Search Results for 'አዲስ አበባ'

Home Forums Search Search Results for 'አዲስ አበባ'

Viewing 15 results - 436 through 450 (of 495 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    ዶ/ር ሂሩት ወልደማርያም በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በአማራ እና በኦሮሞ ብሄር ተማሪዎች መካከል በተነሳው ግጭት የሶስት ተማሪዎች ህይወት ማለፉን ገልፀው፥ የተለየ ፍላጎት ያላቸው ኃይሎች በተማሪዎች መካከል የብሄር ግጭት እንዲነሳ በማድረግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከማስተጓጎል በላይ ለስው ህይወት መጥፋት ምክንያት መሆናቸውን ተናግረዋል።

    አዲስ አበባ (የትምህርት ሚኒስቴር) – በዩኒቨርሲቲዎች ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር አጠቃላይ ማህበረሰቡ ከአካባቢው አስተዳደር ጋር በጋራ እንዲሠራ ተጠየቀ።

    በአሁኑ ወቅት በመላ ሃገሪቱ እየተካሄደ የሚገኘውን ለውጥ ለመቀልበስ የሚፈልጉ ኃይሎች ፊታቸውን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም በማዞር ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደቱን በማወክና ግጭቶች እንዲፈጠሩ በማድረግ ግጭቶቹም የብሄር ግጭት መልክ እንዲይዙ በማድርግ ከፍተኛ ሁከት እና አለመረጋጋት በዩኒቨርሲቲዎች እንዲቀሰቀስ እያደረጉ መሆኑ ተደርሶበታል።

    ይህንኑ ሰሞኑን በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች የተከሰተውን አለመረጋጋትና ሁከት አስመልክቶ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትሯ ዶ/ር ሂሩት ወልደማርያም ኅዳር 12 ቀን 2011 ዓ.ም በፅህፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ “ዩኒቨርሲቲዎች ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ የተለያየ አስተሳሰብና ክህሎት ያላቸው ወጣቶች የተሰባሰቡበት ቦታ መሆኑን ገልፀው፥ እነዚህን ወጣቶች ለተለያየ የፖለቲካ አጀንዳ ማስፈፀሚያ ለማድረግና እርስ በእርሳቸው ያለመተማመንና በመካከላቸውም የብሄር ግጭት በማስነሳት የመማር ማስተማር ሥራውን ከማስተጓጎላቸውም በላይ በግጭቱ ውድ የሆነውን የሰው ህይወት እንዲጠፋ ምክንያት ሆነዋል“ ብለዋል።

    ዶ/ር ሂሩት አያይዘውም ሰሞኑን በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በአማራ እና በኦሮሞ ብሄር ተማሪዎች መካከል በተነሳው ግጭት የሶስት ተማሪዎች ህይወት ማለፉን ገልፀው፥ በግጭቱ ህይወታቸውን ላጡ ውድ ተማሪዎቻችን የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገልፀው ለተማሪ ቤተሰቦችና ለማህበረሰቡ መፅናናትንም ተመኝተዋል።

    አሁን የሚስተዋለውን ችግር ለመፍታትም ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች፤ የዩኒቨርሲቲ ቦርድ አባላት፤ የሁለቱም ብሄር ተወካዮችና ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ጋር በመሆን የዕርቅና ሰላም የማስፈን ሥራ ለመሥራት ወደ ዩኒቨርሲቲው እንደሚሄድ ሚኒስትሯ ጨምረው ገልፀዋል።

    ዩኒቨርሲቲዎች የዕውቀት የክህሎትና የአዳዲስ ሃሳቦች ማፍለቂያ ተቋሞች መሆናቸውን የገለፁት ሚኒስትሯ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ሙሉ ጊዜያቸውን ለትምህርትና ለምርምር በማዋል የመጡበትን ዓላማ ማሳካትና በቆይታቸውም ነገሮችን በደንብ የሚያስቡና አንዳንድ ወደ ጥፋት የሚሄዱ ተማሪዎችንም ወደ በጎነት የሚመልሱ ሊሆኑ እንደሚገባቸው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

    በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምቹና ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር የአካባቢው ማህበረሰብ የአስተዳደር አካላትና የፀጥታ አካላትም በጋራ ሊሠሩ እንደሚገባ በመግለጫው ተካቷል።

    ምንጭ፦ የትምህርት ሚኒስቴር

    ተጨማሪ ትምህርት ተኮር ዜናዎች

    የመማር ማስተማር ሂደት

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ኤግል ሒልስ)–በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የበላይ ጠባቂነት በአዲስ አበባ ለገሀር አከባቢ ሥራዉን ለመጀመር ዝግጅቱን ያጠናቀቀዉ የዱባይ አቡዳቢው ኤግል ሒልስ (Eagle Hills) በአዲስ አበባ ለገሀር የተቀናጀ የመኖሪያ፣ አገልግሎት መስጫና የመዝናኛ ስፍራ ልማት ሥራውን በይፋ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ በተገኙበት ኅዳር 10 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀመረ።

    ይህ በ360,000 ሜትርካሬ መሬት ላይ የሚያርፈዉ የለገሀር የተቀናጀ የልማት ኘሮጀክት የአዲስአበባን መሀል ከተማ ወካይ ሆኖ በዉስጡ ከ4000 በላይ መኖሪያ ቤቶች፣ የመዝናኛ ስፋራዎች፣ ግዙፍ የንግድ ማዕከላት፣ መጋቢና ዋና መንገዶች እና ሌሎች ዘመናዊ አገልግሎት መስጫ ስፍራዎች ይኖሩታል ።

    ከቦሌ ዓለም አቀፍ አዉሮፕላን ማረፊያ በቅርብ ርቀት የሚሠራው ይህ ሁለገብ መንደር እንዲሁም ባለ አምስት ኮከብ ሆቴሎች፣ አረንጓዴ መዝናኛ ስፍራዎች፣ ምቹና ሰፋፊ የእግረኛ መንገዶች እና የመኪና ማቆሚያ ስፍራዎች በበቂ ሁኔታ በዉስጡ እንዳካተተም ማስተር ኘላኑ ያመለክታል።

    ኘሮጀክቱ በኢትዮጵያ መንግስት እና በዱባዩ ኤግል ሒልስ ትብብር የሚሠራ ሲሆን ነዋሪዎች አሁን ባሉበት ቦታ መኖርያ ቤት ተገንብቶላቸዉ በዘላቂነት በሚያዉቁት ቀዬ እንዲኖሩም ይደረጋል።

