Search Results for 'አዲስ አበባ'

Home Forums Search Search Results for 'አዲስ አበባ'

Viewing 15 results - 376 through 390 (of 495 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    ሃገራዊውን የግብር ንቅናቄ በደቡብ ክልል ለማስቀጠል በአዲስ አበባ ከተማ የሩጫ ውድድር ሊካሄድ ነው
    —–

    አዲስ አበባን ጨምሮ በአማራና በትግራይ ክልሎች የተጀመረውን የግብር ንቅናቄ በማስቀጠል በአዲስ አበባ ከተማ የሩጫ ውድድር ሊያካሂድ መሆኑን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

    የገቢዎች ሚኒስትር ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግላጫ እንዳስታወቁት÷ “ግብር ለሃገሬ “ በሚል መሪ ቃል የካቲት 10 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ የሩጫ ውድድር እንደሚካሄድ ገልጸዋል፡፡

    ሚኒስትሯ የግብር ንቅናቄው በሀገር አቀፍ ደረጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው የተናገሩት፡፡

    ሁሉም የሚሳተፍበት የእምዬን ለእምዬ በሚል መርህ የስዕልና የሙዚቃ ድግስ የካቲት 17 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚካሄድም ተናግረዋል፡፡

    ሚኒስትሯ በሀገሪቱ ግብር መክፈል ከነበረባቸው ዜጎች መካከል 60 በመቶ ያህሉ ብቻ እንደሚከፍሉ ገልጸዋል፡፡

    ደረሰኝ ከመስጠትና ከመቀበል ጋር በተያያዘም እስካሁን የግንዛቤ ችግሮች መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡

    በሚኒስቴሩ በግብር ማጭበርበርና ስወራዎች ላይ በተደረገ ክትትል ከ2 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷልም ነው ያሉት።

    ሃገሪቱ ከግብር ስወራና ማጭበርበር ጋር በተያያዘ 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ማጣቷንም አንስተዋል።

    ኤፍ.ቢ.ሲ

    Anonymous
    Inactive

    በአዲስ አበባ እያጋጠመ ባለው የትራንስፖርት እጥረት መቸገራቸውን ነዋሪዎች ገለጹ
    —–

    በአዲስ አበባ እያጋጠመ ባለው የትራንስፖርት እጥረት ሳቢያ በዕለት ተእለት እንቅስቃሴቸው ላይ ችግር እየፈጠረባቸው መሆኑን ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የትራንስፖርት ተጠቃሚዎች ተናገሩ።

    የአዲሰ አበባ መንገድ ትራንስፖርት ባለስልጣን በበኩሉ ችግሩ የተከሰተው የትራንስፖርት ተጠቃሚው ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ አየጨመረ በመሆኑ ለማቃለል እየሰራሁ ነው ብሏል።

    ነዋሪዎቹ እንደሚሉት መንግስት የትራንስፖርት ችግሩን ለማቃለል በተለያዩ ጊዜያት የተማሪዎች ሰርቪስና ሌሎችንም ተሽከርካሪዎች ሲያስገባና ለተጠቃሚዎች አገልግሎት ሲሰጥ ይስተዋላል።

    ይሁንና ችግሩ ሊፈታ እንዳልቻለና ተማሪዎች አሁንም ድረስ ከሰራተኛው ጋር እየተጋፉ ትራንስፖርትን ለመጠቀም እየተገደዱ መሆናቸውንም ነው የሚገልጹት።

    የትራንስፖርት ተጠቃሚ ወጣት ፍሬወይኒ መኮንን እብደተናገረችው”ትራንስፖርቱና ህዝቡ ተመጣጣኝ አይደለም ህዝቡ በየወቅቱ እየጨመረ ነው የመጣው በአሁኑ ወቅት በጠዋት ብትወጪ ስልፉ ዞሮ ነው የምታይው በጣም ረጅም ነው ትራንስፖርቱ በቂ ነው ለማት በጣም አስቸጋሪ ነው፤ የስራ ስዓት ይረፍዳል።”

    የታክሲ ተራ አስከባሪ ወጣት ይውዳኖስ አለሙ በአስተያየቱ”ያሉት ኮድ 1 ታክሲዎች በቂ ናቸው ብዬ አላምንም ተጨማሪ የተሻለ ለህብረተሰቡ አገልግሎት ቢቀርብ” ጥሩ ነው ብሏል፡፡

    የአዲሰ አበባ መንገድ ትራንስፖርት ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት ዘለቀ እንድገለጹት ለተለያዩ ጉዳዮች ወደ አዲሰ አበባ የሚመጣው ህዝብቁጥር ከነዋሪው ጋር ተደምሮ ከፍተኛ በመሆኑ ጫናው እየጨመረ መጥቷል።

    ችግሩን ለቃለል በዚህ በጀት ዓመት 137 አዳዲስ አወቶብሶች በግዥ ገብተው ከፍተኛ የትራንስፖርት እጥረት ባለባቸው አከባቢዎች ይሰማራሉ ብለዋል።

    ህብረተሰቡ አማራጭ ትራንስፖረቶችን አብዘቶ የመጠቀም ልማድ ብዙም እንዳልሆነ የገለጹት ዋና ስራ አስኪያጁ በቀጣይ አመራጮችን በመጠቀም ችግሩ እንዲቃለል የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

    የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን በማጎ እና ኦሞ ብሔራዊ ፓርኮች ላይ ያሉ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ለመፍታት በጥር 28 ቀን የተጀመረው ውይይት መድረክ ጥር 29 ቀን 2011 ዓ.ም. ከቀኑ 7:00 ሰዓት ላይ ተጠናቋል።

    በውይይቱ ወቅት ፓርኮቹ ከሚያዋስኗቸው ዞኖችና ወረዳዎች የተወከሉ የአካባቢው ሽማግሌዎች እና የጽህፈት ቤት ኃላፊዎች በስፋት ሐሳባቸውን አንሸራሽረዋል።

    ኦሞ ኩራዝ የስኳር ፋብሪካ፣ አርብቶ አደሩ እና የጥበቃ ቦታዎቹ በተቀናጀ መልኩ ችግሩን ለመፍታት መሥራት እንደሚኖርባቸው ተገልጧል። የመንገድ፣ መብራት፣ ትምህርት፣ ውሃ እና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን በቀጠናው በማስፋፋት የአካባቢውን ማኅበረሰብ ልማት ተጠቃሚነት በማስፋት በፓርኩ ላይ የሚደርስ ጫና መቀነስ እንደሚገባው የአካባቢው ኗሪዎች አሳወቀዋል።

