Search Results for 'አዲስ አበባ'

Home Forums Search Search Results for 'አዲስ አበባ'

Viewing 15 results - 391 through 405 (of 495 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – አቶ በረከት ስምኦን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) የአማራ ክልል የልማትና ኢንቨስትመንት ድርጅት በሆነው ጥረት ኮርፖሬት ላይ ከደረሰ የሀብት ብክነት ወንጀል ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአማራ ክልላዊ መንግስት ፀረ ሙስና ኮሚሽን አስታወቀ።

    የአማራ ክልል ፀረ ሙስና ኮሚሽኑ ኮሚሽነር አቶ ዝግአለ ገበየሁ አቶ በረከት ስምኦን እና አቶ ታደሰ ካሳ (“ተጠርጣሪዎች”) በቁጥጥር ስር ውለው ወደ ባህር ዳር መወሰዳቸውን ለመገናኛ ብዙኃንና ለጋዜጠኞች አስታውቀዋል። እንደ አቶ ዝግአለ ገለጻ፥ ሁለቱ ተጠርጣሪዎች ከፍተኛ በሆነ የሀብት ብክነት ምክንያት ጥረት ኮርፖሬትን ለኪሳራ ዳርገዋል፤ ይህም በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ምክንያት እንደሆነና የተጠረጠሩበት ወንጀል የተፈፀመው በክልሉ በመሆኑ ጉዳያቸው በክልሉ ፍርድ ቤት የሚታይ ይሆናል።

    የክልሉ ፀረ ሙስና ኮሚሽን በእስካሁኑ የመረጃና ማስረጃ ማሰባሰብ ሂደት በሁለቱ ግለሰቦች ላይ ተገቢውን ክስ ለመመሥረት የሚያስችለውን በቂ መረጃ/ማስረጃ መሰበሰቡንም አስታውቋል።

    አባይ የህትመትና የወረቀት ፓኬጂን ፋብሪካ ባህር ዳር ከተማ ውስጥ ሥራ ጀመረ

    አቶ በረከት ስምኦን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) የቀድሞዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኢሕድን)እና የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) መሥራቾች ከመሆናቸው በተጨማሪ በፌደራልና በክልል መንግስታዊ ቦታውች ለረዥም ጊዜ ሲያገለግሉ ቆይተዋል። በጥረት ኮርፖሬት ውስጥ ደግሞ አቶ ታደሰ ካሳ በዋና ሥራ አስፈፃሚነት አቶ በረከት ስምኦን ደግሞ በቦርድ ሰብሳቢነት ለበርካታ ዓመታት መሥራታቸው ተጠቁሟል።

    አቶ በረከት ስምኦን እና አቶ ታደሰ ካሳን በቁጥጥር ስር ለመዋል ያበቃቸውና ጥረት ኮርፖሬት ላይ የተፈጸመው የሀብት ብክነት ምንድን ነው?

    የጥረት ኮርፖሬት የሀብት፣ እንዲሁም በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የገንዘብ ብክነት ተፈጽሞብኛል ያላቸው ዝርዝሮች፦

    • የኮርፖሬቱ ንብረት የሆኑ አምስት ኩባንያዎች ከ ክስዮን መሸጥ/ግዢ ጋር በተያያዘ ለሀብት ብክነት የዳረገ ብልሹ አሠራር በኦዲት ተደርሶበታል፤
    • ሌሎች ሁለት እህት ኩባንያዎች ላይ ተመሳሳይ የኦዲት ሥራ እየተሠራ ነው፤
    • ተጠርጣሪዎቹ በኮርፖሬቱ ውስጥ በስልጣን ላይ እያሉ የተመሠረቱ ስድስት እህት ኩባንያዎች፥ ከመመሥረታቸው በፊት አስፈላጊውን የአዋጭነት ጥናት ሳይደረግ ለእነዚህ ኩባንያዎች መመሠረቻ/ ግዢ ወደ ሚሊዮን ብር ወጪ ወጥቷል፤
    • እነዚህ ስድስት እህት ኩባንያዎች ከተመሠረቱ/ ከተገዙ በኋላ በጊዜው ወደሥራ ባለመግባታቸው ኮርፖሬቱን ለተጨማሪ ወጪ/ ኪሳራ ዳርገውታል፤
    • ጥረት ኮርፖሬሽን በአጋርነት ከሚሠራቸው ኩባንያዎች ጋርም ከኮርፖሬቱ የፋይናንስ አሠራርና ሕግ ውጪ 7 ሚሊየን ብር ለሁለት ኩባንያዎች ተሰጥቷል፤
    • በሦስት ግለሰቦች ለሚተዳደር አንድ የማዕድን ኩባንያ ላወጣው የእያንዳንዱ አክሲዮን ዋጋ 1,000 ብር ሲሆን፥ ጥረት ኮርፖሬት በአንጻሩ የእያንዳንዱን አክሲዮን ዋጋ በ2,200 ብር እንዲገዛ ተደርጓል። በዚህም ሦስቱ ባለሀብቶች የ4 ሚሊየን 320 ሺህ ብር ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆኑ፥ ጥረት ኮርፖሬት ግን ለኪሳራ ተዳርጓል፤
    • ባለሙያን ያላካተተ የአክስዮን መግዛትና መሸጥ ሥራ በኮርፖሬቱ ውስጥ ይተገበር ነበር፤ ይህም ለሀብት ብክነት ተጨማሪ ምክንያት ሆኗል፤
    • ለካፒታል ዕድገት ለሀገር ውስጥ ገቢ መክፈል የነበረበትን 1 ሚሊዮን 296 ሺህ ብር ባለመክፈሉ ጥረት ኮርፖሬት ባለዕዳ አድርጎታል፤
    • ለፋብሪካ ይገነባል በሚል የ17 ሚሊየን ብር ግብዓት ተገዝቶ እስካሁን ምንም ዓይነት ሥራላ በለመዋሉ ኮርፖሬቱን ለሌላ የሀብት ብክነት ዳርጎታል።

    በስተመጨረሻም አቶ ዝግአለ እንዳስታወቁት የአቶ በረከት ስምኦን እና የአቶ ታደሰ ካሳ በቁጥጥር ስር መዋል መጀመሪያ እንደሆነና፥ ሌሎችም በእንዲህ ዓይነት ወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎች በቁጥጥር ስር ይውላሉ።

    ቀድሞ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኢሕዴን)፣ በመሀል ብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን)፣ አሁን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ) የተባለው የአማራ ሕዝብ ፓርቲ ያቋቋመው ጥረት ኮርፖሬት በአምራችነት ዘርፍ፣ በአገልግሎት መሰጠት ዘርፍ፣ በኮንስትራክሽን ዘርፍ እና በ አግሮ ፕሮሰሲንግ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ የአስራ ዘጠኝ ኩባንያዎች ባለቤት መሆኑን የኮርፖሬቱ ድረ ገጽ ያሳያል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አቶ በረከት ስምኦን እና አቶ ታደሰ ካሳ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፍተኛ ኃይል የሚጠቀሙ ደንበኞቹ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳባቸው በባንክ እንዲከፍሉ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ጥር 13 ቀን 2011 ዓ.ም. ተፈራርሟል።

    ስምምነቱን የተፈፀመው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የባንክ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ደረጄ ፉፋ አማካኝነት ነው።

    ኢትዮ ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ተሸካሚ ላይ የተዘረጋውን ገመድ በጋራ ለመጠቀም ተስማሙ

    የመግባቢያ ስምምነቱ ዋና ዓላማ በመጀመሪያው ምእራፍ 27 ሺህ የሚሆኑ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚጠቀሙ እንዲሁም መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳባቸውን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል እንዲከፍሉ ለማስቻል እና በቀጣይም በአፈጻጸም ሂደቱ የተገኙ ተሞክሮዎችን በማካተት በመላ ሀገሪቱ ያሉ ደንበኞች ላይም ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ በሥነ ሥርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር አስታውቀዋል።