    ስለ ኘሮጀክቱ ፋይዳ ሲናገሩ የኤግል ሒልስ ሊቀ መንበረ ሞሀመድ አልባረ፥ “እንደ አንዷ የአፍሪካ ዕንቁዎች ኢትዮጵያ በባህል፣ ታሪክ እና የተፈጥሮ ዉበት የበለፀገች ነች፤ ስለዚህ የእኛ ፍላጎት እንዲህ ዉብ ከሆኑት የሀገሪቱ ትሩፋቶች አንዱ የሆነውን በአዲስ አበባ የለገሀር አካባቢን አልምቶ ዓለም እንዲያውቀው እና ሰዎች ከተለያየ የዓለም ክፍል ኢትዮጵያን መዳረሻቸው አድርገው ሁሉ ነገር የተሟላለት መንደር መኖር፣ መዝናናት እና መገብየት እንዲችሉ ማድረግም ጭምር ነው። ከዚህ በተጨማሪም ይህ ኘሮጀክት ለአከባቢዉ ነዋሪዎችም ሆነ ለሌሎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የሀገሪቱን ኢኮኖሚ የበለጠ የማነቃቃት ሰፊ ሚና ይኖረዋል።” ብለው የዚህን ዘመናዊ ኘሮጀክት ሰፊ ጥቅም አስረድተዋል።

    Addis Ababa City Administration to transfer more than 17 thousand 40/60 condominiums houses

    ለገሀር ከፈረንሳይኛ ቋንቋ የተወሰደ ሲሆን ትርጓሜዉም የባቡር ጣቢያ ማለት ነው ይኸውም የባቡር ጣቢያ በአዲስ አበባ ዋነኛ ጣቢያ በመሆን ለዘመናት አገልግሏል። በአዉሮፓውያን የዘመን ቀመር በ1917 የተጠናቀቀው ጣብያዉ ለከተማዋ ብሎም ለኢትዮጵያ ዋነኛው የባቡር ትራንስፖርት ማዕከልም ነበር።

    አዲሱ የለገሀር ፕሮጀክትም በዉስጡ በጥልቅ የኪነ ህንፃ ጥበብ የሚሠሩ ለቢሮ አገልግሎት የሚዉሉ ህንፃዎች ሲኖሩት በቅርብ ርቀትም ባለ አራት እና አምስት ኮከብ ሆቴሎች ይገኛሉ።

    የአቡዳቢዉ ኤግል ሒልስ ትልልቅ የተቀናጀ የመኖሪያ መንደሮች ግንባታ ድርጅት ሲሆን በተለያዩ ሀገሮች ብዙ ቁጥር ያላቸው መንደሮችን ገንብቷል። ይህ ኩባንያ ተመሳሳይ መንደሮችን በዓለም ዙሪያ ለመገንባት አቅዶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።

    ኤግል ሒልስ በኢትዮጵያ (በአዲስ አበባ ለገሀር የመኖሪያ ቤቶች ፕሮጀክት)

    ኤግል ሒልስ በኢትዮጵያ የግል የመኖሪያ ቤቶች አልሚ ድርጅት ሲሆን ትልልቅ እሴት ያላቸው ግንባታዎች ላይ ተሳትፎ በማድረግ የሃገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት በማፋጠን ረገድ የግሉን ድርሻ አበርክቶ ለማኅበራዊ እና ኢኮኖሚ እድገት አስተዋጽኦ ያበረክታል።

    ይህ በዉበቱ እና ዘመናዊነቱ የላቀ እንደሚሆን የተነገረለት መንደር በዘርፉ ከፍተኛ እውቀት አና ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች የሚሠራ ከመሆኑም ባሻገር የአካባቢዉን አረንገጓዴነትና እና ለመኖሪያ ምቹነት ባገናዘበ መልኩ ይገነባል።

    በ360,000 ሜትር ካሬ ቦታ ላይ የሚያርፈው ፕሮጀክቱ የአነስተኛ ንግድ ስፍራዎችንም በዉስጡ የያዘ ሲሆን ዙሪያውም በመናፈሻ ፓርክ የተከለለ ነው ።

    ፕሮጀክቱ ሰፋፊ የሥራ ዕድሎችን ከመፍጠሩም ባሻገር በሀገሪቱ ያሉትን የንግድ እንቅስቃሴዎች በእጅጉ ይደግፋል። የለገሀር የመኖሪያ ቤቶች ፕሮጀክት ድረ ገጽ

    ምንጭ፦ ኤግል ሒልስ

    ለገሀር የመኖሪያ ቤቶች ፕሮጀክት

    Semonegna
    Keymaster

    ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ የያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ከተከፈተበት ከ1959 ዓ.ም. ጀምሮ ተቋሙንም በመምራት እንዲሁም ታላላቅ ባለሙያዎችን በማፍራት ለሙዚቃ ዕድገት አስተዋፅዖው የጎላ መሆኑን ለተሳታፊዎች አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት አውስቷል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)–በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ሥር ያለው የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ የሥነ-ጥበባት ማዕከል 40ኛ የጥበብ ውሎ መድረኩን ቅዳሜ ኅዳር 8 ቀን 2011 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ አካሒዷል።

    በዝግጅቱ ላይ የዕውቁ ኢትዮጵያዊ የሙዚቃ ሰው የፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ ሕይወትና ሥራዎች ላይ ውይይት እየተደረገ ተደርጓል። ሥራዎቹን እና ሕይወቱን አስመልክቶ የሙዚቃ ባለሙያ እና በቅርቡ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት ዳይሬክተር ጀነራል ሆኖ የተሾመው አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት የውይይት መነሻ ጥናት አቅርቦ በታዳሚዎች ውይይት ተካሂዶ ነበር።

    “ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ <ባለዋሽንቱ እረኛ>(The Shepherd Flutist)  በተሰኘ ታላቂ ሥራ የኢትዮጵያን መልክ በረቂቅ ሙዚቃ ያሳዩ ናቸው” በማለት አቶ ሠርፀ የገለጿቸው የሙዚቃውን ረቂቅነት በመጥቀስ ሲሆን፤ ፕሮፌሰር አሸናፊ የያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ከተከፈተበት ከ1959 ዓ.ም. ጀምሮ ተቋሙንም በመምራት እንዲሁም ታላላቅ ባለሙያዎችን በማፍራት ለሙዚቃ ዕድገት አስተዋፅዖው የጎላ መሆኑን ለተሳታፊዎች አውስቷል።

    በሙዚቃ ላይ ከሠሯቸው ከበርካታ የምርምር ሥራዎቻቸው ውስጥ “Roots of Black Music” የተሰኘው መጽሐፋቸው በብዙ የዓለማችን የሙዚቃ አጥኚዎች የተዘነጉ (የተዘለሉ) የአፍሪካ/የምሥራቁ ዓለምን የሙዚቃ ስልትና ፍልስፍናን አጉልተው ለተቀረው ዓለም ያሳዩበት እንደሆነም አቅራቢው አብራርተዋል።