    ቪዲዮ፦ የአሜሪካ መንግስት ለታሪካዊው የአባ ጅፋር ቤተ መንግስት እድሳት የሚሆን 335,000 ዶላር ልገሳ አደረገ

    የአገር ሽማግሌዎች እንደገለጡት፤ ላለፉት ሀምሳ ዓመታት ከፓርኮቹ ጋር በሰመረ መልኩ ኖረናል። ፓርኩ ዛሬ የመጣ ጉዳይ አይደለም የፓርኩ ህልውና የእኛ ህልውና እንደሆነ እንገነዘባለን። የስኳር ፕሮጀክቱም ቢሆን በተቀናጀ እና በተጠና መልኩ ከተተገበረ ጠቀሜታ እንዳለው እናምናለን ብለዋል። ሆኖም ግን የቅንጅት አሠራር ላይ በተለይም የፓርክ አስተዳደር እና ስኳር ፕሮጀክት በሚጠበቀው ልክ ባለመቀናጀታቸው ችግሮች መፈጠራቸውን እና ሁኔታውም በዚህ መልኩ የሚቀጥል ከሆነ አደጋው የከፋ እንደሚሆን አስረድተዋል።

    ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተዋረድ ኃላፊነቱን መወጣት ይኖርበታል። ከፌዴራል እስከ ቀበሌ ድረስ የሚጠበቅባቸውን መወጣት አለባቸው ሲሉ በአካባቢው ኗሪዎች በኩል የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ ቃል ገብተዋል። ተሳታፊዎቹ አጽንኦት ሰጥተው የገለጡት ጉዳይ፤ በየመድኩ የሚደረጉ ይህንን መሰል ውይይቶች የጋራ መግባባት ላይ ለመድረስ ፋይዳቸው የላቀ ቢሆንም በሚፈለገው ልክ ወደ ሥራ መውረድ ካልተቻለ በራሱ መድረክ ውጤታማ አያደርገንም የሚለው ዋናው ነው።

    በዚህ ጉዳይ ዙሪያ በርካታ ድረኮች መካሔዳቸውን በመጠቆም ከውሳኔው በኋላ ወደ መሬት ሊወርድ እንደሚገባ አሳስበዋል። ከዱር እንስሳት ቲንክ ታንክ ቡድን እና ከሌሎች ተቋማት የመጡ ባለሙያዎችም ከሁለቱ ፓርኮች ባሻገር የታማ ጥብቅ ስፍራ (Tama Wildlife Reserve) ከፍተኛ የብዝሃ ሕይወት ሀብት ያለው በመሆኑ ትኩረት ተሰጥቶት ጥበቃ ሊደረግለት እንደሚገባ ገልጠዋል።

    በማጎ ብሔራዊ ፓርክ ውስጥ በቅርብ ጊዜ የተከሰተውን የጥበቃና ቁጥጥር ሠራተኛ ግድያም አስመልክቶ የሚመለከታቸው አካላት ህገወጦችን ለፍርድ ማቅረብ እንደሚኖርባቸው ተመልከቷል።

    በተጨማሪም በውይይቱ የተደረሰበትን ውሳኔ ተከታትሎ በማስፈጸም ውጤታማ መሆን እንደሚኖርበት የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል። በቀጣይም በመስክ ሥራዎች የተገኙ ውጤቶች ላይ በተከታታይ ግምገማ ማካሄድ እንዳለበት ተገልጧል።

    በመጨረሻም ስኳር ኮርፖሬሽን ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እና ከክልሉ ጋር በስፋት ተወያይተው የጋራ መግባባት ላይ መድረስ እንደሚገባ ስምምነት ላይ ተደርሷል። መድረኩ የውይይቱን አጠቃላይ ሐሳብ የያዘ ባለስምንት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተቋጭቷል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን (EWCA) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን


    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት በቅርቡ ዋና ካምፓሱን በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፍቼ ከተማ በምድረግ ከተመሠረተው ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ጋር አብሮ ለመሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መለሰ ማርዮ እና የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገናናው ጎንፌ ጥር 8 ቀን 2011 ዓ.ም. በኢንስቲትዩቱ አዳራሽ እውቀትን ለማሸጋገር፣ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በጋራ ለማከናወን የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል።

    የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መለሰ ማርዮ በስምምነት ፊርማው ላይ ባደረጉት ንግግር እንዳስታወቁት የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና የምርምር ተቋማት ጋር አብሮ ሊያሠራው የሚችል ስምምነቶችን በመፈራረም የተለያዩ ተግባራትን ለማከናወን መቻሉን ገልጸዋል። ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በዱረም ስንዴ ላይ በተሠራው ሥራ ከፍተኛ ምርት የሚሰጥና ድርቅን መቋቋም የሚችል ውጤት መገኝቱን፤ ከጎንደር ዩኒቨረሲቲ ጋር በመተባበር በደን ልማት ላይ እየተሠራ መሆኑን እና ከዲላ ዩኒቨረሲቲ ጋርም በመተባበር ለምርምርና ለቱሪስት መስህብ የሚውል የቦታኒክ ጋርደን ግንባታ ሥራ ከተከናወኑ ተግባራት መካከል የሚጠቀሱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

    VIDEO: Ethiopia: After mandatory preparations, Selale University accepts incoming students

    የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገናናው ጎንፌ በበኩላቸው ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በቅርብ ጊዜ ሥራ የጀመረ፣ እየሰፋ የሚሂድና ለግብርና እና የአካባቢ ጥበቃ ልዩ ትኩረት የሚሰጥ ነው። የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ካለው መልካአ ምድራዊ አቀማመጡ ጋር በተያያዘም በእንስሳት ዝርያ አጠባበቅ በተለይም የተለያዩ ዝርያዎችን በማዳቀል ለአዲስ አበባ ከተማ 50 በመቶ የሆነውን የወተት ምርት የሚያቀርበው የሰላሌ አርሶ አደርን ተጠቃሚ ለማድረግ ከኢንስቲትዩቱ ጋር አብረው ለመሥራት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

    ዶ/ር ገናናው አክለውም ስምምነቱ የወረቀት ላይ ስምምነት ብቻ እንዳይሆን ለማድረግና የብዝሀ ሕይወት ጥበቃ ሥራዎችን ለሕብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ከመማር ማስተማር ሥራው ጎን ለጎን የአካባቢውን ማሕበረሰብ ተጠቃሚ የማድረግ ሥራ ለማከናወን ዩኒቨርሲቲው መዘጋጀቱን ገለጸዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦  

    የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የሰጣቸው ምሁራን በመማር ማስተማሩ፣ በጥናትና ምርምር፣ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አገልግሎት እንዲሁም በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት በዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሊጅስሌሽን መሰረት የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ ስለተወጡ ነው።