    ተቋሙ ቀድሞ ይጠቀምበት የነበርውን የፍጆታ ሂሳብ አሰባሰብ ስርዓት በመቀየር፣ ቀልጣፋና በዘመናዊ ቴክኖሎጅ የታገዘ አገልግሎት ለደንበኞቹ ለመስጠት እንደሚስያችለው አክለው ገልፀዋል። ይህም በመሆኑ ተቋሙ፣ ባንኩና ደንበኞች የፍጆታ ሂሳብ ለመክፍል ይፈጠር የነበረውን የገንዘብና የጉልበት ብክነት በከፍተኛ ደረጃ ስለሚቀንሰው፤ ሦስቱም አካላት ተጠቃሚ ይሆናሉ ሲሉ ነው ዋና ሥራ አስፈፃሚው የተናገሩት።

    አዳዲስ የቴክኖሎጂ ዕውቀቶችና ልምዶች የተገኙበትና በምስራቅ አፍሪካ በርዝመት ቀዳሚውን ስፍራ የያዘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት ህንጻ

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የባንክ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ደረጄ ፉፋ በበኩላቸው፥ ዘመናዊ የክፍያ ስርዓት መዘርጋቱ ደንበኞች ሳይጉላሉ ካሉበት ስፍራ ሆነው ክፍያ በባንኩ አማካኝነት በቀላሉ ለመክፍል እንደሚያስችላቸው ገልፀዋል። ሲያጋጥሙ የነበሩ የአከፋፈል ስርዓት ችግሮችን እንዲቀርፍ ያስችላል፤ ደንበኞችም ያጠፉት የነበረውን ጊዜና የሚያጋጥማቸው ውጣ ውረድ ይቀንስላቸዋል ሲሉ ነው አክለው የተናገሩት።

    በስምምነቱ መሠረት እነዚህ ደንበኞች በቂ ግንዛቤ በተለያዩ አማራጮች ካገኙ በኋላ በያዝነው ዓመት ከሚያዝያ ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ እንዲሁም የዚህን ጅምር ሥራ ውጤታማነት ከታየ በኋላ ሁሉም ደንበኞች በተመሳሳይ መልኩ ክፍያ እንዲፈፅሙ በቀጣይ አንደሚደረግ ተገልጿል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– አዲስ አበባን ከኤርትራዋ ምጽዋ ጋር ለሚያገናኘው የባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥናት ወጪ ለመሸፈን የጣሊያን መንግስት መስማማቱን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

    በጣሊያን ጉብኝት እያደረጉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጣሊያን አቻቸው ጁሴፔ ኮንቴ ጋር ተወያይተዋል። መሪዎቹ ከውይይቱ በኋላ በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ጣልያን አዲስ አበባን ከምፅዋ ለሚያገናኘው የባቡር መስመር ፕሮጀክት የመጀመሪያ ጥናት ወጪ ለመሸፈን ተስማምታለች።

    ከጥናቱም በኋላ በሚገኘው ውጤት በጋራ ለመሥራት ፍላጎት እንዳላት ጁሴፔ ኮንቴ እንደገለጹላቸውና ለዚህም የኢትዮጵያ መንግስት ምስጋናውን እንደሚያቀርብ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ተናግረዋል።

    አዲስ አበባ እንደ ስሟ እንድትሆንና ነዋሪዎች ወጥተው ሲገቡ የሚዝናኑበትን ቦታ ከመፈለግ አንጻር በአዲስ አበባ በሚገኙ ኤምባሲዎች የተወሰነ ቦታቸውን ለህዝብ መዝናኛ ፓርክ እንዲያውሉ ጥያቄ ቀርቧል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ የጣልያን መንግስትም ለዚህ ቅን ምላሽ መስጠቱን ተናግረዋል።

    ◌ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከጣሊያን አቻቸው ጁሴፔ ኮንቴ የሰጡት የጋራ መግለጫ

    የኢትዮጵያ መንግስት የብሔራዊ ቤተ መንግስቱን ግማሽ የህዝብ መዝናኛ ፓርክ ለማድረግ እየሠራ መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጠቅሰዋል። በአዲስ አበባ ለተቸገሩ ወገኖች ምግብ ለማቅረብ በሚደረገው ጥረት ጣልያን በመዲናዋ የዳቦ መጋገሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ፍላጎት እንዳላትም አንስተዋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጣልያን ቆይታቸው ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በልማትና በሰላም ውይይቶች እንዳደረጉና ከአቻቸው ጁሴፔ ኮንቴ ጋር ያደረጉት ሁለገብ ምክክርም የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማሳደግ ፈር ቀዳጅ እንደሆነ ተናግረዋል።

    በምስራቅ አፍሪካ ሰላም፣ ልማትና አንድነት እንዲረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የጣሊያን መንግስት ድጋፍ ለማድረግ ፍላጎት እንዳለው ዶ/ር አብይ አመልክተዋል።

    በኢትዮጵያና በጣልያን መካከል የተደረገው ውይይት ፍሬያማ እንዲሆን በተለያዩ አጋጣሚዎች በሚካሄዱ የሁለትዮሽ ውይይቶች አገራቱ በሰላም፣ በልማትና በቱሪዝም ያለውን ግንኙነት ማጠናከር እንደሚገባም አንስተዋል። አገራቱ ለጋራ እድገትና ሰላም በጋራ እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።

    በአጠቃላይ ከልዑካን ቡድኑ ጋር በጣልያን የነበራቸው ቆይታ ስኬታማ እንደነበረ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለፁት። “እንደ ወንድም አገርና እንደ ጠንካራ ወዳጅ ከምናያት ከጣልያን የምንፈልገውን ነገር አግኝተናል” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

    የኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ምርቱን ለመጨመር እና የኤክስፖርት መጠኑን ለማሳደግ እየሠራ ነው

    የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጄሴፔ ኮንቴ በበኩላቸው ሁለቱ አገራት ታሪካዊ የሚባል ግንኙነት እንዳላቸውና በበርካታ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራና በትብብር ለመሥራት መግባባታቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለምታከናውናቸው የልማት ሥራዎች የጣሊያን መንግስት የሚሰጠውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ቃል ገብተዋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በጣልያን ጉብኝት ያደረጉት የጣሊያኑ አቻቸው ጁሴፔ ኮንቴ በ2011 ዓ.ም መጀመሪያ በኢትዮጵያ ጉብኝት ባረደጉበት ወቅት ባቀረቡላቸው ግብዣ መሠረት ነው።

    ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጣሊያን ቆይታቸው ከአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሰርጂዮ ማታሬላ፣ ከዓለም የምግብ ድርጅት ዋና ዳሬክተር ዴቪድ ቤዝሊ፣ ከተባበሩት መንግስታት የምግብና የእርሻ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ሆዜ ግራዚያኖ ዳ ሲልቫና ከግብርና ልማት ዓለም አቀፍ ፈንድ ፕሬዝዳንት ጊልበርት ሆዉንግቦ ጋር ተወያይተዋል።

    በሌላ በኩል ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር የተጓዘው የልዑካን ቡድን በሮም ከጣሊያን ባለሃብቶች ጋር ውይይት አካሂዷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ አምባሳደር ፍጹም አረጋ እንዲሁም የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር አበበ አበባየሁን ያካተተው የልዑካን ቡድን ለባለሃብቶቹ ሃገሪቱ ስላላት የተለያዩ የኢንቨሰትመንት ዘርፎችና አማራጮች ማብራሪያ መስጠታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

    በኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የሚገኙ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካዎች ምርታቸውን ወደውጭ ሀገራት መላክ ጀምረዋል

    ካርቪኮ ግሩፕ በአሁኑ ሰዓት በኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ በ23 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ ግንባታውን እያጠናቀቀ ሲሆን፥ በጣሊያንና በቬትናም በሚገኙ ፋብሪካዎች የሠራተኛ ስልጠና በማድረግ ዝግጅቱን ለመጀመር በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።

    በውይይቱ የተገኙት ሌሎች ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በመድኃኒት፣ በግንባታ፣ በግብርና ማቀነባበርያ እና አልባሳት ዘርፍ በስፋት ለመሰማራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል ተብሏል።

    በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራው የልዑካን ቡድን ከጣልያን ቆይታው በኋላ በስዊዘርላንድ ዳቮስ ከተማ በሚካሄደው የዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም ለመሳተፍ ወደ ስፍራው ያቀናል ተብሎ ይጠበቃል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከጣሊያን አቻቸው ጁሴፔ ኮንቴ ጋር


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በ2006 ዓ.ም. በሰባት የየመገናኛ ብዙሃን (ሚዲያ) እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የተቋቋመው ጉዞ ዓድዋ፥ አንድ ሺሕ አስር ኪሎሜትሮችን የሚሸፍን፣ ከኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ተነስቶ መዳረሻውን የዓድዋ ድል አምባ ተራሮች ጫፍ ላይ የሚያደርግ ረዥም የእግር ጉዞ ነው። ላለፉት ስድስት ዓመታት ከጥር ወር ጀምሮ የዓድዋ ድል በዓል እስከ ሚከበርበት የካቲት 23 ቀን ድረስ ከስድስት ሳምንታት ላላነሰ በየዓመቱ ሳይቋረጥ የቆየው ጉዞ ዓድዋ፥ ዘንድሮ የኢትዮጵያዊነቱ ስሜት እጅግ ጎልቶ በጉዞው ላይ የሚሳተፉት ቁጥርም ጨምሯል። በዘንድሮው ጊዞ ዓድዋ 44 ተጋዦች ከአዲስ አበባ እና 4 ተጓዦች ከሐረር በአጠቃላይ 48 ተጓዦች ጥር 7 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀን ከአዲስ አበባ ተነስተዋል።

    የመላው አፍሪቃውያን ድል እስከመባል የደረሰው ታላቁ የዓድዋ ድል፥ የግዝፈቱን ያህል ክብር እና መታወሻ ሥነሥርዐት ሳይኖረው እየተከታተለ ከመጣው ትውልድ ጋር የበዓሉ አከባበር ዐውድ እየወረደ ጭራሽ እየተዘነጋ እና እየደበዘዘ መሔድ ያሳሰባቸው የጉዞ ዓድዋ መሥራቾች ትውልዱ ትኩረት ሰጥቶ የድሉን መንፈስ እንዲጋራ ለማድረግ ይህንን የጉዞ ሐሳብ አመንጭተዋል።

    ◌ የጉዞ ዓድዋ ተጓዦችና የኢትዮጵያዊያን አስተያየት

    በዚህም የተነሣ ጉዞ ዓድዋ ባለፉት ስድስት ዓመታት ብቻ ከታለመው ዓላማ አንጻር ከፍተኛ የሆነ አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ የዓድዋ ድል በዓል ቀድሞ ከነበረበት አከባበር የላቀ ተሳትፎ ያለው የድል በዓል እንዲሆን አስተዋጽዖ ለማድረግ ተችሏል።

    ጉዞውን ከማካሔድ በተጓዳኝ በየመንገዱ ተንቀሳቃሽ የመጻሕፍት ንባብ መሰናዶ በማካሔድ በየዓመቱ የሚጓዙ አባላትን በዓድዋ ጦርነት እና ድል ዙሪያ በቂ የሆነ ግንዛቤ እና ዕውቀት የማጋራት ዝግጅቶችን ሲያካሂድ ቆይቷል። ከአንድ ወር በላይ በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ሰፊ ሽፋን የሚሰጠው የጉዞው የዕለት ተእለት ውሎ፣ በዓሉ ከመድረሱ አስቀድሞ በበርካታው ሕዝባችን ላይ የካቲት 23 ዕለትን በጉጉት የመጠበቅ ስሜት እንዲፈጠር አድርጓል።

    ◌ የዓድዋ ድል በዓል በጎሰኞች ዓይን የዲያቆን ዳንኤል ክብረት መጣጥፍ

    ከዚህ ቀደም የድል በዓሉ በብቸኝነት ከሚከበርባቸው የአዲስ አበባ እና የዓድዋ ከተሞች በተጨማሪ ከ28 በላይየሚሆኑ የክልል ከተሞች እና በርካታ ሕዝብ የሚኖርባቸው የገጠር ወረዳዎች ተጓዥ ቡድኑ በየደረሰበት በሚኖሩ ደማቅ አቀባበሎች ላይ በሚሰጡ የግንዛቤ መስጫ መልዕክቶች ስለ ዓድዋ ድል ታሪክ ግንዛቤ በመሰጠቱ የበዓሉአከባበር ከፍተኛ ለውጥ በማምጣት ላይ ይገኛል። የጉዞ ዓድዋ ትሩፋቶች፦

    • በዓድዋ ከተማ ውስጥ በአምስት ዓመት አንድ ጊዜ ብቻ የነበረው የዓድዋ ድል በዓል አከባበር ሥነ ሥርዐትበየዓመቱ እንዲካሔድ አስችሏል።
    • የበዓሉ አከባበር በፌደራል መንግሥት ደረጃ እንዲከበር ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጓል።
    • ከ120 ዓመታት በፊት መቀሌ ከተማ በሚገኘው የእንዳየሱስን ምሽግ ለማስለቀቅ ከጣሊያን ጦር ጋር ሲዋጉ ሕይወታቸው ያለፉ ጀግና ኢትዮጵያውያን አጽም የትም ተበታትኖ በመቅረቱ፥ ጉዞ ዓድዋ በአሁኑ ሰዓት የቦታው አስተዳዳሪ የሆነውን የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ በማንቃት፤ የካቲት 26 ቀን 2008 ዓ. ም አጽማቸውን አሰባስቦ በክብር እንዲያርፍ ተደርጓል። ከዚህም ባሻገር በዓመቱ የካቲት 26 ቀን 2009 ዓ.ም በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ወጪ “የጀግኖች ኢትዮጵያዊያን መታሰቢያ ሙዚየም” የተሰኘ ጣራ አልባ ቤተ መዘክር በእንዳየሱስ ታሪካዊ ምሽግ ላይ ተገንብቶ ለመመረቅ በቅቷል።
    • የዓድዋ ጦርነት መንስዔ የሆነው የዉጫሌ ውል የተፈረመበት “ይስማ ንጉሥ” የተባለው ታሪካዊ ቦታ ተከልሎ ጥበቃ እንዲደረግለት በማድረግ ጉዞ ዓድዋ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል። ከዚህም በተጨማሪ ውሉ በተፈረመበት ዕለት ሚያዝያ 25 ቀን በየዓመቱ፤ ምሁራዊ ተዋስዖ የሚደረግባቸው መድረኮች በመፍጠር፣ ላለፉት ስድስት ዓመታት ባበረከተው የላቀ አስተጽዖ የአምባሰል ወረዳ የዓድዋ ድልን ለመዘከርና ቦታውን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ያለመቋሚ ቤተ መዘክር በቦታው ላይ እንዲገነባ የሚያስችል የ19 ሚልዮን ብር የበጀት ድጋፍ ከአማራ ክልል መንግሥት እንዲያገኝ ጉዞ ዓድዋ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል።
    • ለበርካታ ዓመታት አገልግሎቱ ተዘግቶ የቆየው በዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ የትውልድ መንደር “አንጎለላ” የሚገኘው የዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ መታሰቢያ ክሊኒክ እንዲከፈት ከፍተኛ ቅስቀሳ በማድረግ፤ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ድጋፍ ክሊኒኩ ታዳጊ የጤና ጣቢያ ሆኖ በድጋሚ አገልግሎት እንዲሰጥ ጉዞ ዓድዋ አስተዋጽዖ ካደረጉ መካከል ግንባር ቀደሙን ሚና ተጫውቷል።
    • የዓድዋ ጀግና የሆኑት ራስ አሉላ አባ ነጋ የቀብር ቦታ በሆነው የአባ ገሪማ ገዳም ውስጥ ለሁለቱም ጾታዎች ጉብኝት ምቹ በሆነ ቦታ ላይ ሐውልት እንዲቆምላቸው ጉዞ ዓድዋ ባመቻቸው ዕድል በአንድ ባለ ሀብት ሐውልታቸው ተሠርቶ ለምረቃ በቅቷል።
    • በየዓመቱ በሚካሔዱ ጉዞዎች ከዓድዋ ድል ጋር ግንኙነት ያላቸው ቦታዋችን እና ልዩ ታሪካዊ መረጃዎችን በምስል እና በጽሑፍ በመሰብሰብ ለጥናትና ምርምር አስተዋጽዖ ማበርከት የሚችሉ የታሪክ ግብዓቶችን በማደራጀት በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በተለይም የማኅበራዊ ድረ ገጽን በመጠቀም ቅርሶችን የማስተዋወቅና የመጠበቅ ሥራዎችንበ መሥራት ላይ ይገኛል።