    በውይይቱም ከተሳታፊዎች የኢትዮጵያ ሙዚቃ በዘመናት መካከል የመድመቅና መልሶ የመደብዘዝ ችግር ከምን የመነጨ እንደሆነ ጥያቄ የቀረበ ሲሆን፥ “ዋናው ችግር በተለያዩ ምክንያቶች የኢትዮጵያ ሙዚቃ ተቋም ፈርሷል፤ እሱን መልሶ መገንባት የቤት ሥራችን ነው” ብለዋል አቶ ሠርፀ። አክለውም የኢትዮጵያ የሙዚቃ ትምህርት ሥርዓት ከተመሠረተበት ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ከምዕራባውያን የሙዚቃ ሥርዓተ-ትምህርት ነፃ መውጣት ያለመቻሉም ሌላ ምክንያት እንደሆነ አቅራቢው ጠቅሰዋል።

    ውይቱን የመሩት የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ የሥነጥበባት ማዕከል ዳይሬክተር አቶ እንዳለጌታ ከበደ በበኩላቸው ለኢትዮጵያ ሥነ ጥበብ ማደግ ብርቱ ጥረት ያደረጉ የጥበብ ሰዎችን ፈለግ እና ሥራዎቻቸውን ለተተኪው ትውልድ ለማውረስ በሁሉም አካላት ጥረት መደረግ አለበት ብለዋል።

    ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት 8 ቀን 1930 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው፣ እናታቸው ደግሞ ወ/ሮ ፋንታዬ ነከሬ ያባሉ ነበር። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ቢሆኑም ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እናታቸውን በሞት አጥተዋል።

    ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (አሁን ኮከበ ጽባሕ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት የሚባለው) ካጠናቀቁ በኋላ ከሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከዚያም ወደ አሜሪካ በማቅናት ኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ሮቸስተር፣ ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት (University of Rochester’s Eastman School of Music) በ1954 ዓ.ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ በመመለሰ የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤትን መሥርተዋል። የትምህርት ቤቱም የመጀመሪያው ዳይሬክተር ከመሆናቸውም ባሻገር በመሆን ሙዚቃን ከማስተማሩ ባሻገር አገልግለዋል። በተጨማሪም በአዲስ አበባ የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ.)፣ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር።

    በድጋሚ ለከፍተኛ ትምህርት ወደ አሜሪካ ተመልሰው፣ ኮነቲከት ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው ዌስልያን ዩኒቨርሲቲ (Wesleyan University) በ1961 ዓ.ም የማስትሬት፣ እንዲሁም በ1963 ዓ.ም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ምዕራባዊ ባልሆኑ ሙዚቃዎች ምርምር (ethnomusicology) አግኝተዋል።

    ከሙዚቃው መምህርነትና ተመራማሪነት ባሻገር ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ ደራሲም ነበሩ። እ.ኤ.አ በ1964 ዓ.ም ኮንፌሽን (Confession)፣ እ.ኤ.አ በ1982 ዓ.ም ሩትስ ኦፍ ብላክ ሙዚክ (Roots of Black Music) የሚሉ መጻሕፍትን ያሳተሙ ሲሆን፣ በሙዚቃ ላይ ያተኮሩ በርካታ ጽሁፎችን፥ በተለይም ደግሞ በአፍሪካ-አሜሪካውያን ባህልና አኗኗር ላይ ለሚያተኩረው “The Chronicler” ለተሰኘው መጽሔት ጽፈዋል።

    በአሜሪካ ፕሮፌሰር አሸናፊ ኑሯቸው ፍሎሪዳ ክፍለ ሀገር በሚገኘው ፍሎሪዳ ስቴት ዩኒቨርሲቲ (Florida State University) የሙዚቃ ኮሌጅ ውስጥ በመምህርነት የሠራ ሲሆን፣ ተቀማጭነቱን እዚያው አሜሪካ ያደረገውናታዋቂውን የኢትዮጵያ ምርምር ካውንስልን (Ethiopian Research Council) በዳይረክተርነት መርቷል።

    ፕሮፌሰር አሸናፊ ከመጀመሪያ ኢትዮጵያዊ ባለቤታቸው (ወ/ሮ እሌኒ ገብረመስቀል) እና ሁለተኛ ባለቤታቸው (አሜሪካዊ) አራት ልጆችን (ሦስት ሴቶችና አንድ ወንድ) ልጆችን አፍርተዋል። ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ የ60ኛ የልደት በዓላቸው ዕለት በመኖሪያ ቤታቸው ግልጽ ባልሆነ ምክንያት ሞተው የተገኙ ሲሆን፤ ምናልባትም የራሳቸውን ሕይወት ሳያጠፉ እንዳልቀሩ ብዙዎች ይገምታሉ።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ
    PHOTO: Ethiopian Academy of Sciences

    Semonegna
    Keymaster

    ደብረ ብርሃን (ኢዜአ)–በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በአንጎለላና ጠራ ወረዳ ሀሰተኛ ሰነድ በመጠቀም ከመንግሥት ካዝና ከ466 ሺህ ብር በላይ ለግል ጥቅሟ ያዋለችው ግለሰብ በ18 ዓመት ጽኑ እስራትና የገንዘብ ቅጣት ተጣለባት።

    በሰሜን ሸዋ ዞን ፍርድ ቤት የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ወ/ሪት ዘርትሁን ያዘው ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንደገለጹት ፍርድ ቤቱ በግለሰቧ ላይ ቅጣቱን የወሰነው በወረዳው ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ጽህፈት ቤት ገንዘብ ያዥ ሆና ስትሠራ የመንግሥትን ገንዘብ ለግል ጥቅሟ ማዋሏ በመረጋገጡ ነው።

    ተከሳሿ ወ/ሮ አበበች ጽጌ ከ2007 እስከ 2009 ዓ.ም ድረስ በጽህፈት ቤቱ ስትሠራ ሀሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀትና መንግሥታዊ ሰነድ በመደበቅ የሙስና ወንጀል መፈፀሟ በሰውና በሰነድ ማስረጃ እንደተረጋገጠባትም አስረድተዋል።

    ግለሰቧ በአገር አቀፍ ደረጃ በውሃና በአካባቢ ንጽህና ፕሮጀክት (WASH) ግዢ ከአቅራቢዎች ላይ የተሰበሰበ ሁለት በመቶ ገንዘብ 171 ሺህ 417ብር ለግል ጥቅም ማዋሏ ተረጋግጦባታል ነው የተባለው።

    እንዲሁም በ56 ደረሰኞች ላይ በበራሪው ትክክለኛዉን የገንዘብ መጠን በመመዝገብና የከፋዮችን ስም በመቀያየር የገቢ መጠኑን በመቀነስ ለመንግሥት መግባት የነበረበት 94 ሺህ 90 ብር ሰነድ በማበላለጥ መጠቀሟም ነው የተገለፀው። በተጨማሪም በራሪ ደረሰኞችን ለከፋይ በትክክል ቆርጣ ከሰጠች በኋላ በሁለተኛና ሦስተኛ ካርኒዎች ላይ አቀናንሳ 181ሺህ 16 ብር ለግል ጥቅሟ ማዋሏን መረጋገጡን ባለሙያዋ ገልጸዋል።