    አዲስ አበባ (አ.አ.ዩ)– በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሚመለከታቸው የትምህርት ክፍሎች ተመርመሮ፣ በየኮሌጆች አካዳሚክ ጉባዔዎች ተፈትሾ፣ አጥጋቢ በሆነ መልኩ ተገመግሞ በዩኒቨርሲቲው ሴኔት ታይቶ እና ይሁንታ አግኝቶ የቀረበለትን መረጃ የተመለከተው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ጥር 26 ቀን 2011 ዓ.ም. የዶ/ር ሂሩት ወልደማርያምን፣ የዶ/ር ተፈሪ ገድፍን፣ የዶ/ር ምሩፅ ግደይን፣ የዶ/ር ሃጎስ አሸናፊን፣ የዶ/ር መረራ ጉዲናን እና የዶ/ር ጌታቸው አሰፋን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አፅድቋል። ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው 6 መምህራን አጭር መግለጫ እንደሚከተለው ነው።

    1. ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም የመጀመርያ፣ ሁለተኛ እና የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በቋንቋ ጥናት (Linguistics) ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል።

    ፕሮፌሰር ሂሩት በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ6 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 42 ነጥብ አስመዝገበዋል። በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሂዩማኒቲስ፣ የቋንቋዎች ጥናት፣ የጆርናሊዝምና የኮሚዩኒኬሽን ኮሌጅ የቋንቋ ጥናት ትምህርት ክፍል ባልደረባ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

    2. ፕሮፌሰር ተፈሪ ገድፍ የመጀመርያና ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ዲግሪያቸውን በፋርማሲ (Pharmacy) ትምህርት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በፋርማሲ ትምህርት በጀርመን ከማርቲን ሉተር ሐለ-ቪተንበርግ ዩኒቨርሲቲ (Martin Luther University Halle-Wittenberg) አግኝተዋል።

    ፕሮፌሰር ተፈሪ በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ20 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 104.56 ነጥብ አስመዝገበዋል። በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ፕሮፌሰር ተፈሪ ገድፍ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሳይንስ ኮሌጅ የፋርማሲ ትምህርት ክፍል መምህር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

    ቪዲዮ፦ ኢትዮጵያ ውስጥ ትምህርት ቤቶች አካባቢ የሚከፈቱ የጫት እና የሁካ ቤቶች ተማሪዎች ለሱሰኝነት እየዳረጓቸው ነው

    3. ፕሮፌሰር ምሩፅ ግደይ የመጀመርያ ዲግሪያቸውን በባዮሎጂ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በባዮዳይቨርሲቲ (Biodiversity) ከ ከስዊድን የእርሻ ዩኒቨርሲቲ (Swedish University of Agricultural Sciences)፣ እንዲሁም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ቦታኒካል ሳይንስ (Botanical Science) ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል።

    ፕሮፌሰር ምሩፅ በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ18 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 56 ነጥብ አስመዝገበዋል። በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ፕሮፌሰር ምሩፅ ግደይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአክሊሉ ለማ የፓቶባዮሎጂ ኢንስቲትዩት (Aklilu Lemma Institute of Pathobiology) በእንዶድና ሌሎች የመድሃኒት ዕጽዋት የምርምር ማዕከል (Endod and Other Medicinal Plants Research Unit) ባልደረባ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

    የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ

    4. ፕሮፌሰር ሃጎስ አሸናፊ የእንስሳት ህክምና ዲግሪያቸውንና የሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በቤልጄም ከሉቨን የካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ (Catholic University of Leuven) አግኝተዋል።

    ፕሮፌሰር ሃጎስ በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ24 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 94.06 ነጥብ አስመዝገበዋል። በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ፕሮፌሰር ሃጎስ አሸናፊ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በእንስሳት ህክምና እና ግብርና ኮሌጅ የፓቶሎጂና ፓራሲቶሎጂ (Pathology and Parasitology) ትምህርት ክፍል መምህር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

    5. ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና የመጀመርያ ዲግሪያቸውን በፖለቲካ ሳይንስ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከአሜሪካን ዩኒቨርሲቲ ኢን ካይሮ (The American University in Cairo)፣ እንዲሁም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በፖለቲካ ሳይንስ ከኤራስመስ ዩኒቨርሲቲ ሮተርዳም ኢንስቲትዩት ኦፍ ሶሻል ስተዲስ (Erasmus University Rotterdam – Institute of Social Studies) አግኝተዋል።

    ፕሮፌሰር መረራ በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ12 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 37.25 ነጥብ አስመዝገበዋል። በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሶሻል ሳይንስ ኮሌጅ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለማአቀፍ ግንኙነት (Political Science and International Relations) ትምህርት ክፍል መምህር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

    6. ፕሮፌሰር ጌታቸው አሰፋ የህክምና ዲግሪያቸውን (Doctor of Medicine) ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የስፔሻሊቲ ዲግሪያቸውን በራዲዮሎጂ (Radiology) ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ እንዲሁም የሰብ-ስፔሻሊቲ ዲግሪያቸውን በኒሮራዲዮሎጂ (Neuroradiology) በኦስትሪያ ከሜዲካል ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቭየና (Medical University of Vienna) አግኝተዋል።

    ፕሮፌሰር ጌታቸው በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ17 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 75.25 ነጥብ አስመዝገበዋል። በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ፕሮፌሰር ጌታቸው አሰፋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሳይንስ ኮሌጅ የዲያጎነስቲክ ራዲዮሎጂ (Diagnostic Radiology) ትምህርት ክፍል መምህር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

    አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የሚሰጣቸው ምሁራን በመማር ማስተማሩ፣ በጥናትና ምርምር፣ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አገልግሎት እንዲሁም በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት በዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሊጅስሌሽን መሰረት የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ ለተወጡ እና ለዓለም የዕውቀት ስርጸት መዳበር ስኬታማ አበርክቶ ላደረጉ ነው።

    ምንጭ፦ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ


    Anonymous
    Inactive

    የጊዳቦ ግድብና መስኖ ልማት ፕሮጀክት ተመረቀ
    —–
    ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የጊዳቦ ግድብና መስኖ ልማት ፕሮጀክትን መርቀው ከፈቱ።

    በ2002 ዓ.ም ግንባታው የተጀመረው የጊዳቦ ግድብና መስኖ ልማት ፕሮጀክት በሁለት ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል ቢባልም ከተባለለት ስድስት ዓመት ዘግይቶ ዛሬ ተመርቋል።

    ከአዲስ አበባ በ365 ኪሎ ሜትር ርቀት፣ ከዲላ ከተማ አቅራቢያ ጊዳቦ በተሰኘ የደቡብና የኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ ቦታ ላይ ነው ግድቡ የተገነባው።