    የጉዞ ዓድዋ ማኅበር የዓድዋ ድል በዓል በኢትዮጵያውያን እንዲሁም በጥቁር አፍሪካውያን ዘንድ የሚገባውን ክብር እንዲያገኝ ላደረገው ጥረት፣ ከላይ ለተጠቀሱት እና በየዓመቱ በሚያደርጋቸው እጅግ አመርቂ ክንዋኔዎች ምክንያት በ2009 ዓም በቅርስና ባሕል ዘርፍ የዓመቱ በጎ ሰው ተሸላሚ ሆኗል።

    ላይ የሚሳተፉ ተጓዦች በጉዞአቸው ላይ የሚያደርጓቸውን የተለያዩ ክንዋኔዎችና የሚዘግቧቸውን ታሪክ ተኮር ዘገባዎች ለመከታተል የማኅበሩን የፌስቦክ ገጽ ይጎብኙ።

    ◌ ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ በደብረ ብርሃን ከተማ ሃውልት ሊቆምላቸው ነው

    ምንጭ፦ በጎ ሰው ሽልማት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ጉዞ ዓድዋ


    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት የሚያዘጋጀው ሽልማት ዓላማ በኢትዮጵያ አምራቾችና አገልግሎት ሰጪዎች እንዲሁም በግንባታ ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች ለጥራት የሚያደርጉትን ሥራ ማበረታታት መሆኑ በሽልማቱ ሥነ-ሥርዓት ወቅት ተገልጿል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለሦስተኛ ጊዜ የአገር አቀፍ የጥራት ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆነ። ዩኒቨርሲቲው ያገኘውን ሽልማት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ደሳለኝ መንገሻ (ዶ/ር) ከፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እጅ ተቀብለዋል።

    የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ስድስተኛ ዙር የጥራት ሽልማት ጥር 2 ቀን 2011 ዓ.ም. ምሽት በብሔራዊ ቤተ-መንግስት ተካሂዷል። በሽልማትና ዕውቅና ሥነ-ሥርዓቱ ላይ 40 ድርጅቶችና ተቋማት የምስክር ወረቀትና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በውድድሩ ላይ

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ሐረር ቢራ አክሲዮን ማኅበር እና አማራ መልሶ ማቋቋምና ልማት ድርጅት የአንደኛ ደረጃ ዋንጫ ተሸላሚ ሲሆኑ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለተከታታይ ሦስት ዓመታት የጥራት ደረጃውን ጠብቆ አሸናፊ በመሆኑ የልዩ ዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

    The Ethiopian Quality Award Organization

    ከ336 በላይ ድርጅቶች እንዲመዘገቡ ጥሪ የተደረገ ቢሆንም የተመዘገቡት 52 ነበሩ። ከነዚህ ውስጥ 21 በአምራች፣ አምስት በአገልግሎት፣ አራት በከፍተኛ ትምህርት፣ አምስት በጤና እና አምስት በግንባታ ዘርፍ የተሰማሩ፤ በድምሩ 40 ተቋማት እስከመጨረሻው በውድድሩ የዘለቁ ናቸው።

    የሽልማቱ ዋና ዓላማ በኢትዮጵያ አምራቾችና አገልግሎት ሰጪዎች እንዲሁም በግንባታ ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች ለጥራት የሚያደርጉትን ሥራ ማበረታታት መሆኑ በሥነ-ሥርዓቱ ወቅት ተገልጿል።

    የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት የበላይ ጠባቂ የሆኑት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የጥራት ጉዳይ የሥነ-ልቦናና የፈረጠመ የኢኮኖሚ የበላይነት እንዲሁም የበለፀገ ማኅበረሰብ መገለጫዎች ናቸው ብለዋል። የምርትና አገልግሎት ጥራትን ለማስጠበቅና ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ከደረሱበት የጥራት ደረጃ ለመድረስ ጠንክሮ መሥራት እንደሚገባም አሳስበዋል።

    የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት በ2000 ዓ.ም በዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከልና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትብብር የተቋቋመ ነው። ድርጅቱ ሲመሠረት ዓላማውን መንግስት በጥራት ረገድ የሚያደርገውን ጥረት ለመደገፍና የጥራት ጽንሰ ሀሰብን በማኅበረሰቡ፣ በአምራቾች፣ በአገልግሎት ሰጪዎችና በግንባታ (ኮንስትራክሽን) ዘርፍ በተሰማሩ ድርጅቶችና ተቋማት ዘንድ እንዲሰርጽ ለማድረግ ነው። እስካሁን 49 ድርጅቶችና ተቋማት የድርጅቱን የልዕቀት ማዕረግ የዋንጫ ሽልማት አግኝተዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት


    Semonegna
    Keymaster

    የከተማዋን የቱሪዝም ዕድገት ከፍ ለማድረግ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ምኒልክ ሃውልቶችን የከተማ አስተዳደሩ ኅብረተሰቡን በማሳተፍ ያስገነባል። ስለሆነም የሁለቱ ታላላቅ መሪዎች ሃውልት በከተማዋ እንዲቆም እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ከ6 መቶ ዓመታት በላይ ባስቆጠረችው የድሮዋ ደብረ ኤባ የዛሬዋ ደብረ ብርሃን ከተማ ለዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሃውልት ሊቆምላቸው እንቅስቃሴ መጀመሩን ከተማ አስተዳደሩ አስታውቋል።

    የከተማዋ ምክትል ከንቲባ እና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ብርሃን ገብረሕይወት ጥር 9 ቀን 2011 ዓ.ም. አዲስ አበባ ላይ በሰጡት መግለጫ ደብረ ብርሃን ከተማን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የከተማ አስተዳደሩ እየሠራ ነው፤ ከተማዋን የኮንፈረንስ ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግም ከተማ አስተዳደሩ ባዛሮችን በተለያዩ ጊዚያት እንደሚያካሂድ ተገልጿል።

    የከተማዋን የቱሪዝም ዕድገት ከፍ ለማድረግ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ምኒልክ ሃውልቶችን የከተማ አስተዳደሩ ኅብረተሰቡን በማሳተፍ ያስገነባል። ስለሆነም የሁለቱ ታላላቅ መሪዎች ሃውልት በከተማዋ እንዲቆም እንቅስቃሴ እየተደረገ ነውም ተብሏል።

    ደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ በከተማዋ ለሚኖሩ ዜጎች የተለያዩ የሥራ ዕድሎችን ፈጥሯል

    ከተማ አስተዳደሩ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እየሠራ እንደሆነም አስታውቋል። ደብረ ብርሃን ከተማ በዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ መመሥረቷ ይታወቃል።

    አጼ ዘርአ ያዕቆብ

    አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስትክብረ እግዚ እ.ኤ.አ. በ1399 ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮው ፈታጃር ክፍለ ሀገር ተወለዱ። የነገሡበትም ዘመን እ.ኤ.አ. ከ 1434 እስከ 1468 (እስከሞቱበት ጊዜ) ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው።

    ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ

    ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ከአባታችው ከሸዋው ንጉሥ ኃይለ መለኮት ሣህለ ሥላሴና ከእናታቸው ወይዘሮ እጅጋየሁ ለማ አድያም እ.ኤ.አ. ነሐሴ 17 ቀን 1844 ደብረ ብርሃን አካባቢ አንጎለላ ከሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ በአንጎለላ መቅደላ ኪዳነ ምኅረት ቤተ ክርስቲያን ክርስትና ተነሱ። የነገሡበትም ዘመን እ.ኤ.አ. ከ 1889 እስከ 1913 (እስከሞቱበት ጊዜ) ነበር። ያረፉትም ተዓካ ነገሥት ለማርያም ወደብረ መንክራት ስዕል ቤት ኪዳነ ምኅረት ገዳም (አዲስ አበባ) ነው።