    ግለሰቧ ወንጀሉን ከፈጸሟ በኋላ ከአካባቢው በመሰወሯ ፖሊስ ወንጀለኛዋን አድኖ በመያዝ ለማረሚያ ቤት እንዲያስረክብም ትዕዛዝ ተሰጥቷል። ከዚህ በተጨማሪ ለአምስት ዓመታት ከማንኛውም የእንቅስቃሴ መብቷ እንደታገደችም ተወስኖባታል።

    በሌላ ዜና፥ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለረጅም ጊዜ ታጥረው በቆዩ ቦታዎች ንብረታቸውን በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ባላነሱት ላይ እርምጃ መውሰድ ተጀመረ።

    የከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማት ማኔጅመንት ፅህፈት ቤት የደንብ ማስከበር ፅህፈት ቤት ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በጋራ በመሆን እርምጃ መውሰድ መጀመሩን አስታውቋል።

    በዚህም ያለ ልማት ለረጅም ጊዜ ታጥረው የቆዩ ቦታዎች ላይ የሚገኙ የአጥር ቆርቆሮዎችን ማንሳት መጀመሩን ገልጿል።

    አስተዳደሩ ባልለሙ ቦታዎች ላይ ንብረቶቻቸውን ያስቀመጡ አካላት ንብረታቸውን እንዲያነሱ ከሳምንት በፊት መግለጫ መስጠቱ የሚታወስ ነው። ይሁን እንጅ እነዚህ አካላት ንብረቶቻቸውን ማንሳት ባለመጀመራቸው ምክንያት አስተዳደሩ በዛሬው ዕለት ወደ እርምጃ መግባቱን ነው የገለጸው።

    አስተዳደሩ የሕዝብን ሃብት ለተገቢው ልማትና ለነዋሪዎች ተጠቃሚነት እንዲውል በጀመረው ተግባር ህገ ወጥነትን እንደማይታገስና፥ ህግ የማስከበር ሃላፊነቱን እንደሚወጣ መግለጹን ከከተማዋ ከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

    ምንጮች፦ ኢዜአ እና ኤፍቢሲ

    ለግል ጥቅሟ

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ኢ.ፕ.ድ) በአዲስ አበባ በ2010 ዓ.ም የትምህርት ጥራት ደረጃን ያላሟሉ 52 የቅድመ መደበኛ፣ የአንደኛ ደረጃና የሁለተኛ ደረጃ መሰናዶ ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን የአዲስ አበባ አጠቃላይ ትምህርት ጥራትና አግባብነት ተቆጣጣሪ ባለስልጣን አስታወቀ።

    የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ብሩክነሽ አርጋው ኅዳር 7 ቀን 2011 ዓ.ም ለብዙኃን መገናኛ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ በ2010 ዓ.ም በአጠቃላይ ትምህርት ጥራትና አግባብነት ተቆጣጣሪ ባለስልጣን አማካኝነት ቁጥጥር ከተደረገባቸው 1 ሺህ 407 ትምህርት ቤቶች ውስጥ በቅድመ መደበኛ 26፣ በመጀመሪያ ደረጃ 22፣ በሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ አራት ትምህርት ቤቶች ከደረጃ በታች በመሆናቸው ተዘግተዋል።

    እንደ ወ/ሮ ብሩክነሽ ገለጻ፥ በቅድመ መደበኛ ትምህርት ከደረጃ በታች ሆነው የተዘጉ ትምህርት ቤቶች የቅድመ መደበኛ ትምህርት ተቋም ሊኖሩት የሚገባ የአገልግሎት መስጫ ክፍሎች ማሟላት አልቻሉም፤ ተመጣጣኝ የሆነ የመምህራንና የሠራተኞች የትምህርት ደረጃም የላቸውም፤ የመምህራንና ሠራተኞች ብዛት አነስተኛ ነው፤ የሕፃናት ማሸለቢያ ክፍልና የመምህራን ማረፊያ ክፍል ውስጥ ሊኖሩ የሚገባቸው ቁሳቁሶች አልተሟሉም፤ ቋሚ የውጭ መጫወቻ መሳሪያዎች የሏቸውም። የትምህርት ማበልፀጊያ ማዕከል እጥረት፣ በቂ የሰው ኃይልና ለሰውነት ማጎልመሻ ትምህርት የሚያስፈልጉ የትምህርት መሳሪያዎችና የአገልግሎት መስጫ ክፍሎች አለመኖርም ለትምህር ቤቶቹ መዘጋት ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው።

    ወ/ሮ ብሩክነሽ፥ የተዘጉ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 3በ1 የሆነ ቤተ ሙከራና የማዕከል ቁሳቁስ ግብአት በተገቢው ያልተሟላላቸው፣ 3በ1 የሆነ የስፖርት ሜዳ ያላሟሉና የሰለጠነ መምህር የሌላቸው እንዲሁም የመምህራን ማረፊያ ክፍል ውስጥ ሊኖሩ የሚገባቸው ቁሳቁሶችን እንዳላሟሉ ገልጸዋል። የሁለተኛና መሰናዶ ትምህርት ቤቶችም በተመሳሳይ ለትምህርት ጥራት የተሰጠውን የመመዘኛ መስፈርት ባለማሟላታቸው እንደተዘጉ ተናግረዋል።

    These two Ethiopian students are working to launch their own rocket – the future Eng. Kitaw Ejigu

    በቅድመ መደበኛ ከተዘጉ ትምህርት ቤቶች መካከል ቦሌ ቡልቡላ፣ ሳሊተ ምህረት፣ ቶምናጄሪ፣ ገነተ ኢየሱስ፣ አዲስ ሰው፣ ኤሎን፣ ሀመር፣ ሙሴ፣ ሜሲ ሚዶ፣ ብራስ ዩዝ፣ ንጋት፣ አሀዱ ቤተሰብ፣ ደብል፣ አፍሪካስ ድሪም፣ ባቤጅ፣ ብሪሊያንት፣ አልአፊያ ቁጥር 1፣ ጂ. ኤች፣ ኢስት አፍሪካ፣ ቅዱስ ዮሃንስ፣ አጼ ተክለጊዮርጊስ፣ ሳም ፋሚሊ፣ ኒው ዩኒክ፣ ብራይት የሚጠቀሱ ሲሆን፥ ማራናታ፣ ቦሌ ካውንት፣ ማይ ፊውቸር፣ ሰብለ መታሰቢያ፣ ጎል፣ አካዳሚ ፎር ኤክሰለንስ፣ ፎንት፣ ሰለሞን፣ አፍሪካስ ድሪም፣ ቤተሰብ፣ ቅዱስ ገብርኤል፣ ብሪሊያንት፣ እየሩሳሌም፣ ስሪ ኤስ ሜርሲ ከተዘጉ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ናቸው።