    በሁለት ዓመታት ውስጥ ግንባታው እንደሚጠናቀቅ ታቅዶና በ258 ሚሊዮን ብር በጀት የተጀመረው የጊዳቦ ግድብና መስኖ ልማት ፕሮጀክት በ1 ነጥብ 26 ቢሊዮን ብር ተጠናቋል።

    ግድቡ ከ63 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር በላይ ውኃ የመያዝ አቅም ሲኖረው 13 ነጥብ 5 ሺህ ሄክታር መሬት በመስኖ ለማልማት ያስችላልም ተብሏል።

    በግድቡ ግራና ቀኝ ዋና ዋና የውኃ ቦዮች መገንባታቸውና በአሁኑ ወቅትም ከ1 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ያካለለ ውኃ በግድቡ መጠራቀሙም ታውቋል።

    በምርቃቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድና የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጅነር ስለሺ በቀለን ጨምሮ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳ፣ የደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ፣ የሁለቱ አጎራባች ክልሎች ነዋሪዎች፣ አባ ገዳዎችና ሌሎችም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

    የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ዋልታ)– ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ ድርጅቶች የሚመረቱ የታሸጉ ውሃዎች ላይ ሁነኛ የሆነ የጥራት ችግር እንዳለ ተገለፀ።

    በአገሪቱ ለመጠጥ ውሃ የሚውሉት የታሸጉ ውሃዎች ላይ በሚታየው የጥራት መጓደል ምክንያትም በኅብረተሰቡ ላይ አሉታዊ የጤና ችግር መንስዔ ከመሆናቸው ባሻገር አገሪቱ ማግኘት ያለባትን ገቢ አለማግኘቷም ተገልጿል።

    የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ በውሃ ምርቶች ላይ የሚስተዋሉትን ችግሮችና የጥራት ማስጠበቅ ሥራዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ጥር 23 ቀን 2011 ዓ.ም. አካሄዷል።

    ቪዲዮ፦ የታሸጉ ውሃዎች በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ የመጣው ፍላጎት እና የውሃዎቹ ያልተመጣጠነ ዋጋ

    በመጠጥ ውሃ የፕላስቲክ ማሻጊያዎቹ ክዳን ላይ የሚለጠፉትና ከፍተኛ የውጭ ምናዛሬን የሚጠይቁ ግብዓቶች ተመሳስለው በሀገር ውስጥ የሚሠሩ በመሆኑ የማሸጊያዎችም የምርት ጥራት ላይ ችግር እየተስተዋለ በመሆኑ ይህን ለማስቀረት እየተሠራ ይገኛል።

    በሀገሪቱ እየተስፋፉ ያሉ የውሃ ማምረቻ ተቋማት ንፁ ውሃን በማቅረብ እና ኢኮኖሚውን ከመደገፍ አንጻር አበረታታች ሥራ ቢሠሩም አሁንም ግን ዘርፉ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚንስትር ዴኤታ አቶ እሸቱ አስፋው ተናግረዋል።

    በርካታ በሀገሪቱ የሚኖሩ ኤምባሲዎችና የውጭ ኮሚኒቲ አካላት የታሸጉ ውሃዎችን ወደ አገር ውስጥ እያስገቡ በመሆኑ፤ በዘርፉ ያለውን የጥራት ችግር ያሳያል።

    የምርቶቹን የጥራት ደረጃ በማሻሻል ለውጭ ገበያ እንዲቀርቡ በማድረግ ሀገሪቱን ከዘርፉ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ለማሳደግ መሥራት እንደሚገባ ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል።

    የምርቶችን የአመራረት፣ የአስተሻሸግ፣፤ የማጓጓዝ እና የአቀማመጥ ሆነ ለገበያ በሚቀርቡበት ጊዜ ያለው አያያዝ ችግር ምርቶቹን በከፍተኛ ሁኔታ የጥራት ችግር እንዲጋለጡ ማድረጉን ሚኒስትር ዲኤታው አክለው ገልጸዋል።

    አሁን በሥራ ላይ የሚገኙ ከ 65 በላይ የታሸጉ ውሃ አምራቾች አለም አቀፉን የጥራት ደረጃ በጠበቀ መልኩ እንዲያመርቱ እየተሠራ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ ዳይሬክተር አቶ ይልማ መንግስቱ ተናግረዋል።

    ምንጭ፦ ዋልታ ሚዲያ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የታሸጉ ውሃዎች


    Anonymous
    Inactive

    በአዲስ አበባ በ2.5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የጤና ከተማ ሊገነባ ነው (ሪፖርተር ጋዜጣ)

    ቪዥን አፍሪካ ሆስፒታል የተባለው የግል ኩባንያ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በ2.5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የጤና ከተማ ሆስፒታል በአዲስ አበባ ሊገነባ ነው፡፡

    በሚቀጥለው ዓመት (ጥር 2012 ዓ.ም.) ይጀመራል የተባለው ይኸው የግንባታ ፕሮጀክት፣ በቦሌ ለሚ አይሲቲ ፓርክ በአንድ ሚሊዮን ስኩዌር መሬት ላይ የሚያርፍ ሲሆን፣ ለግንባታ የሚውለው ገንዘብ ከዓለም አቀፉ አበዳሪዎችም የሚገኝ መሆኑን የቪዥን አፍሪካ ሆስፒታል ኩባንያ ኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ቴዎድሮስ ታደሰ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

    እ.ኤ.አ. በ2028 ይጠናቀቃል የተባለው ይኸው ፕሮጀክት፣ ከሁለት ዓመት በፊት ጀምሮ ቅድመ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝና በዚህ ጊዜም በጣሊያን ዲዛይን ኩባንያ የተሠራው የሆስፒታሉ ሥነ ሕንፃ ዲዛይን መጠናቀቁንም ተናግረዋል፡፡

    የጤና ከተማ ሆስፒታሉ አምስት ሺሕ አልጋዎች ያሉትና በቀን እስከ ሰባት ሺሕ ተኝተውና በተመላላሽ ለማከም የሚያስችል ሆስፒታል፣ ሦስት ሺሕ ተማሪዎችን በአዳሪነት መያዝ የሚችል የሕክምና ትምህርት ቤት፣ የአፍሪካ የባህል ማዕከልና ሙዚየም፣ ለኤምባሲዎችና ለዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የሚያገለግሉ ቢሮዎች፣ ምግብ ማደራጃዎች፣ የገንዘብ ተቋማት፣ ባለአምስት ኮከብ ሆቴል፣ የስፖርትና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማዕከል፣ ቤተ መጻሕፍት፣ የገበያ ማዕከል፣ ተጨማሪ የጤና ማዕከላትና ማኅበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ይኖሩታል፡፡