    ምንጭ፦ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሃውልት


    Semonegna
    Keymaster

    የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጅክቶቹ በገንዘብ ሚኒስቴር የ100 ቀናት ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ሲሆን ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ 798 ኪሎ ዋት የማመንጭት አቅም አላቸው። የፕሮጀክቶቹ ወጪ 795 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንደሚገመት በጥናቱ ላይ ተመላክቷል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – በኢትዮጵያ መንግስትና በግል ድርጅቶች (ኢንቨስተሮች) አጋርነት የሚሠሩ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል።

    ጥር 9 ቀን 2011 ዓ.ም. በገንዘብ ሚኒስቴር በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተገለፀው ስድስቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በአፋር፣ በሶማሌ፣ በኦሮሚያ እና በትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስታት ስር ይተገበራሉ ተብሏል።

    ስድስቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጅክቶች በገንዘብ ሚኒስቴር የ100 ቀናት ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ሲሆን ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ 798 ኪሎ ዋት የማመንጭት አቅም አላቸው። የፕሮጀክቶቹ ወጪ 795 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንደሚገመት በጥናቱ ላይ ተመላክቷል።

    የኮምቦልቻ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ የውጪ ንግዱን ለማሳደግ እና የምርት መጠኑን ለመጨመር እየሠራ መሆኑን አስታወቀ

    የገንዘብ ሚኒስቴር ዴኤታ ተሾመ ታፈሰ (ዶ/ር) አገሪቱ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ ለመሰለፍ ያስቀመጠችውን ራዕይ ለማሳካት ከዚህም ጋር ተያይዞ በየጊዜው ሳያቋርጥ እያደገ የመጣውን የህዝብ የኃይል አገልግልት ፍላጎት ለማሟላት ከመንግስት የፋይናንስ ምንጮች በተጨማሪ ሌሎች አማራጮችን ማየት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ሲሉ ገልጸዋል።

    የመንግስትና የግል አጋርነት (መግአ) የመሠረተ-ልማት አቅርቦትን ለማሻሻል እንደ አንድ ስልት የሚወሰድ ነው ያሉት ዶ/ር ተሾመ በአግባቡ ሥራ ላይ ከዋለ የግሉን ዘርፍ የኢንቨስትመንት አቅም እንደ አስፈላጊነቱ ለመጠቀም እድል ይሳጣል ሲሉ ተናግረዋል።

    ምንጭ፦ የገንዘብ ሚኒስቴር/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጅክቶች


    Semonegna
    Keymaster

    የጊዳቦ ግድብ ሥራ ፕሮጀክት በ258 ሚሊዮን ብር በጀት የተጀመረ ቢሆንም ግንባታው በተያዘለት የጊዜ ገደብ ባለመጠናቀቁ እና የዲዛይን ለውጥ በመደረጉ አጠቃላይ የግንባታ ወጭው 1.66 ቢሊዮን ብር መድረሱን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አስታውቀዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢ.ኮ.ሥ.ኮ) በውሃ መሠረተ ልማት ኮንስትራክሽን ዘርፍ እየተገነባ የሚገኘው የጊዳቦ ግድብ ሥራ ፕሮጀክት መቶ በመቶ መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ገለጹ።

    የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር አብዱልፈታህ ታጁ በታህሳስ ወር 2011 ዓ.ም. ፕሮጀክቱን ለጎበኙ በኮርፖሬሽኑ የኮርፖሬት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ባለሙያዎች እንደገለጹት የጊዳቦ ዋና ግድብ ሥራ መቶ በመቶ ተጠናቆ በጥር ወር 2011 ዓ.ም እንደሚመረቅ ገልጸዋል።

    የጊዳቦ ግድብ ሥራ ፕሮጀክት በ258 ሚሊዮን ብር በጀት የተጀመረ ቢሆንም ግንባታው በተያዘለት የጊዜ ገደብ ባለመጠናቀቁ እና የዲዛይን ለውጥ በመደረጉ አጠቃላይ የግንባታ ወጭው 1.66 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቀዋል።

    በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በብዛት አክሲዮን በመግዛት እየተሳተፉበት ያለውና ግንባታው እይተፋጠነ ያለው ግዙፉ የአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ የኮንፈረንስ ማዕከል

    የግድቡን ዲዛይንና የቁጥጥር ሥራውን ያካሄደው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይንና ቁጥጥር ኮርፖሬሽን ሲሆን፣ ግንባታውን ደግሞ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን አከናውኖታል።

    የኦሮሚያ እና ደቡብ ክልሎችን በመስኖ ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ የሚጠበቀው የጊዳቦ ግድብ በአጠቃላይ 63.5 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ እና 13,425 ሔክታር መሬት ማልማት ያስችላል የተባለው ይህ የጊዳቦ መስኖ ልማት ግድብ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ሳይጠናቀቅ የዘገየው እና የፕሮጀክቱ የገንዘብ መጠኑ የጨመረው ውሉ ከተፈረመ ከሁለት ዓመታት በኋላ ግንባታው መጀመሩ፣ የዲዛይን ለውጥ መደረጉ፣ በአካባቢው የካሳ ክፍያ የሚጠይቁ ሥራዎች መኖራቸው፣ የባለድርሻ አካላት ችግር፣ በግንባታ ዕቃዎች አቅርቦት እጥረት ምክንያት ነው። ግድቡ የተጀመረው በ2002 ዓ.ም. ሲሆን፥ ሲጀመር ይጠናቀቃል ተብሎ የታቀደው በ2004 ዓም ነብር።

    ግድቡ ሲጀመር ተይዞ የነበረው 16 ሜትር ከፍታ ሲሆን አሁን ላይ ወደ 22.5 ሜትር ከፍታ፣ 315 ሜትር ርዝመትና፣ 7.16 ኪ.ሎ ሜትር ርዝመት ያለው በግድቡ ግራ እና ቀኝ የዋና ቦይ ግንባታ ሥራዎችን መሠራቱ እና በአንድ ሺህ አምሳ ሄክታር መሬት ላይ ውሃ እንዳጠራቀመ (ሰው ሠራሽ ሀይቅ እንደሚኖረው) ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።

    በአሁኑ ወቅት ግንባታው ሙሉ በሙሉ በመጠናቀቁ በሚቀጥለው በያዝነው ወር የፌዴራል፣ የደቡብ እና የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ ባለሥልጣናት በተገኙበት ይመረቃል ተብሎ መርሐ ግብር ተይዟል።

    ምንጭ፦ ኢ.ኮ.ሥ.ኮ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የጊዳቦ ግድብ


    Semonegna
    Keymaster

    አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ከኢትዮጵያም አልፈው በአፍሪካ አህጉር ለረዥም ዓመታት በዲፕሎማትነት ያገለገሉ ግለሰብ ሲሆኑ፥ ለዚህም አገልግሎታቸው እ.ኤ.አ በኅዳር ወር 2015 የአፍሪካ ህብረት የክብር ሽልማት ሸልሟቸዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ለ52 ዓመታት በተለያዩ ሀገራትና ተቋማት ኢትዮጵያን በመወከል በዲፕሎማትነት ያገለገሉት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ላባረከቱት አገልግሎት ከኢፌደሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ዕውቅና ተሰጣቸው።

    አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ የአገልግሎት የክብር እውቅናው በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) የተሰጣቸው ጥር 07 ቀን 2011 ዓ.ም. ነው።

    ይህ ሽልማት አምባሳደሯ ለረጅም ዓመታት በተለያዩ የዓለም ሀገራት፣ በአህጉር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ለኢትዮጵያ ተወካይና ዲፕሎማት በመሆን ላበረከቱት ስኬታማ አገልግሎት እንደተበረከተላቸው የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት (ኤፍ.ቢ.ሲ.) ዘግቧል።

    አምባሳደር ቆንጂት በግብፅ ፣ በእስራኤል፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ሀገራቸውን በዲፕሎማትነት በመወከል ውጤታማ ስራ ማስመዝገባቸው ተገልጿል።

