሆኑን ከጴጥሮስ መረዳት እንችላለን ብለዋል።

    የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በዚሁ ዕለት የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን ከመጎብኘታቸው በተጨማሪም ከየኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዴሪ) የጤና ሚኒስትር አሚር አማን (ዶ/ር) እንዲሁም ከኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ጋር ተገናኝትው በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።

    ከሰኔ 24 ቀን 2009 ዓ.ም. ቀን ጀምሮ ዋና መቀመጫው ጄነቭ፣ ስዊዘርላንድ የሆነውን የዓለም ጤና ድርጅትን (WHO) በዋና ዳይረክተርነት የሚመሩት ኢትዮጵያዊው ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከዚህ ስልጣናቸው በፊት ከ ከኅዳር 20 ቀን 2005 ዓ.ም. እስከ ጥቅምት 22 ቀን 2009 ዓ.ም. ድረስ የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ከጥቅምት 2 ቀን 1998ዓ.ም. እስከ ኅዳር 19 ቀን 2005 ዓ.ም. ደግሞ የኢፌዴሪ የጤና ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።

    ምንጭ፦ የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

     

    የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (EIAR) – የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የአርሶ አደሩን እንዲሁም አርብቶና ከፊል አርብቶ አደሩን የአገሪቱ ማህበረሰብ ኑሮ የተሻለ ለማድረግ ብሎም የግብርናው ዘርፍ ዘላቂ እድገት እንዲያስመዘግብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።

    ኢንስቲትዮቱ የገጠሩን ማህበረሰብ ምርታማነት ከማሣደግም ባለፈ በከተማ ዙሪያ የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ዘመናዊ የግብርና ዘዴዎችን በማስተዋወቅ አምራች እንዲሆኑ ለማስቻል እየሠራ ይገኛል ። በዚህም በምርምር የሚያወጣቸውን ከአካባቢ ስነ ምህዳር እንዲሁም አየር ንብረት ጋር ተስማሚ የሆኑ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለከተማ አርሶና አርብቶ አደሮች የማስተዋወቅና የማስፋፋት ሥራ ሲሠራ ቆይቷል። ተቋሙ ይህንን እንቅስቃሴ አጀንዳው አድርጎ መሥራት የጀመረው በ2009ዓ.ም ሲሆን በኢንስቲትዩቱ የቴክኖሎጂ ስርፀትና ኮሜርሻላይዜሽን ምርምር ዳይሬክቶሬትም ይህንኑ ተግባር እያስተባበረ ይገኛል።

    ቪዲዮ፦ እየተገነቡ ያሉት የግብርና ማቀነባበሪያ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለሀገሪቱ የእርሻ ሴክተር እና ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አስተዋጽኦ

    ከከተማ ግብርና የሚገኝ ምርት የምግብ ስርዓትን በማሳደግ ጤናማ ማህበረሰብ ለመገንባት አይነተኛ አስተዋጽኦ አለው። ለዚህም እንደ ማሳያ ማህበረሰቡ በአነስተኛ ቦታ ዘመናዊ የግብርና ዘዴዎችን በመጠቀም ለጤና ጠቃሚ የሆኑ የግብርና ምርቶችን በማምረት ለለት ተእለት ፍጆታው ማዋል ሲጀምር የምግብ ደህንነቱ ከመጠበቁም በተጨማሪ በምርቱ ጥራት ላይ የሚኖረው እምነት ይጨምራል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም እንደ ትራንስፖርት፣ የዘመናዊ እህል ማከማቻ ቦታ እጥረት እንዲሁም የገበያ ችግርና የመሣሠሉ በተለያዩ ምክንያቶች የሚከሰቱ የድህረ ምርት ብክነት መንስኤዎችን ለመቀነስ ያስችላል። የከተማው ማህበረሰብ የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝ በማድረግ ጤናማ ማህበረሰብ መፍጠር ያስችላል፤ በከተሞች የሚኖረው የምግብ ዋስትና ችግር ከእናቶችና ህፃናት ጤና ከፍተኛ የሆነ ትስስር ያለው በመሆኑ የስርዓተ-ምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ አንጻር ከፍተኛ ፋይዳ አለው።