    ሙሉውን ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ያንብቡ

    Semonegna
    Keymaster

    መቀዛቀዝ የታየበትን የህዝባዊ ተሣትፎ ለማነቃቃት የተለያዩ መድረኮችን በቀጣይነት እንደሚያዘጋጅ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሣትፎ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ አብርሃም ገልጸዋል።

    አዲስ አበባ (ዋልታ)– የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሣትፎ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ባለፉት 6 ወራት 484 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡን አስታውቋል።

    ጽህፈት ቤቱ በበጀት ዓመቱ እስከ አንድ ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ እየሠራ ሲሆን በቀጣይ የተጠናከረ አፈጻጸም ለማስመዝገብ እንደሚንቀሳቀስ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማኅበር እና የህዳሴው ግድብ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ባዘጋጁት ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጿል።

    መቀዛቀዝ የታየበትን የህዝባዊ ተሣትፎ ለማነቃቃት የተለያዩ መድረኮችን በቀጣይነት እንደሚያዘጋጅ የህዳሴው ግድብ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ አብርሃም ገልጸዋል።

    ቪዲዮ፦ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የግንባታ ድጋፍ ዙሪያ ከኢትዮጵያውያን የዳያስፖራ አባላት ጋር የተደረገው ውይይት

    ከዚሁ ጋር በተያያዘም ጥር 22 ቀን 2011 ዓ.ም. ከንቅናቄ መድረኮች አንዱ የሆነው ሁሉም የዳያስፖራ አካላት የሚገኙበት መድረክ በራስ ሆቴል መድረክ አዘጋጅቶ ከተለያዩ ሀገራት ከመጡ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት ጋር በቀጣይነት እና በተሻለ ሁኔታ ግድቡን ሊደግፉ በሚችሉበት መንገድ ላይ ውይይት አድርጓል።

    ዳያስፖራው ባለፉት ሰባት ዓመታት 46 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ማድረጉ የተገለጸ ሲሆን ሃገሪቱ ካላት ዲያስፖራ ቁጥር አንጻር ድጋፉ አነስተኛ መሆኑ ተጠቁሟል። በመሆኑም በተለይም በምዕራብ አውሮፓ የሚገኙ ዲያስፖራዎች የሚጠበቅባቸውን ያህል ድጋፍ ስላላደረጉ ትኩረት አድርጎ እንደሚሠራ የዳያስፖራ ማኅበሩ ዋና ዳይሬክተር አቶ አብርሃም ስዩም አስታውቋል።

    ለዚህም ዳያስፖራው ለህዳሴው ግድብ አዲስ የዳያስፖራ ተሳትፎ ንቅናቄ ለመፍጠር እና በዳያስፖራው ዘንድ በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ ያለውን ብዥታ ለማጥራት መድረክ ፈጥሮ ውይይት ማድረግ አስፈላጊ እንደነበርና፣ የራስ ሆቴሉ ውይይትም የዚሁ ዋነኛ አካል እንደነበር ተገልጿል። በተመሳሳይ ሁኔታም በዕለቱ የተለያዩ የህዝብ አደረጃጀቶች የሚሳተፉበት የንቅናቄ መድረክ በካፒታል ሆቴል ተካሂዶ ነበር።

    ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከሁለት ዓመት በኋላ ኃይል ማመንጨት እንደሚጀምር የተገለጸ ሲሆን ከአራት ዓመት በኋላ ተገንብቶ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።

    ምንጭ፦ ዋልታ ሚዲያ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦  

    ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የአሜሪካ ኢምባሲ 2ኛውን ‹‹SolveIT›› የተሰኘ ሀገር አቀፍ የፈጠራ ውድድርን የኢዲስ አበባ ከተማን በይፋ አስጀመረ። ኢምባሲው ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ ከጃፓን ዓለማቀፋዊ ኮኦፐሬቲቭ ኤጀንሲ (Japan International Cooperation Agency – JICA) እና ከአይኮግ ላብስ (iCog Labs) ጋር በመተባር ነው ውድድሩን ይፋ ያደረገው።

    ፕሮጀክቱ በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ 15 ከተሞች የሚካሄድ ሲሆን ቴክኖሎጂ ነክ የፈጠራ ሥራዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው።
    ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂ ነክ የፈጠራ ሰራዎች ያሏቸው ወጣቶች የሚሳተፉበት ይህ ውድድር የፈጠራ ባላሙያዎቹ ሥራዎቻቸውን ሊያዳብር የሚችል ስልጠና በየከተሞቹ ይሰጣቸዋል።

    SolveIT ሀገር አቀፍ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውድድርን የአሜሪካ ኢምባሲና የጃፓን ዓለማቀፋዊ ኮኦፐሬቲቭ ኤጀንሲ ፕሮጀክቱን በገንዘብ ይደግፉታል። ተመሳሳይ ፕሮግራሞች በየከተሞቹ የሚዘጋጁ ሲሆን የተመረጡ ችግር ፈቺ የፈጠራ ሥራዎች ለሽልማት ይበቃሉ ተብሏል።

    VIDEO: These two Ethiopian students are working to launch their own rocket – the future Eng. Kitaw Ejigu

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኢኖቬሽን ልማትና ምርምርና ዘርፍ ዳይሬክተር ጀነራል ካህሊድ አህመድ (ዶ/ር) በፕሮጀክቱ ተመርጠው የመጡ የፈጠራ ሥራዎች ገበያውን እንዲቀላቀሉ ሚኒስቴሩ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

    ተጨማሪ ስልጠና የሚያስፈልጋቸውን በቴክኖሎጂ ማበልፀጊያ ማዕከላት በማስገባትና የሥራ ማስጀመሪያ ገንዘብ በመደጎም ጭምር ድጋፍ እንደሚያደረግ አረጋግጠዋል።

    የአሜሪካ ኤምባሲ በኢትዮጵያ በዋናነት ስፖንሰር የሚያደርገው SolveIT ውድድር በወጣት ኢትዮጵያውያን ዘንድ የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የኢንጂነሪንግ፣ የአርት እና የሒሳብ (STEAM) በወጣቶች ዘንድ ይበልጥ እንዲጎለብቱ የሚያበረታታ ውድድር ሲሆን ፥ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ለሚኖሩበት ህብረተሰብ፣ ብሎም ለሀገራቸው ችግር ፈቺ የሆኑ የቴክኖሎጂ፣ የሶፍትዌርና የሀርድዌር ፈጠራዎችን በመፍጠር እንዲሳተፉ ያደርጋል።

    ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 28 ዓመት የሆነ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በሚኖሩበት ከተማ ሆነው ህብረተሰባቸው የሚያጋጥመውን ችግር ሊፈታ የሚፍል ፈጠራ ለመፍጠር ለዘጠኝ ወራት ያህል ጊዜ ተሰጥቷቸው ይሠራሉ። በዚህም ጊዜ ከአወዳዳሪዎች በተመደቡላቸው ባለሙያዎች ስልጠና ይሰጣቸዋል። ፈጠራዎቻቸው ከሞባይ አፕ (mobile app) ጀምሮ እስከ ከፍ ያለ የኮምፒዩተር ሶፍትዌር ሊሆን ይችላል። በከተሞቻቸው (በክሎቻቸው) አሸናፊ የሆኑ ተወዳዳሪዎች ከፍ ወዳለው (የፌደራል) ውድድር ያልፋሉ፤ በዚያም ለሳምንት ያህል በዳኞች ና በከፈተኛ ኤክስፐሮች እየተዳኙ ይወዳደራሉ። በዚህም የመጨረሻዎቹ አሸናፊዎች ይለያሉ።

    በአሁኑ ጊዜ ተወዳዳሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል። የበለጠ መረጃ የአይኮግ ላብስ (iCog Labs) ድረ ገጽ ላይ ማግኘት ሲችሉ (እዚህ ጋር ይጫኑ)፥ መመዝገቢያውን ደግሞ እዚህ ጋር ያገኙታል (Register)።

    ምንጭ፦ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    SolveIT ውድድር


    Semonegna
    Keymaster

    ባለቤት አልባ ውሾችን ከማስወገዱ ተግባር ጎን ለጎን በከተማዋ ያሉ ውሾችን የቤት ለቤት ምዝገባ በማከናወን የባለቤትነት ማረጋገጫ በየወረዳው እየተሰጠ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገልጿል። በዚህም፣ ህብረተሰቡ ለሚመለከተው አካል እያሳወቀ ችግሩን በጋራ መቅረፍ እንደሚገባም ጥሪ ቀርቧል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 7ሺህ 8 መቶ ባለቤት አልባ ውሾችን ማስወገዱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።

    በከተማ አስተዳድሩ አስተዳደር የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ የከተማ ግብርና ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አሰግድ ኃ/ጊዮርጊስ ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) እንደተናገሩት በከተማዋ እየተበራከቱ የመጡ ባለቤት አልባ ውሾችን ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ለማስወገድ በጋራ እየሠራ ነው። ባለቤት አልባ ውሾቹ በህብረተሰቡ ላይ የሚደርሱትን የጤና ስጋት ችግር ለመቅረፍ እየሠራ መሆኑንም አስተባባሪው አቶ አሰግድ ገልፀዋል።

    በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ ከከተማው ውበትና መናፈሻ፣ የጽዳት አስተዳደር፣ ጤና ቢሮ እንዲሁም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እስካሁን 7ሺህ 8 መቶ ውሾችን ማስወገድ መቻሉንም ተመልክቷል። በየቦታው ተንጠባጥበው የሚገኙ ባለቤት የሌላቸው ውሾችን የማስወገዱ ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉንም አቶ አሰግድ ተናግረዋል።

    ቪዲዮ፦ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተለያዩ የቆሻሻ መጣያ የነበሩ ቦታዎችን በማጽዳትና አረንጓዴ በማድረግ፣ እንዲሁም የተለያዩ አትክልቶችን አልምቶ በመሸጥ ራሳቸውን የሚያስተዳድሩ ወጣቶች

    በተጨማም በከተማዋ ያሉ ውሾችን የቤት ለቤት ምዝገባ በማከናወን የባለቤትነት ማረጋገጫ በየወረዳው እየተሰጠ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገልጿል። በዚህም፣ ህብረተሰቡ ለሚመለከተው አካል እያሳወቀ ችግሩን በጋራ መቅረፍ እንደሚገባም ጥሪ ቀርቧል።

    በአንፃሩ ባለቤት አልባ ውሾችን በማስወገዱ ሂደት ከአንድ ወር በላይ ጊዜ የመድሃኒት አቅርቦት እጥረት እንደገጠመውም አስተዳደሩ ገልጿል። በዚህም፣ በፌዴራል ደረጃ የመድሃኒት ፈንድ መድሃኒቱን እስኪያቀርብ እየተጠበቀ መሆኑንና አቅርቦቱ እንደተሟላ ባለቤት አልባ ውጮችን የማስውገዱ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል ሲል ዘግቧል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕረሽ ድርጅት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ባለቤት አልባ ውሾች - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– ግዙፉ የመኪና አምራች የሆነው የጀርመኑ ኩባንያ ቮልስዋገን በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ፈረመ። ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር አበባ አበባየሁ እና ከሰሃራ በታች የኩባንያው የአፍሪካ ቀጣና ሥራ አስፈጻሚ ቶማስ ሻፈር ተፈራርመዋል። በስምምነቱ መሠረትም ኩባንያው የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ መክፈት፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎችን ማቅረብ፣ የስልጠና ማዕከል መክፈት እና ተጓዳኝ ሥራዎችን ይሠራል።

    በስምምነቱ ላይ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ላይ የሚገኙት የጀርመኑ ፕሬዚዳንት ፍራንክ ዋልተር ስታይንማየር እና የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ተገኝተዋል።

    ቮልስዋገን ኩባንያ ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ አገራት መካከል ኢትዮጵያን የማስፋፊያ ማዕከሉ አድርጎ ሲመርጥ፣ ከኩባንያው ጋር የመግባቢያ ስምምነት በመፈረም ከሰሃራ በታች ካሉ አገራት ኢትዮጵያ ሦስተኛዋ አገር (ከጋና እና ናይጄሪያ ቀጥሎ) ሆናለች።

    ◌ VIDEO: የጀርመኑ ግዙፍ የመኪና አምራች ኩባንያ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰፊ ኢንቨስትመንት ለመጀመር እየተንቀሳቀሰ ነው

    ኩባንያው ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ለመሥራት መስማማቱ በቀጥታ የእሴት ሰንሰለት የተቀናጀ የአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ ክላስተር ለመፍጠር ወሳኝ ምዕራፍ ይከፍታል ነው የተባለው።

    ኮሚሽነር አበበ አበባየሁ በፊርማ ሥነ-ስርዓቱ ላይ እንዳሉት መንግሥት አገሪቷን ቀዳሚ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ በቁርጠኝነት እየተንቀሳቀሰ ነው።