    አምባሳደሯ ከምንም በላይ ሀገራቸውን በማስቀደም በዲፕሎማሲው ዘርፍ ያበረከቱት አስተዋጽዖም ለሌሎቸ ዲፕሎማቶች አርዓያ የሚሆን ነው ተብሏል።

    ለአምባሳደሯ የተሰጣቸውን የክብር እውቅና ተገቢ እንደሆነ በመደገፍ የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በትዊተር ገጻቸው ላይ እንዲህ ብለው ጽፈዋል

    እህቴ፣ ባልንጀራዬ ክብርት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ረዥሙን የአገልግሎት ዘመን የያዙ ዲፕሎማት በዛሬው ዕለት ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር የሚገባቸውን ሽልማትና እውቅና በማግኘታቸው እንኳን ደስ አላቸው! ደስ አለን! አገርን በጨዋነት፣ በታማኝነት፣ በታታሪነት የማገልገል ዋጋ ነው። ለሁሉም በተለይ በዛሬ ጊዜ ትልቅ ትምህርት ልንወስድበት ይገባል።

    አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ለተደረገላቸው እውቅና ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፥ በቅርቡ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ በሀገሪቱ ትልልቅ ቦታዎች ላይ ሴቶች ሹመት እንዲያገኙ መደረጉንም አድንቀዋል።

    በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያን በመወከል የሚሠሩ ዲፕሎምቶችና አምባሳደሮችም ለሀገራቸው ጥቅም ቅድሚያ በመስጠት ሊሠሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።

    አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ የተወለዱት በሐረር ከተማ እ.ኤ.አ. በ1940 ሲሆን፥ በእንግሊዝ ሀገር ለንደን ከተማ ከሚገኘው ለንደን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ እ.ኤ.አ በ1954 ዓለም አቀፍ ግንኙነት (International Relations) በዲግሪ ተመርቀዋል። እ.ኤ.አ በ1963 ኒው ዮርክ ከተማ፣ አሜሪካ ከሚገኘው የኮለምብያ ዩኒቨርሲቲ የካርኒጌ ፌሎውሺፕ (Carnegie Fellowship) አግኝተዋል። ኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተቀጥረው መሥራት የጀመሩት እ.ኤ.አ በ1962፥ ይህም የአፍሪካ አንድነ ድርጅት (የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት) ከመቋቋሙ ከአንድ ዓመት በፊት ነው።

    አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ከኢትዮጵያም አልፈው በአፍሪካ አህጉር ለረዥም ዓመታት በዲፕሎማትነት ያገለገሉ ግለሰብ ሲሆኑ፥ ለዚህም አገልግሎታቸው እ.ኤ.አ በኅዳር ወር 2015 የአፍሪካ ህብረት የክብር እውቅና ሰጥቷቸዋል

    የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከአምባሳደር ቆንጂት በተጨማሪም በተለያዩ ሀገራት በአምባሳደርነት ሲሠሩ ቆይተው በጡረታ ለተሰናበቱ ቀደምት ዲፕሎማቶች የዕውቅና ምስክር ወረቀት ሰጥቷል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ


    Semonegna
    Keymaster

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ጥር 6 ቀን ለኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች በሰጡት ገለጻ አስካሁን ባለው ሂደት ኢትዮጵያዊያን ዳያስፖራዎች በቀረበላቸው ሀገራዊ ጥሪ አማካኝነት በዳያስፖራ ትረስት ፈንድ በኩል 1 ነጥበ 9 ሚሊዮን ዶላር አዋጥተዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – በዳያስፖራ ትረስት ፈንድ አንድ ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ዶላር መሰብሰቡን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ጥር 6 ቀን 2011 ዓ.ም. አስታወቁ። እስካሁን ባለው ሂደት በትረስት ፈንዱ አማካኝነት 12 ሺህ 9 መቶ ዳያስፖራዎች መዋጮ አድርገዋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው የ2011 ዓ.ም. አገራዊ በጀትን በአስጸደቁበት ወቅት ኢትዮጵያዊ ዳያስፖራ ሁሉ በአገሩ ልማት ላይ እንዲሳተፍ በቀን የ1 ዶላር መዋጮ መጠየቃቸው ይታወሳል። ይሁን እንጂ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ዳያስፖራው ለጠቅላይ ሚነስትሩ የሰጠው ምላሽ አጥጋቢ እንዳልሆነ ሲነገር ቆይቷል።

    Commercial Bank of Ethiopia to start diaspora mortgage loan to ease Ethiopians’ home ownership

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ጥር 6 ቀን ለኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች በሰጡት ገለጻ አስካሁን ባለው ሂደት ዳያስፖራው በቀረበለት ፈንድ አማካኝነት 1 ነጥበ 9 ሚሊዮን ዶላር አዋጥቷል።

    በመዋጮውም 12 ሺህ 900 ዳያስፖራዎች እንደተሳተፉ የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ከዚህም ውስጥ 10 ሺህ 300 የሚሆኑት በአሜሪካ የሚኖሩ ናቸው። 1ነጥብ 6 ሚሊዮን ዶላሩ ከእነዚህ በአሜሪካ ከሚኖሩ ዳያስፖራዎች መሰብሰቡን አክለዋል።

    በአሜሪካ ካሉ ግዛቶች መካከል ሜሪላንድና ካሊፎርኒያ እንደቅደም ተከተል ከፍተኛ መዋጮ የተገኘባቸው አካባቢዎች መሆናቸውንም ገልጸዋል።

    በዓለም ላይ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዳያስፖራዎች ቢኖሩም መዋጮው እምብዛም ያልሆነበት ምክንያት መተማመኑ ባለመፈጠሩ መሆኑንም ጠቅላይ ሚንስትሩ አስገንዝበዋል።

    The case of Ethiopian diaspora, their interest to invest in Ethiopia and bureaucratic bottlenecks

    የሚዋጣውን ነገር በሚታይ ነገር ላይ በማዋል መተማመንን ለመፍጠር እንደሚሠራ የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በፈንዱ የተሰበሰበው ገንዘብ ግን 10 ሚሊዮን ዶላር አስኪደርስ ጥቅም ላይ እንደማይውል ገልጸዋል።

    ይህ የሚሆነውም በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች መካካል ፍትሃዊ ክፍፍልን ለመፍጠር መሆኑንም ጠቁመዋል።

    የኢትዮጵያውያን ዳያስፖራ ትርስት ፈንድ የተቋቋመው በነሀሴ ወር 2011 ዓ.ም. በጠቅላይ ሚኒስትሩ ዋና ሰብሳቢነት ሲሆን፥ በዋነኝነት በተለያዩ የአርሜሪካ ግዛቶች የሚኖሩ 15 ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በአማካሪ ካንስል አባልነት ያቀፈ ቡድን በበላይነት ይከታተለዋል።

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ ድረ-ገጽ: EDTF

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ዳያስፖራ ትርስት ፈንድ


    Semonegna
    Keymaster

    ቤልካሽ ኢትዮጵያ የሚያስጀምራቸው ሄሎማርኬት እና ሄሎሾፕ የተሰኙ ሁለት የኤሌክትሮኒክስ መገበያያ ገፆች በኢትዮጵያ ውስጥ እና ከኢትዮጵያ ውጪ ለሚገኙ ተገልጋዮች ኢንተርኔት አማካኝነት ግብይት መፈም የሚችሉባቸው ናቸው።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ቤልካሽ ኢትዮጵያ ተጠቃሚዎች በበይነመረብ (ኢንተርኔት) አማካኝነት ግብይት መፈም የሚችሉባቸው ሁለት የኤሌክትሮኒክስ መገበያያ ገፆችን በቅርቡ እንደሚያስጀምር አስታወቀ።

    ሄሎማርኬት (Hellomarket) የተሰኘው ገፅ በዋነኛነት በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚገኙ ተገልጋዮቹ ብቻ ካሉበት ቦታ ሆነው ቁሳቁሶችን የሚሸምቱበት አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን በበይነመረብ አማካኝነት የግዥ ትዕዛዝ እና ክፍያ የተፈፀመባቸው ቁሳቁሶቹን ወደ ደምበኞች ለማጓጓዝም ከ ዓለምአቀፉ ዲኤችኤል (DHL) ጋር ስምምነት ተፈራርሟል።