    ኢንስቲትዩቱ ለከተማ ግብርና ልማት ሥራ በሚረዱ ቴክኖሎጂዎች ላይ ምርምር እንደሚሠራና ከኢንስቲትዩቱ የወጡ ከነባር የዶሮ ዝርያዎች የተሻለ የምርት ልዩነት የሚሠጡ የዶሮ ዝሪያዎች፤ ከአንድ የወት ላም በቀን ውስጥ ሊገኝ የሚችለውን የወተት መጠን ማሣደግ የቻሉ የተሻሻሉ የላም ዝርያዎች ፤ እንዲሁም የተለያዩ የሠብል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ቴክኖሎጂዎችም ወደ ተጠቃሚ ተሸጋግረው ማህበረሰቡ ውጤታማ ምርት ማምረት የሚያስችለውን አሠራር በመዘርጋት የምግብ ደህንነትን ለማስጠበቅ እየሠራ ይገኛል ። በዚህም የማህበረሰቡ አካል የሆኑ በርካታ ሴቶችና ወጣቶች ተጠቃሚ የሚሆኑባቸው የሥራ እድሎችን ይፈጥራል። ይህንንም እንደ መነሻ በመውሠድ ተቋሙ እነዚህን የከተማ ግብርና ሥራዎች ለማስፋፋትና በምርምር ያወጣቸውን የሰብልና እንሠሣት ቴክኖሎጂዎች በስፋት ለተጠቃሚዎች ለማዳረስ ከፍተኛ እንቅስቀሴዎች ሲያካሂድ ቆይቷል።

    ቪዲዮ፦ የተሻሻሉ የአቦካዶ ምርቶች ለገበሬዎች መልካም ምርት እየሰጡ ነው

    ከኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በምርምር የሚወጡ የሰብል፣ እንስሳትና ተፈጥሮ ሀብት ቴክኖሎጂዎች በመሠረታዊነት የገጠሩን ህዝብ ያማከሉ ቢሆኑም ቴክኖሎጂዎቹ ውጤታማ በመሆን ከፍተኛ ምርት መስጠት ከሚያስችላቸው አየር ንብረትና ሌሎች ተያያዥ ግብአቶች ጋር ተቀራራቢ ስነምህዳር ባላቸው ከተማዎች እንዲሁም ከተማ ቀመስ ለሆኑ አካባቢዎች በቀላሉ እንዲላመዱ በማድረግ የሚታሠበውን ውጤት ማምጣት ይቻላል ። በተለይም የተሻሻሉ የአትክልትና ፍራፍሬ ቴክኖሎጂዎች፣ የእንስሳት መኖ ቴክኖሎጂዎች፣ የመዓዛማና መድሀኒት ሠብሎች፣ የዶሮ ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም ከተፈጥሮ ማዳበሪያና አካባቢ ጥበቃ ጋር የተያያዙ ምክረ ሃሳቦችን ለከተማ ግብርናም በቀላል ወጪ እንዲሁም አነስተኛ ቦታ ተግባራዊ መሆን የሚችሉ ናቸው።

    የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ከኦሮሚያ ክልል ፊንፊኔ ልዩ ዞን በረህ ወረዳና በዚሁ ወረዳ የተለያዩ ማኅበራዊ እንቅስቃሴዎችን እያከናወነ የሚገኘው የልማትና የአቅም ግንባታ ማዕከል (Center for Development and Capacity Building – CDCB) ፕሮጀክት ጋር በመተባበር የአካባበቢውን ማህበረሰብ በማስተባበር አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን የማስተዋወቅና የማስፋት እንዲሁም የቴክኖሎጂ ዘር ብዜት ተግባራትን የማከናወን ኃላፊነት ወስዶ ሲሠራ ቆይቷል። በዚህም በበርህ ወረዳ ሮጌ ቀበሌ የሚገኙ ነዋሪዎችን በክላስተር በማቀናጀት የሰንዴ ቴክኖሎጂ የዘር ብዜት ሥራ ተካሂዷል። በተጨማሪም በአካባቢው የአርሶ አደር ማሳ ላይ የሽብምራ ቴክኖሎጂ ሠርቶ ማሳያ በማከናወን በሌሎች የአካባቢው ማኅበረሰቦች እንዲጎበኝ ተደርጓል። በተመሳሳይም በዚሁ ወረዳ ሞጎሮ ቀበሌ የሚኖሩ የአካባቢው አርሶአደሮችን በክላስተር በማደራጀት የስንዴ ዘር ብዜት ማከናወን የቻሉ ሲሆን፣ በቀበሌው የአርሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከል የተከናወኑ የተለያዩ የግብርና ቴክኖሎጂ ሙከራዎችም ተካሂደዋል። የሰንዴና የጤፍ ሠርቶ ማሳያዎችን፣ የአርሶ አደር ማሰልጠኛ እንዲሁም የዶሮ ምግብ ማቀነባበርያ ማዕከላትም በወረዳው በሚገኝ ለገቦሎ ቀበሌ የተከናወኑ ተግባራት ናቸው።