    ከዚህ በተጨማሪ እንጦጦ ወንጌላዊት፣ ማርክ፣ አዲስ አበባ ሉተራንና መካነ ኢየሱስ የሁለተኛ ደረጃ መሰናዶ ትምህርት ቤቶች የተዘጉ መሆናቸውንም ዳይሬክተሯ አስታውቀዋል። ከኤጀንሲው የተገኘ መረጃ እንደሚያመለክተው፤ በከተማዋ በ2011 ዓ.ም ፈቃድ ያገኙ 101 አዲስ ት/ቤቶች የመማር ማስተማር ሥራቸውን ጀምረዋል።

    የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአጠቃላይ ጥራትና አግባብነት ተቆጣጣሪ ባለስልጣን (ሬጉላቶሪ ኤጀንሲ) የሰጠው መግለጫ

    የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአጠቃላይ ጥራትና አግባብነት ሬጉላቶሪ ኤጀንሲ የ2010 ዓ.ም የትምህርት ተቋማት የኢንስፔክሽን እና የእውቅና ፍቃድ እድሳት ሪፖርትን በተመለከተ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ

    • የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአጠቃላይ ትምህርት ጥራትና አግባብነት ሬጉላቶሪ ኤጀንሲ ዳይሬክተር ወ/ሪት ብሩክነሽ አረጋው በ2010 ዓ.ም ከቅድመ መደበኛ እስከ መሰናዶ ድረስ ባሉ የመንግስትና የግል ትምህርት ተቋማት በተካሄደ የኢንስፔክሽን መረጃ መሠረት ተቋማቱ ያሉበትን ደረጃ በዝርዝር አቅርበዋል። በዚሁ መሠረት በቅድመ መደበኛ ትምህርት አገልግሎት ከሚሰጡ ተቋማት መካከል 41 ተቋማቱ ደረጃ 1፣ 560 ደረጃ 2 እንዲሁም 108 ተቋማት ደረጃ 3 እና 1 ተቋም ደረጃ 4 ላይ መሆናቸው ገልፀዋል።
    • በመጀመሪያ ደረጃ በሚገኙ የትምህርት ተቋማት በተደረገ ኢንስፔክሽን 10 ተቋማት በደረጃ 1፣ 409 ተቋማት ደረጃ 2፣ 125 ደረጃ 3፣ እና 1 ተቋም ብቻ ደረጃ 4 ላይ እንደሚገኝ የተጠቆመ ሲሆን በሁለተኛና መሰናዶ ተቋማት ላይ በተካሄደ ኢንስፔክሽን ደግሞ 6 ተቋማት ደረጃ 1፣ 80 ተቋማት ደረጃ 2፣ 66 ተቋማት ደረጃ 3 ላይ ሲገኙ አንድም ተቋም ደረጃ 4 ላይ አለመገኘቱን ነው ዳይሬክተሯ ገልፀዋል።
    • በሌላ በኩል ባለስልጣኑ ከኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ በመሆን በአዲስ አበባ ደረጃ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና የተማሪዎች ውጤት ዝቅተኛ የሚሆንበትን ምክንያት በተለመከተ ጥናት ማድረጉ በመግለጫው ከመገለፁ ባሻገር የጥናቱን ውጤትም የኮተቤ ሜትፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዘዳንት ዶ/ር ኤላዛር ታደሰ ያቀረቡ ሲሆን ለ8ኛ ክፍል ውጤት ማሽቆልቆል በዋናነት ከተለዩ ምክንያቶች መካከል ተማሪዎች ለትምህርት ያላቸው አሉታዊ አመለካከት፣ የመምህራን ለደረጃው ብቁ አለመሆን እንዲሁም በየትምህርት ተቋማቱ የሚደረገው (የማስተባበርና መቆጣጠር (የሱፐርቪዥንና ኢንስፔክሽን) አሠራር በቂ አለመሆን እንደምክንያት ተጠቁሟል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ
    ትምህርት ቤቶች

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አባባ (ብርሃን ባንክ)–የብርሃን ባንክ ባለአክስዮኖች ዘጠነኛ መደበኛ ጉባኤ ቅዳሜ ኅዳር 1 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ ተካሂዷል። የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ጉማቸው ኩሴ ይፋ ባደረጉት ሪፖርት እ.ኤ.አ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ባንኩ በዋና ዋና የአፈፃፀም መለኪያዎች የላቀ የሥራ አፈጻጸም በማስመዝገብ እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ ጠንካራ እና ተፎካካሪ ባንክ መሆኑን በድጋሚ አስመስክሯል ሲሉ ገልፀዋል።

    በተገባደደው የበጀት ዓመት ብርሃን ባንክ ከግብር በፊት ብር 410.9 ሚሊዮን ትርፍ ማስመዘገብ መቻሉን ገልፀዋል። በዚሁ በጀት ዓመት ባንኩ ተጨማሪ አክስዮኖችን በመሸጥ የተከፈለ ካፒታሉን ወደ ብር 1.7 ቢሊዮን ያሳደገ ሲሆን ከአለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ20 በመቶ የሆነ ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን ገልፀዋል። በተመሳሳይ መልኩም ባንኩ በበጀት ዓመቱ የባለአሲዮኖቹን ቁጥር ወደ 14,879 አድርሷል። ይህም ባንኩን በኢትዮጵያ ባንክ ኢዱስትሪ ውስጥ ከግል ባኮች በባለአክስዮኞ ቁጥር ቀዳሚ ባንክ አድርጎታል። በመሆኑም ባንኩ ሠፊ የሕዝብ መሠረት /Public Base/ ያለው የሕዝብ ባንክ መሆኑን ያረጋግጣል ብለዋል። በሌላ በኩል ሊቀመንበሩ በበጀት ዓመቱ ባንኩ አጠቃላይ ሀብቱ አምና ከነበረው 10 ቢሊዮን ወደ ብር 14 ቢሊዮን ብር በማድረስ የሀብት መሠረቱን እያሰፋ እና ራሱን ለቀጣይ እድገት ይልጥ በተሻለ ሁኔታ እያደራጀ መሆኑን ገልፀዋል። ከዚህም በተጨማሪ ባንኩ የነበረውን የደንበኞች አገልግሎት በላቀ መልኩ የተቀላጠፈ ለማድረግ እንዲሁም አዳዲስ የባንክ አገልግሎት አማራጮችን በመቅረፅ ደንበኞችን ይበልጥ ለማገልገል የሚረዳ ደረጃውን የጠበቀ የመረጃ ማዕከል ገንብቶ እ.ኤ.አ 2018/19 የበጀት ዓመት ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል።