    The dispute between RIDE Taxi, Ethiopian-kind of Uber, and Addis Ababa Transport Authority continues

    ተቋሙ በመጀመርያው ምዕራፍ ወደ 2,500 የሚጠጉ ሴት ኢትዮጵያውያን በባለቤትነት በሚያስተዳድሩዋቸው የተለያዩ ድርጅቶች የተመረቱ ምርቶችን ለማሻሻጥ ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል።

    በተመሳሰይ ቤልካሽ ከኢትዮጵያ ውጭ ሆነው የኤሌክትሮኒክ ግብይት መፈፀም ለሚፈልጉ ደንበኞቹ አገልግሎት የሚሰጥ ሄሎሾፕ (Helloshop) የተሰኘ ሌላ ገፅ ያዘጋጀ ሲሆን የክፍያ ስርዓቱም በማስተር ካርድ አማካኝነት አንደሚከወን ለማወቅ ተችሏል።

    Ethiopia – blueMoon Incubator and Addis Garage co-working space for startups in Ethiopia

    ቤልካሽ ኢትዮጵያ መቀመጫውን ኔዘርላንድ ባደረገው እና ቤልካሽ ቴክኖሎጂ ሶሉሽን (Belcash Technology Solutions) የተሰኘ በኤሌክትሮኒክ ክፍያ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ላይ የተሰማራ ድርጅት እህት ኩባንያ ሲሆን እ.ኤ.አ ከ2011 ጀምሮ በኢትዮጵያ በተለይም በሞባይል ክፍያ እና የገንዘብ ማስተላለፍ ዘርፎች ላይ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ከኩባንያው ድረገፅ የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

    የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ሥርዓት በተገቢው አለመስፋፋት እና በዚህ ዘርፍ ላይ ግልፅ የሆኑ ፖሊሲዎችን አለመኖራቸው በኢትዮጵያ መሰል የኤሌክተሮኒክ ግብይት ተቋማት እንዳይስፋፉ እንቅፋት መሆኑን ባለሞያተኞች ይገልፃሉ።

    ከዚህ ዜና ጋር በተመሳሳይ የቻይናው ግዙፉ የኤሌክትሮኒክስ መገበያያ (e-commerce) አሊባባ ኢትዮጵያ ውስጥ ገብቶ ለመሥራት ፍላጎት እንዳለውና ከኢትዮጵያ ባላስልጣናት ጋር (የቀድሞ የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመን ጨምሮ) መወያየቱን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቦ ነበር

    ምንጭ፦ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ / አዲስ ፎርቹን
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ቤልካሽ ኢትዮጵያ


    Anonymous
    Inactive

    እሁድ ጥር 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ሁለተኛው ዙር ከትራፊክ ፍሰት ነፃ መንገዶች ቀን (car free day) በአዲስ አበባ፣ ባህር ዳር፣ ሀዋሳ፣ ጅማ፣ መቀሌ፣ ጅጅጋ እና ድሬደዋ በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል።

    የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    እንደ ፕሮፈሰር ጣሰው ወልደሃና ገለጻ፥ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባለፉት ስድስት ወራት በተጽዕኖ የሚካሄዱ የፖለቲካ አሠራሮችን በማጽዳትና የፖለቲካ ሃሳቦችን በነጻ የሚያራምዱበት የጋራ መድረክ በማዘጋጀት የተሻለ ሰላም ማምጣት ችሏል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ከፖለቲካ ተጽዕኖ በማላቀቅ በሰላም አብሮ የመኖር ባህልን ማሳደግ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፈሰር ጣሰው ወልደሃና ተናገሩ።

    ዩኒቨርሲቲው ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ”ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሰላም” በሚል ጥር 4 ቀን 2011 ዓ.ም. መክረዋል።

    ፕሮፌሰር ጣሰው በዚሁ ወቅት፥ የሰላማዊ አብሮ የመኖር ባህልን በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለማሳደግ ተማሪዎችን ከፖለቲካ እንቅስቃሴና ፉክክር ነጻ ማድረግ ይገባል። ባለፉት ዓመታት ሰላም ላይ ትኩረት ተደርጎ ባለመሠራቱ ተማሪዎች በዘር የመከፋፈልና እርስ በእርስ ያለመታማመን ችግሮች አጋጥሟቸዋል። ይህም በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ግጭትና ሁከትን በመቀስቀስ የመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ ያመጣው አሉታዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ ነው ብለዋል።

    ተማሪዎችና መምህራን በፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ የሚያደርጉት ፉክክርና አንዳንድ ድርጅቶችም የፖለቲካ እንቅስቃሴያቸውን ያለገደብ በተቋማቱ ማራመዳቸው የተማሪዎችን አብሮነት እንደሸረሸረውም ነው ፕሮፌሰሩ ያብራሩት። የዩኒቨርሲቲዎች ዋነኛ ተግባር ማስተማርና መመራመር መሆኑን አጽንዖት ሊሰጡት እንደሚገባም አመልክተዋል።

    ትውልድን በመቅረጽ፣ አገርን በመገንባት በኩል መምህራን የበኩላቸውን አስተዋጽዖ መወጣት ይጠበቅባቸዋል ― ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ

    እንደ ፕሮፈሰሩ ገለጻ፥ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባለፉት ስድስት ወራት በተጽዕኖ የሚካሄዱ የፖለቲካ አሠራሮችን በማጽዳትና የፖለቲካ ሃሳቦችን በነጻ የሚያራምዱበት የጋራ መድረክ በማዘጋጀት የተሻለ ሰላም ማምጣት ችሏል።

    ዩኒቨርሲቲው በሰላም ዙሪያ የሚመራመርና ሃሰቦችን የሚያፈልቅ አስር አባላት ያሉት ቡድን አዋቅሮ በተቋሙ ቀጣይነተ ያለው ሰላም ለማምጣት እየሠራ ነውም ብለዋል – ፕሮፌሰር ጣሰው። ለቡድኑም አንድ ሚሊዮን ብር ዩኒቨርሲቲው መመደቡን አስታውቀዋል።
    ሌሎችም ዩኒቨርሲቲዎች ይህንን ተሞክሮ በማስፋት ለአገር ሰላምና ለአብሮነት የሚያደርጉትን ጥረት ማጠናከር እንዳለባቸውም ተመላክቷል።

    በመድረኩ “ሰላምና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት” በሚል ጽሁፍ ያቀረቡት በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር ፕሮፌሰር ካሳሁን ብርሃኑ በበኩላቸው ሰላምን ለማስፈን ተቋማቱን ከፖለቲካ ተጽዕኖ ነጻ ማድረግ ተቀዳሚ ተግባር ሊሆን ይገባል።

    በተለይ በተቋማቱ የሰላም እጦት መንግስትና ምሁራን በሰላም ላይ ያልተገበሯቸው በርካታ ተግባራት ለመኖራቸው ዋቢ ነው ብለዋል – ፕሮፈሰሩ።

    በቀጣይም ኢትዮጵያዊ አብሮነትን ያካተተ መርሃ ግብር በመቅረጽ፤ በጎሳና በዘር የተከፋፈለውን የምደባ ስርዓት በመከለስ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የፌዴራል ተቋማት መሆናቸውን ማጉላትና የተማሪዎች ህብረትን ከፖለቲካ የጸዱ ማድረግ ይገባል ብለዋል። አክለውም ምሁራን የግጭት አራጋቢዎች ከመሆንና የሥራ መርሃ ግብራቸውን በአግባቡ ካለመወጣት ተቆጥበው ትውልድ የመቅረጽ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

    የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አልማዝ መኮንን እንዳሉት ምሁራን ለሀገሩ ቀና የሆነ ዜጋንና ስለአገሩ ሰላምና ዲሞክራሲ የሚተጋ ዜጋን የማፍራት ኃላፊነት እንዳለባቸው በመጥቀስ፥ በተለይ ምሁራን አገሪቷ አሁን ከገጠማት የሰላም እጦት ለመውጣት ሙያዊና የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

    ለአንድ ቀን ብቻ በተደረገው የምከክር መድረኩ ላይ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተወከሉ መምህራን፣ የተማሪዎች መማክርት፣ የሰላም መልዕክተኞችና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ጣሰው ወልደሃና