    በግብርናው ዘረፍ የሚሠሩ የተለያዩ የመንግስት ፓሊሲ አውጪዎችን ጨምሮ የግብርና ተመራማሪዎች፣ የዞንና የወረዳ የግብርና ሃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ የአካባቢው አርሶ አደሮች እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታቸውን አካላት በማሳተፍ በከተማ ግብርና ዙሪያ የተሠሩትን ውጤታማ የሆኑ የቴክኖሎጂ ሠርቶ ማሳያና የዘር ብዜት ሥራዎች በመጎብኘትና ውይይት በማድረግ ውጤታቸውን በጋራ ለመገምገምና ግብረመልስ ለማሰባሰብ እንዲሁም በኢንስቲትዩቱ፣ በወረዳውና በCDCB በቅንጅት የተሠሩትን የቴክኖሎጂ ማስተዋወቅና ማስፋት ሥራዎችን በማሳየትና ውይይት በማድረግ ቋሚ የሆነ ትስስር ለመፍጠር የሚረዳ የመስክ ቀን ህዳር 16 ቀን 2011 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል ፊንፊኔ ልዩ ዞን በረህ ወረዳ ሮጌ፣ ሞጎሮና ለገቦሎ ቀበሌዎች ተካሂዷል።

    VIDEO: Making Ethiopians not only have food per se but nutritious and quality food – Bless Agri Food Lab

    የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በኦሮሚያ ክልል ፊንፊኔ ልዩ ዞን የከተማ አካባቢ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ማዕከል በማድረግ በ2010/11 መኸር ወቅት የቴክኖሎጂ አቅርቦት፣ ማስተዋወቅ እና አቅም ግንባታ ስልጠናዎች ሲያከናውን ቆይቷል። እነዚህ ተግባራትም ከምርምር ማዕከል የሙከራ ጣቢያዎች ጀምሮ እስከ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚዎች ድረስ በስፋት በማሳተፍ የተከናወኑ ሲሆን አላማውም አዳዲስና የተሻሻሉ ዝርያዎችን ለተጠቃሚዎች በማቅረብ፣ የመነሻ ቴክኖሎጂ ብዜት ሥራዎችን በማካሄድንና የአቅም ግንባታ ሥራዎችን በማከናወንን በአገሪቱ ውጤታማ የሆነ የከተማ ግብርና ማስፋፋት ነው። ኢንስትቲዩቱ በዘርፉ ውጤታማ ከሆኑ ሀገራት ቴክኖሎጂ፣ እውቀትና ልምድ በመውሰድ ለአገሪቱ ስነምህዳር ተስማሚና ኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ የሚችሉና ለከተማ ግብርና አመቺ የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን በመለየት የማላመድ ሥራ በመሥራት ጥቅም ላይ እያዋለ ይገኛል። ለውጤታማነቱም ተቋማዊ ድጋፍ በማድረግ፣ ለተጠቃሚዎች ስልጠና በመስጠት፣ ከስልጠናም በኋላ ተገቢው የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በሥራ ላይ እንዲውል ክትትልና ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም ከሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር የገበያ ትስስር በመፍጠር የበኩሉን አስተዋጽኦ እየተወጣ ይገኛል።

    ሆኖም የከተማ ግብርና ተግባራት ሂደት ከዚህ በተሻለ ፍጥነት ወደፊት እንዲራመድ ለማስቻል ዘርፉ በቴክኖሎጂና እውቀት ሊታገዝ የሚገባው ሲሆን ተግባራቱም በከተማ ውስጥ ባሉ አነስተኛ ቦታዎችና ተፈጥሮ ሃብት ሊተገበሩ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል ይላሉ በዘርፉ ለረጅም ጊዜያት ያገለገሉ የግብርና ባለሞያዎች። ከዚህ በተጨማሪም የህብረተሰብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በኢኮኖሚ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን መሠረት ያደረገ ሊሆን እንደሚገባም ይጠቁማሉ። የተጠቃሚዎችን አቅም ሊገነቡ የሚችሉ የልምድ ልውውጥና የግንዛቤ መፍጠር ሥራን ማከናወን ለሥራው ዘለቄታዊነት መፍትሄ ሊሆን እንደሚገባም ይጠቅሳሉ።

    በተለይም በዝቅተኛ የእለት ገቢ ራሣቸውን የሚያስተዳድሩ በከተማ አካባቢ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጉዳዩ በቀጥታ በሚመለከታቸው አካላት ቀና ድጋፍ በአነስተኛ ቦታ ማምረትና ህይወታቸውን መቀየር የሚያስችላቸውን መንገድ መፍጠር፤ የተጀመሩትንም ሥራዎች አጠናክሮ መቀጠል ያስፈልጋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት (EIAR) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት


Viewing 15 results - 361 through 375 (of 495 total)