    ብርሃን ባንክ በበጀት ዓመቱ ካስመዘገበው የላቀ የሥራ አፈፃፀም ውጤት ባሻገር ከእሴቶቹ መካከል አንዱ የሆነውን ማኅበራዊ ኃላፊነትን ከመወጣት አንፃር በተለያዩ ምክንያቶች ከመኖሪያ ቀዬዎቻቸው ለተፈናቀሉ የህብተሰብ አካላት ድጋፍ እንዲደረግ ከሚመለከታቸው የክልል መንግስታት በቀረበለት ጥያቄ መሠረት የብር ሁለት ሚሊዮን ድጋፍ አድርጓል።

    Berhan Bank, one of the private banks in Ethiopia, registers more than 410 million birr before tax

    የብርሃን ባንክ ፕሬዘዳንት የሆኑት አቶ አብርሃም አላሮ በበኩላቸው የተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከፍተኛ የገበያ ውድድር እና በባንኩ ክፍለ ኢኮኖሚ በርካታ ተግዳሮቶች የነበሩበት ዓመት መሆኑን ጠቅሰው በበጀት ዓመቱ ባንኩ በሁሉም የሥራ ዘርፍ ያስመዘገበው የሥራ አፈጻጸም ውጤት እጅግ አመርቂ መሆኑን ገልጸዋል። ባንኩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ጠቅላላ ተቀማጭ ሂሳቡን ወደ ብር 11 ቢሊዮን ሲያሳድግ ይህም ከአለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር የ42 በመቶ የሆነ ከፍተኛ ዕድገት ማሳየቱን አስታወቀው፥ በተመሳሳይ መልኩም ባንኩ ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሰጠው የብድር ክምችት በበጀት ዓመቱ ከፍተኛ እድገት አስመዝግቦ ብር 7 ቢሊዮን መድረሱን ይህም ከዓምናው ጋር ሲነጻጸር የ33 በመቶ የሆነ ከፍተኛ ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል። ባንኩ በኢኮኖሚው በተለያዩ ዘርፎች እያፈሰሰ ያለው የብድር መጠን በየጊዜው እየጨመረ የመጣ መሆኑን ያስረዱት ፕሬዝዳንቱ ባንኩ በአገር ልማት እና እድገት ላይ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን ተናረግዋል።

    ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ብርሃን ባንክ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 21 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት በመላ አገሪቱ ያሉትን የቅርንጫፎች ቁጥር ወደ 182 የደረሰ ሲሆን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የባንኩ ደንበኞች ቁጥርም ከአለፈው ዓመት ከነበረው የ43 በመቶ የሆነ ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ 523,705 መድረሱን ገልጸዋል።

    ብርሃን ባንክ እያስመዘገበ የመጣውን ከፍተኛ የሆነ ሁለንተናዊ ዕድገት ተከትሎ 372 ተጨማሪ ሠራተኞችን በበጀት ዓመቱ የቀጠረ ሲሆን ይህም ባንኩ ያለውን አጠቃላይ የሰው ሃብት ቁጥር ወደ 3,237 ማሳደጉን ፕሬዘዳንቱ ጠቁመዋል። አያይዘውም ባንኩ ለሰው ሃብት ከሚሰጠው ልዩ ትኩረት የተነሳ በበጀት ዓመቱ የባንኩን የተቀላጠፈ የደንበኞች አገልግሎት የሚያሳልጥ እንዲሁም የባንኩን ግልፅነት እና ተዓማኒነት የተሞላበት እሴቶቹን ሊያስጠብቁ እና ደንበኞችን በልሕቀት ማገልግል ይቻል ዘንድ የተለያዩ ስልጠናዎች እንዲወስዱ ተደርጓል ብለዋል። አቶ አብርሃም በቀጣዩ የበጀት ዓመት ባንኩ እሰካሁን የመጣበትን የስኬት ጉዞ ሊያስቀጠል የሚችል ስትራቴጂ ነድፎ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ባንኩ የበለጠ ውጤት እንደሚያመጣ ጽኑ እምነት እንዳላቸው ገልጸው፥ የባንኩ ዳይሬክተሮች ቦርድ፣ የበላይ አመራሩ እና መላው ሠራተኛ እንዲሁም በዋናነት ደግሞ የባንኩ ደንበኞች እና ባለድርሻ አካላት እስካሁን ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅዖ ምስጋናቸውን አቅርበው ባንኩ ከዚህም በኋላ በላቀ እና በተቀላጠፈ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱ ደንበኞቹን በትጋት እና በታማኝነት እንደሚያገለግል ያላቸውን ፅኑ እምነት ገልፀዋል።

    ምንጭ፦ ብርሃን ባንክ (berhanbanksc.com)

    ብርሃን ባንክ

    Semonegna
    Keymaster

    የትግራይ ሕዝብ ለዓመታት የከፈለው መስዋዕትነት የህግ የበላይነት እንዲከበርና በማንኛውም ወቅት ተጠያቂነት እንዲኖር ለማድረግ መሆኑን የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሰጠው መግለጫ፥ መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ በሁሉም ተጠርጣሪዎች ላይ እንዲያተኩር ጠቁሟል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – የትግራይ ሕዝብ ለዓመታት የከፈለው መስዋዕትነት በሃገሪቱ የህግ የበላይነት እንዲከበርና በማንኛውም ወቅት ተጠያቂነት እንዲኖር መሆኑን የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስታወቀ።

    የክልሉ መንግስት ኅዳር 5 ቀን 2011 ዓ.ም በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው መንግስት አሁን የጀመረው የህግ የበላይነትን የማስከበር ሂደት በተገቢው ጥንቃቄ ሊከናወን የሚገባው ነው በማለት አስታውቋል።

    ሰብዓዊ ጥሰትና ሙስና በፈጸሙ ሰዎች ላይ በመንግስት ሰሞኑን እየተወሰደ ያለው እርምጃ የህግ ልዕልና ሳይሸራረፍ ከተጽዕኖ በጸዳ መልኩ ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት መግለጫው አመልክቷል።

    የትግራይ ሕዝብ ለዓመታት የከፈለው መስዋዕትነት የህግ የበላይነት እንዲከበርና በማንኛውም ወቅት ተጠያቂነት እንዲኖር ለማድረግ መሆኑን ያመለከተው መግለጫው መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ በሁሉም ተጠርጣሪዎች ላይ እንዲያተኩር ጠቁሟል።

    በሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ የሙስና ችግርና ህገ-መንግስታዊ ጥሰት ውስጥ እጃቸው ያለ አመራሮችና ተቋማት ስለመኖራቸው ቀደም ሲል በተካሔዱ የኢህአዴግ መድረኮች ውይይት መደረጉንም አመልክቷል።

    ችግሩ በእኩል እንዲስተናገድ ከማድረግ ባለፈ እርቅና ይቅር ባይነትን መሠረት አድርጎ የተጀመረው ሂደት ወደ ኋላ እንዳይመለስ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ጠቅሷል።