    ”በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው መስክ ልዩ ክላስተር እንዲመሠረት መንግሥት ያለሰለሰ ጥረት ያደርጋል” ያሉት ኮሚሽነሩ ይህን ተግባራዊ ለማድረግ ቮልስዋገንን ጨምሮ ፍላጎት ካላቸው ተቋማት ጋር በቅንጅት ለመሥራት ‘ዝግጁ ነው’ ብለዋል።

    ◌ VIDEO: German companies including Volkswagen and Siemens embarking to invest in Ethiopia

    የኩባንያው የአፍሪካ ቀጣና ሥራ አስፈጻሚ ቶማስ ሻፈር በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንግሥት ለአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው እድገት ትኩረት መስጠቱ ‘የሚደነቅ ነው’ ሲሉ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ ቶማስ ሻፈር ‘ኢትዮጵያ ፈጣን እድገት በማስመዝገብ ላይ ያለች እና በሕዝብ ብዛትም ከ አህሪካ አገራት በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠች በመሆኗ፥ ከሰሃራ በታች ባሉ ሀገራት ለመስፋፋት በምናደርገው ጥረት ኢትዮጵያን ሁነኛ ተመራጭ አገር አድርገናታል፤ በተጨማሪም ቮልስዋገን ኩባንያ ሀገሪቱ ያላትን የስትራቴጂ ጥቅም ከግምት በማስገባት በ አውቶሞቲቭ ዘርፍ ከፍትኛ እድገት እንድታስመዘግብ ይተጋል’ ብለዋል።

    ከዚህ ጋር በተያያዘ የጀርመን የቢዝነስ ልኡካን ቡድን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሥራ ሃላፊዎችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት መስክ በሚሰማሩበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።

    ሲመንስ የተሰኘው በግዙግነቱ ከአውሮፓ ኩባንያዎች ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዘው የጀርመን የቴክኖሎጂ ኩባንያ በኢትዮጵያ ከዚህ በፊት ሲሠራቸው ከነበሩ የቴክሎጂ ዘርፍ ሥራዎች በተጨማሪ በተጠናከረ መልኩ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል።

    NEWS: German automaker Volkswagen develops automotive industry in Ethiopia

    የጀርመን የቴክኖሎጂ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ማኅበርም ቢሮውን አዲስ አበባ በመክፈት ወደ ሥራ ለመግባት ፍቃደኛ መሆኑን አሳውቋል። ማኅበሩ ጀርመን ውስጥ ያሉ የቴክኖሎጂ ድርጅቶች ማኅበር እንደመሆኑ ድርጅቶቹ በመስኩ ለመሰማራት የሚያስችላቸውን ሁኔታ ለማመቻቸት መልካም አጋጣሚን እንደሚፈጥር ይታመናል።

    በኢትዮጵያ መንግስት በኩል በጊዜያዊነት በነፃ ቢሮ በመስጠት ጭምር ማንኛውንም እገዛ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑንም ተገልጿል።
    የልኡካን ቡድኑ አባላት በኢትዮጵያ ውስጥ በኢንቨስትመንት የተሰማሩ ድርጅቶች ከምንዛሬ እጥረት፣ በደላላ ምክንንያት ምርቶቻቸው ተጠቃሚው ጋር በተጋነነ ዋጋ መድረስ የመሳሰሉ ችግሮች እንደገጠሟቸው ተናግረዋል።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ለመጀመር ሥራዎች እየተሰሩ በመሆኑ ወደ ሥራ ሲገባ ችግሩ እንደሚቀረፍ ተናግረዋል።

    ምንጮች፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ቮልስዋገን


    Semonegna
    Keymaster

     

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢትዮጵያ አየር መንገድ 65 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በሚደርስ ወጪ ያስገነባውና ዓለምአቀፍ ደረጃውን የጠበቀው ስካይላይት ሆቴል እሁድ ጥር 19 ቀን 2011 ዓ.ም. ታላላቅ ባልስልጣናት እና የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተመረቀ።

    በአጠቃላይ 40 ሺህ ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው ስካይላይት ሆቴል (መደበኛ ስሙ፦ የኢትዮጵያ ስካይላይት ሆቴል/ Ethiopian Skylight Hotel) ለሦስት ዓመታት ያህል የግንባታው ሥራ አቭዬሽን ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ኦፍ ቻይና (Aviation Industry Corporation of China) በተባለ ድርጅት ሲከናወን የቆየ ሲሆን፥ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የባለ 5 ኮከብ ደረጃን ያገኛል ተብሎ ይጠበቃል።

    ሆቴሉ በመላው ዓለም የሚገኙ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አዲስ አበባ የሚመጡና በአዲስ አበባ የሚያልፉ ትራንዚተሮችን ከማስተናገድ ረገድ ትልቁን ድርሻ እንደሚወጣ ተገልጿል።

    Ethiopian Skylight Hotel – A new entrant to Ethiopia’s ever-growing hotel and hospitality industry

    ስካይላይት ሆቴል ከመደበኛ የመኝታ ክፍሎች እስከ ፕሬዝዳንታዊ ክፍሎች (presidential suites) የሚደርሱ በአጠቃላይ 373 የማረፊያ ክፍሎች፣ አራት ደረጃቸውን የጠበቁ ምግብ ቤቶች ሬስቶራንቶች (የኢትዮጵያ ባህላዊ ምግብ ቤት፣ የቻይና ሬስቶራንት፣ ዓለምአቀፍ ሬስቶራንት፣ ወዘተ)፣ ደረጃውን የጠበቀየመዋኛ ገንዳ፣ 2000 ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል ለስብሰባ ወይም ለተመሳሳይ አገልግሎቶች የሚውል የመሰብሰቢያ አዳራሽ፣ ሌሎች አነስተኛ የውይይት አዳራሾች እና ሌሎችም ዘርፈ-ብዙ የሆቴል አገልግሎቶችን ያሟላ ነው። ሆቴሉ ሀገሪቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ትኩረት ሰጥታ እየሠራችበት ያለውን የቱሪዝም ኢንዱስትሪን ይበልጥ እንደሚያግዝም ታምኖበታል።

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ እኤአ በ2025 በዓለምአቀፍ ደረጃ እጅግ ተወዳዳሪ አየር መንገድ ለማድረግ የሚያደርገውን ጥረት ለማሳካት መሰል የሆቴል ግንባታዎች ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑን በአየር መንገዱ የመሠረተ ልማት ክፍል ኃላፊ አቶ አብርሃም ተስፋዬ ለዋልታ ሚዲያ ተናግረዋል።