    Semonegna
    Keymaster

    አል ማክቱም ፋውንዴሽን በየካ ክፍለ ከተማ ካስገነባው ትምህርት ቤት በተጨማሪ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማም በተመሳሳይ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው አፋን ኦሮሞ የሆኑ ተማሪዎች የሚማሩበት ትምህርት ቤት አስገንብቷል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ተቀማጭነቱን በዱባይ ከተማ ያደረገው አል ማክቱም ፋውንዴሽን የተባለ የተባበሩት አረብ ኤምሬት ግብረ ሰናይ ድርጅት በአርባ ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው ትምህርት ቤት ታህሳስ 30 ቀን 2011 ዓ.ም. ተመርቋል። ግብረ ሰናይ ድርጅቱ እስከ አሁን በኢትዮጵያ አራት ትምህርት ቤቶችን ማስገንባቱን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዘግቧል።

    ትምህርት ቤቱ በየካ ክፍለ ከተማ በተለምዶ አያት አደባባይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኝ ሲሆን የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው አፋን ኦሮሞ የሆኑ ተማሪዎች የሚማሩበት ነው።

    የትምህር ቤቱ የግንባታና የቁሳቁስ ወጪ በግብረ ሰናይ ድርጅቱ የተሸፈነ ሲሆን ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የአስተማሪዎችን ሙሉ የደመወዝ ክፍያም በድርጅቱ የሚሸፈን ይሆናል።

    ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በትምህርታቸው የላቀ ውጤት ለሚያመጡ ተማሪዎችም ሱዳን በሚገኘው ‘ኢንተርናሽናል ዩኒቨርሲቲ ኦፍ አፍሪካ’ በተሰኘው ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት የነፃ የትምህርት ዕድል ተጠቃሚ እንደሚሆኑም የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ታቦር ገብረመድህን በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተናግረዋል።

    በተጨማሪም ለመምህራን የትምህርት ዕድል ለመስጠትና ከሌሎች የአፍሪካ አገራት ጋር የመምህራን የልምድ ልውውጥ ለማድረግ መታቀዱንም ጠቁመዋል። የትምህርት ቤቱን የቅበላ አቅም ለማሳደግ የማስፋፊያ ሥራ ለመሥራት ዝግጅት መጠናቀቁንም ዶ/ር ታቦር ተናገረዋል።

    የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ከድር ጃርሶ በበኩላቸው ትምህርት ቤቱ የአፍ መፍቻቸው አፋን ኦሮሞ ለሆኑ እና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ወላጆች ልጆች የትምህርት ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ብለዋል። እንዲሁም ትምህርት ቤቱ በአካባቢው መከፈቱ ለበርካታ ሥራ አጥ ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል።

    የአል ማክቱም ፋውንዴሽን የኮሙኒኬሽን ባለሙያ አቶ አብዱልሸኩር መንዛ እንዳሉት ግብረ ሰናይ ድርጅቱ በኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፍ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ በማጠናከር በሌሎች ዘርፎች ለመሥራትም ዕቅድ አለው።

    ግብረ ሰናይ ድርጅቱ በኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፍ መጠናከር የአገሪቱ መንግስት ላደረገው ቀና ትብብርም አቶ አብዱልሸኩር አመስግነዋል።

    አል ማክቱም ፋውንዴሽን በየካ ክፍለ ከተማ ካስገነባው ትምህርት ቤት በተጨማሪ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማም በተመሳሳይ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው አፋን ኦሮሞ የሆኑ ተማሪዎች የሚማሩበት ትምህርት ቤት አስገንብቷል።

    በሁለቱም ክፍለ ከተሞች የተገነቡት ትምህርት ቤቶች በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ስር እንዲተዳደሩ የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ አስረክቧል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አል ማክቱም ፋውንዴሽን


    Semonegna
    Keymaster

    በአስር ሺህ ካሬ ሜትር ላይ በ58 ሚሊዮን ብር ወጪ በአዳማ ከተማ የተገነባዉ ጊዜ ያለፈባቸው እና ጥቅም ላይ የማይውሉ መድኃኒቶችን ማስወገጃ ማዕከል 10 ሺህ ኪሎ ግራም በሰዓት የማቃጠል አቅም ያለው ሲሆን፥ በሌሎች 7 ከተሞችም 500 ኪሎ ግራም በሰዓት ማቃጠል የሚችሉ ማዕከላትም በመገንባት ላይ ይገኛሉ።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ የመድኃኒት ፈንድና አቅርቦት ኤጀንሲ በ100 ቀናት ዕቅድ የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው እና በተለያዩ ምክንያቶች ጥቅም ላይ የማይውሉ መድኃኒቶችን እና የህክምና ግብአቶችን ማስወገጃ ማዕከል ገንብቶ አስመረቀ።

    በአስር ሺህ ካሬ ሜትር ላይ በ58 ሚሊዮን ብር ወጪ በአዳማ ከተማ የተገነባዉ ጊዜ ያለፈባቸው እና ጥቅም ላይ የማይውሉ መድኃኒቶችን ማስወገጃ ማዕከል (incinerator) ምረቃ ሥነ ስርዓትላይ የተገኙት የኢፌዴሪ የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን እንደተናገሩት፥ ማዕከሉ 10 ሺህ ኪሎ ግራም በሰዓት የማቃጠል አቅም ያለው ሲሆን፥ በሌሎች 7 ከተሞችም 500 ኪሎ ግራም በሰዓት ማቃጠል የሚችሉ ማዕከላትም በመገንባት ላይ ይገኛሉ ብለዋል። በቅርቡም ግንባታቸው ተጠናቆ አገልግሎት እንደሚጀምሩ ዶ/ር አሚር አክለው ተናግረዋል።

    ጊዜ ያለፈባቸው መድኃኒቶች እና ግብዓቶች ማስወገጃ ማዕከሉ ለሀገራችን የመጀመሪያ ሲሆን ከዚሀ ቀደም በየተቋሟቱ በተለያዩ ምክንያቶች ጥቅም ላይ የማይውሉ ወይም የተበላሹ መድኃኒቶችን በማስወገድ ረገድ ይገጥሙ የነበሩ ችግሮችን ከመሠረቱ እንደሚፈታ የገለጹት ሚኒስትሩ፥ የምለሳ ሎጂስቲክ (recycle logistic) ስርዓትን በመተግበር የማያገለግሉ የህክምና ግብአቶች እና በባኅሪያቸው ጎጂ የሆኑ ኬሚካሎችን በዘመናዊ መንገድ አካባቢን በማይበክል ሁኔታ በማስወገድ ከዚህ ቀደም አካባቢ የሚበከልበትን ሁኔታ እንደሚያስቀር ተናግረዋል።

    የኢትዮ-አሜሪካውያን ዶክተሮች ቡድን እያስገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አገልግሎት ይሰጣል ተብሎ የሚጠበቀው ሆስፒታል

    ለዚህ ሥራ መሳካት ተባባሪ የሆኑ ያካባቢው ማኅበረሰብ አባላትና የአዳማ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤትን ያመሰገኑት ሚኒስትሩ፥ ማዕከሉ ለአካባቢ ነዋሪዎች ቅድሚያ ተጠቃሚ የሚያደረግ ስልጠናና የሥራ ዕድል በኤጀንሲው እንዲመቻችላቸውም ተናግረዋል።

    የኢትዮጵያ የመድኃኒት ፈንድና አቅርቦት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬከተር ዶ/ር ሎኮ አብርሀም በበኩላቸው የአዳማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በሌላው ዓለም የሚተገበሩ ዘመናዊ አሠራሮችን በመቀመር የመድኃኒት እና የህክምና መገልገያ አቅርቦት እና ስርጭት የልህቀት ማዕከል ሆኖ ለሌሎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች መማማሪያ እንዲሆን ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን ተናግረው ለአካባቢው፥ ማኅበረሰብም የሥራ ዕድል እየፈጠረ እንደሆነ እና በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    መድኃኒቶችን ማስወገጃ


Viewing 15 results - 391 through 405 (of 495 total)