    ጥር 19 ተመርቆ ወደ ሥራ የሚገባው የቱሪዝም ኮንፌረንሱን በማገዝም የጎላ አስተዋፅዖ አለው ተብሏል። ስካይላይት ሆቴልን መቀመጫነቱን ቻይና ውስጥ ሸንዘን ከተማ (Shenzhen) ያደረገው ግራንድ ስካይላይት ሆቴል ማኔጅመንት (Grand Skylight Hotel Management) የተባለ የሆቴልና ሆስፒታሊቲ ድርጅት እንደሚያስተዳድረው ተጠቁሟል።

    ከዚህ ጋር በተያያዘ በዚሁ ዕለት (ጥር 19) አየር መንገዱ የአዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ላይ ሲያስገነባ የነበረው የማስፋፊያ ፕሮጀችትን እንደሚያስመረቅም አስታውቋል። እ.ኤ.አ. በ2018 መገባደጃ ላይ የዱባይ ኤርፖርትን በመብለጥ ወደ አፍሪካ ያለውን ከፍተኛ የመንገደኞች ፍሰት ያስተናገደው የአዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አሁን የሚመረቀው ማስፋፊያ ሲታከልበት ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ አዲስ ምዕራፍ እንደሚከፍት እምነት ተጥሎበታል። አዲሱ ማስፋፊያ በ74,000 ስኩዌር ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ሲሆን አሁን ኤርፖርቱ ማስተናገድ የሚችለውን የመንገደኛ ብዛት ከ8.5 ሚሊዮን ወደ 22 ሚሊዮን ከፍ ያደርገዋል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ስካይላይት ሆቴል


    Semonegna
    Keymaster

    ዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር ደጀን ከተማ ውስጥ (አማራ ክልል) የሚያስገነባው ሲሚንቶ ፋብሪካ አጠቃላይ ወጪው 8.8 ቢልዮን ብር እንደሆነና ግንባታው በ24 ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተጠቁሟል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– ዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር በአማራ ክልል ደጀን ከተማ ላይ ሲሚንቶ ፋብሪካ ለመገንባት ከሁለት የውጭ ሀገር ድርጅቶች ጋር የሦስትዮሽ የሥራ ስምምነት ተፈራረመ።

    አክስዮን ማኅበሩ አክስዮን ማኅበሩ ስምምነቱን የተፈራረመው መቀመጫውን ኮፐንሃገን ከተማ (ዴንማር) ያደረገውና ዓለምአቀፍ የምህንድስና (ግሎባል ኢንጂነሪንግ) ኩባንያ ከሆነው “FLSmidth & Co. A/S” እና መቀመጫውን ያንግጆ ከተማ፣ ቻይና (Yangzhou, China) ያደረገው ሌላው ዓለምአቀፍ የምህንድስና ኩባንያ “Hengyuan Group” ጋር አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሸራተን አዲስ ሆቴል ውስጥ ነው ነው። በስምምነቱ መሠረት “FLSmidth & Co. A/S” የግንባታ መሣሪያዎችን ሲያቀርብ፣ “Hengyuan Group” ደግሞ የግንባታውን ሥራ ያከናውናል። የፋብሪካው ግንባታ አጠቃላይ ወጪውም 8.8 ቢልዮን ብር እንደሆነና ግንባታው በ24 ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተጠቁሟል።

    ቪድዮ፦ በ8.8 ቢልዮን ብር በደጀን ከተማ (አማራ ክልል) የሲሚንቶ ፋብሪካ ሊገነባ ነው።

    የዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር ለሚገነባው ፋብሪካ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸውንም የአክስዮን ማኅበሩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበል ጠቁመዋል።

    በስምምነቱ ወቅት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝደንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፦ “ይሄ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለክልሉ ልማት ትልቅ አጋዥ ይሆናል የሚል እምነት አለን፤ ስለዚህ ገንቢዎቹም፣ አቅራቢዎቹም፣ ሁላችሁም ደጀን ላይ ይህንን ሲሚንቶ ፋብሪካ ለማፋጠን በምታደርጉት ጥረት የአማራ ክልል ሕዝብና መንግስት ሁልጊዜም ቢሆን ከጎናችሁ ይሆናል” በማለት የክልሉን መንግስት ደጋፍ አረጋግጠዋል።

    የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንም በበኩላቸው የመሠረት ድንጋይ ማስቀመጥ ብቻ ትርጉም እንደሌለውና፣ ይልቁንም በፍጥነት ተገንብተው ወደማምረት ሥራና ለኅብረተሰቡ የሥራ ዕድል ፈጠራ መግባት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

    የሲሚንቶ ፋብሪካው ወደ ሥራ ሲገባ በቀን 5 ሺህ ቶን ክሊንከር እና በዓመት 2.25 ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ እንዲያመርት፣ ለዚህም 655 ሰዎችን በቋሚነት የሚቀጥር ሲሆን፥ ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ሥራ ሲጀምር ደግሞ የሠራተኞቹን ቁጥር ወደ 1,500 ለማሳደግ ታቅዶ እንደሚገነባ ማብራሪያ ተሰጥቷል።

    ዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር በህዝብና በግል ባለሀብቶች ባለቤትነት በአክስዮን የተቋቋመ የንግድ ድርጅት ነው። ዋና መሥሪያ ቤቱም የአማራ ክልላዊ መንግስት ዋና ከተማ በሆነችው ባሕር ዳር ከተማ ውስጥ ነው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር


    Anonymous
    Inactive

    የአቶ በረከት ስምኦን እና አቶ ታደሰ ካሳ በቁጥጥር ሥር መዋል

    ሁለቱ የቀድሞ የብአዴንና የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች በቁጥጥር ሥር የዋሉት በጥረት ኮርፕሬት ፈፅመዋል ተብለው በተጠረጠሩበት የኃብት ብክነት ወንጀል ነው።
    ባህር ዳር —

    ሁለቱ የቀድሞ የብአዴንና የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች በቁጥጥር ሥር የዋሉት በጥረት ኮርፕሬት ፈፅመዋል ተብለው በተጠረጠሩበት የኃብት ብክነት ወንጀል ነው።
    አቶ ታደሰ ካሳ በጥረት ኮርፕሬት በዋና ሥራ አስፈፃሚነት አቶ በረከት ስምኦን ደግሞ የጥረት ኮርፕሬት የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ለበርካታ ዓመታት ሰርተዋል። ሁለቱ የቀድሞ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ አዲስ አበባ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ነው የተያዙት።
    ይህንን ተከትሎ የአማራ ክልል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። አቶ በረከትና አቶ ታደሰ ዛሬ ጠዋት ባህር ዳር ከተማ የገቡ ሲሆን በጊዜያዊ ማረፊያ ቤት ውስጥ እንደሚገኙ ኮሚሽነር ዝግ አለ ገበየሁ ተናግረዋል።

    ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
    VOA Amharic

Viewing 15 results - 376 through 390 (of 495 total)