    “የህግ የበላይነትም ሳይሸራረፍ እንዲተገበር ከፍተኛ ጥንቃቄና ጥናት የሚጠይቅ መሆኑንም የክልሉ መንግስት ያምናል” ብሏል መግለጫው።

    የትግራይ ክልል ሕዝብ ከሌሎች ብሔሮችና ብሔረሰቦች ጋር በመሆን የከፈለው መስዋዕትነት የዜጎች እኩልነትና ሰብዓዊ መብት እንዲከበር እንጂ በማንም አካል እንዲጣስ እንዳልሆነ መግለጫው አመልክቷል።

    ባለፉት ዓመታት ይታዩ የነበሩት የፍትህና የዲሞክራሲ መጓደሎች እንዲስተካከሉ ሕዝቡ በጽናት እየታገለ መምጣቱንም መግለጫው አስታውሶ በጥልቅ ተሀድሶ ወቅት ህዝቡ ያሳየው ተሳትፎ አንዱ ማሳያ መሆኑን አስረድቷል።

    ከሰብአዊ መብት አያያዝና ከሙስና ጉዳዮች ጋር በተያያዘ እየታየ ላለው ሁኔታ ተጠያቂዎቹ እጃቸው ያለበት አመራሮችና ተቋማት መሆናቸውንም መግለጫው አመልክቷል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)ሰሞነኛ ኢትዮጵያ |
    የትግራይ ሕዝብ

    Semonegna
    Keymaster

    ምክትል ከንቲባው የራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲቀጥል የመፍትሔ አማራጭ አስቀመጡ
    —–
    የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) ከራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ከወ/ሪት ሳምራዊት ፍቅሩ ጋር በመወያየት፣ ራይድ የጀመረው ዘመናዊ የትራንስፖርት አገልግሎት ተጠናክሮ መቀጠል በሚችልበት አማራጭ መፍትሔ ዙሪያ መከሩ።
    ሪፖርተር: https://www.ethiopianreporter.com/article/13863

    Semonegna
    Keymaster

    (የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ጋዜጣዊ መግለጫ) – የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ሰኞ ኅዳር 03 ቀን 2011 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በአዲስ አበባ ውስጥ ብቻ አሰቃቂ ድርጊት የሚፈጸምባቸው 7 ድብቅ እስር ቤቶች መገኘታቸውን፤ ከእነዚህም በተጨማሪ በማረሚያ ቤቶችና በፖሊስ ጣቢያዎችም ጭምር በተጠረጣሪዎች ላይ ከሰብዓዊነት ያፈነገጠ እጅግ አሰቃቂ ድርጊቶች ሲፈፀሙ መቆየታቸውን ገልፀዋል። ከእነዚህ በሕግ ጥላ ስር በሚገኙ ዜጐች ላይ ከሚፈፀሙት የማሰቃየት ድርጊቶች መካከልም የታሳሪዎችን ሰውነት በኤሌክትሪክ ሾክ ከማድረግ ጀምሮ ብልት ላይ ውሃ የያዘ የፕላስቲክ ኮዳ ማንጠልጠል፣ብልትን በፒንሳ መሳብ፣ ጥፍር መንቀል፣ ከአውሬ ጋር ማሳደር፣ ሴቶች ታሳሪዎችን መድፈር፣ በወንዶች ላይ ግብረሰዶም መፈፀም፣ እንዲሁም ደብዛን ማጥፋት በጉልህ የሚጠቀሱ በሕግ ጥላ ስር በተገኙ ዜጐች ላይ የተፈፀሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መሆናቸውን ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ አረጋግጠዋል።

    የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ/ ሰመጉ) ባለፉት 27 ዓመታት ይህ ድርጊት በተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላት፤ ሃሳብን የመግለፅ ሕገ-መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው ሃሳባቸውን በነፃነት ሲያንሸራሽሩ በነበሩ ጋዜጠኞች እና አክቲቪስቶች፣ እንዲሁም የሲቪል ማህበረሰቡ አባላት ላይ እየተፈፀመ መሆኑን በማጋለጥ መንግስት የእርምት እርምጃ እንዲወስድ ሲወተውት መቆየቱ ይታወሳል። መንግስት ለአመታት ለችግሩ ምላሽ መንፈግ ብቻ ሳይሆን የማሰቃየት ድርጊቶቹን ውጤት በመጠቀም የዜጐችን ሕገ-መንግስታዊ እና ሰላማዊ ጥያቄዎች በኃይል ሲያዳፍን ብሎም ንጹሃንን ሲያሸብር ቆይቷል። ይህንንም የማሸበር ድርጊት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ፊት በመቅረብ በግልፅ መናገራቸው እና ይቅርታ መጠየቃቸው የሚታወስ ነው። እነዚህ የማሰቃየት ድርጊቶች ለዜጐች ከለላ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቅ ከነበረው ፍርድ ቤት የተደበቀ እንዳልሆነ በፍርድ ቤቶች ውስጥ የማሰቃየት ድርጊት ሰለባዎች ለችሎት ከሚያቀርቡት የቃል እና የፅሁፍ አቤቱታዎች በተጨማሪ፤ ልብሶቻቸውን በድፍረት በማውለቅ አካላዊ ጉዳታቸውን ቢያሳዩም በፍርድ ቤቶች በኩል የተወሰዱ እርምጃዎች አለመኖራቸው ታይቷል። በዚህም ፍርድ ቤቶች የዜጐችን ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች የማስከበር ግዴታቸውን በአግባቡ ባለመወጣታቸው ዜጐች እምነት አጥተውበት ቆይተዋል።

    ባለፉት 7 ወራት የመጣውን የመንግስት አስተዳደር ለውጥ ተከትሎ በመንግስት በኩል ሲወሰዱ የነበሩት እርምጃዎች በመልካምነታቸው የሚጠቀሱ ናቸው። በተለይም ላለፉት 27 ዓመታት መንግስታዊ ኃላፊነትን ተገን በማድርግ በንፁሃን ላይ ኢሰብዓዊ ድርጊቶችን ሲፈፅሙ በቆዩ የብሔራዊ ደኅንነት የሥራ ኃላፊዎች እና ድርጊቱን በቀጥታ ሲፈፅሙ በነበሩ ግለሰቦች ላይ እየተወሰደ ያለው ሕጋዊ እርምጃ የሚደገፍ ነው። እስካሁን ከተወሰደው የማጣራት ሥራ በተጨማሪም ተመሳሳይ ድርጊቶችን ሲፈፅሙ እና ሲያስፈፅሙ የነበሩ ሌሎች የመንግስት ኃላፊዎችም ላይ እርምጃው እንዲቀጥል ሰመጉ ይጠይቃል።

    የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ መንግስት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈፃሚዎች ላይ መውሰድ የጀመረውን ሕጋዊ እርምጃ በመደገፍ ረገድ፤ ከሰብዓዊ መብት ጥሰቱ ሰለባዎች ያሰባሰባቸውን መረጃዎች ለሚመለከተው የሕግ አስከባሪ አካል መስጠትን ጨምሮ በማናቸውም መንገድ የሚጠበቅበትን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ያረጋግጣል። በተጨማሪም የማሰቃየት ድርጊቶቹ ሰለባ የሆኑ ዜጐች የደረሰባቸው አካላዊ ብቻ ሳይሆን ስነ-ልቦናዊ እና ማኅበራዊ ጉዳት በቀላሉ የሚሽር እንዳልሆነ እሙን ነው። በመሆኑም ለተጐጂዎችና ለቤተሰቦቻቸው ነፃ የህክምና፣ የስነ-ልቦና ምክር አግልግሎት እና ኢኮኖሚያዊ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ሰመጉ ይጠይቃል።

    በአጠቃላይ መንግስት በከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በፍጥነት ለፍትህ ማቅረቡ ሊመሰገን የሚገባው ተግባር ነው። ይህ የፍርድ ሒደት መንግስት ከበቀል በፀዳ መልኩ ሕግን ብቻ መሠረት ያደረገ እንቅስቃሴ በማድርግ ላይ መሆኑን የሚያሳይበት፣ ዜጐች በፍርድ ቤቶች ላይ የተሸረሸረ እምነታቸውን የሚያድሱበት እና የሕግ ልዕልና የሚከበርበት የፍርድ ሒደት እንዲሆን ሰመጉ ይጠይቃል።

    ምንጭ፦ የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ሰመጉ) | ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የሰብዓዊ መብቶች

    Semonegna
    Keymaster

    ራይድ የተባለዉ የታክሲ አገልግሎት ድርጅት የስም ማጥፋት ዘመቻ እና ጥቃት ደርሶብኛል በማለት ወቀሰ። የመለያ ቁጥር 3 ባለንብረቶች ሕጋዊ ባልሆነ ደረሰኝ በትራፊክ ፖሊሶች እየተቀጣን ነው ሲሉም ተናገሩ።

    “ዛይቴክ አይቲ ሶሉዊሽን” በተባለ የግል ኩባንያ ለአገልግሎት የበቃው የራይድ የሞባይል አፕልኬሽን፤ ዓላማዉ ተሳፋሪን እና አሽከርካሪን ማገናኘት እንደሆነ አስታዉቋል። ሥራውን የጀመረዉ ከሁለት ዓመት ከስድስት ወር በፊት ነው። ኩባንያው እንደሚለዉ ግቡ በሚንቀሳቀስ የጥሪ ማዕከል አማካኝነት የታክሲ አገልግሎት በተመጣጣኝ ክፍያ መስጠት ነበር። ኩባንያው በስሩ በርካታ አሽከርካሪዎችን አቅፎ እየሠራ ቢቆይም በቅርብ ጊዜ ግን እንቅፋት ገጥሞኛል ባይ ነዉ።

    የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ታደሰ እንደሚሉት በድርጅታቸዉ ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ፤ በሚያስማራቸዉ አሽከርካሪዎች ላይ ደግሞ ቅጣት ደርሶባቸዋል። አቶ ሐብታሙ ለዘመቻዉ እና ለጥቃቱ የአዲስ አበባን ትራንስፖርት ባለስልጣንን ይወቅሳሉ።

    አቶ ሐብታሙ አክለዉ እንዳሉት ድርጅታቸዉ ከንግድ ሚንስቴር ሕጋዊ ፈቃድ አዉጥቷል። “የስምሪት ሥራ እየሠራችሁ ነው” የሚባለው የአሠራራችን ሁኔታ አለማወቅ ነው ይላሉ። የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ባለስልጣን በዘርፉ የተሰማሩ ድርጅቶችን ጠቅሶ ሕጋዊ እንዳልሆኑ በመገናኛ ብዙሃን ሁሉንም በጥቅል መናገሩ ስም ማጥፋት እንደሆነ ይናገራሉ።

    RIDE, Ethiopia’s version of Uber, is opening up for women in male-dominated taxi business

    ራይድ የጥሪና የአፕልኬሽን የትራንስፖርት አገልግሎት ኮድ 1 የታክሲ ባለንብረቶች ጋር በጋራ ይሠራል። 540 ኮድ 1 መኪኖችን ለአገልግሎት ያሰማራል። ሆኖም የራይድ አገልግሎትን የሚያመለክቱ ስቲከሮችን የለጠፉ ተሽከርካሪዎች ለቅጣት እየተዳረጉና እንግልት እየደረሰባቸው እንደሆነ አቶ ሐብታሙ አስታዉቀዋል። ሕጋዊ ባልሆነ ደረሰኝ እየተቀጣን ነው ይላሉም።

    በሌላ በኩል ኮድ 1 ታክሲ ባለንብረቶች በብድር የገዛነውን መኪና ዕዳ መክፈል አልቻልንም ሲሉ አንድ ያነጋገርኳቸው የታክሲ ባለንብረት ዶይቸ ቬለ ራድዮ የአማርኛ ዝግጅት ክፍል ገልጸዋል። ስምሪቱ በቶሎ አይደርሰንም ሲሉ ያማርራሉ። በዚህ አገልግሎት መስጠት ያለባቸው ኮድ አንድ ብቻ መሆን እንዳለባቸውም ይገልጻሉ።

    በሌላ በኩል ኮድ 3 የኪራይ መኪናዎች ሕግን ተከትለው በዚሁ ዘርፍ እየሠሩ ቢሆንም እንዳይሠሩ ተጽዕኖ እየተፈጠረብን ነው ይላሉ።

    በትራንስፖርቱ ዘርፍ ፍቃድ የሌላቸው ተቋማት አገልግሎት መስጠት እንደሌለባቸው የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ባለስልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ዳዊት ዘለቀ ባለፈዉ ሳምንት ለሀገር ዉስጥ መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል። እውቅና ሳይኖራቸው አገልግሎት ሲሰጡ የተገኙ ተቋማት መኖራቸውንም ዋና ሥራ አስኪያጁ ቢናገሩም የተቋማቱን ስም ግን አልጠቀሱም። በስልክ ያነጋገርናቸዉ የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ባለሥልጣናት ኃላፊዎች ለጥያቄያችን መልስ ለመስጠት ፈቃደኞች አይደሉም። የዶይቸ ቬለ ራድዮ የአማርኛ ዝግጅት ክፍል ጋዜጠኞች የአዲስ ትራፊክ ፖሊስ ጽህፈት ቤትን ኃላፊዎችን ለማነጋገር በተደጋጋሚ ስልክ ቢደውሉም መልስ የሚሰጣቸው አላገኙም።

    የ“ዛይቴክ አይቲ ሶሉዊሽን” ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ታደሰ ከዶይቸ ቬለ ራድዮ ጋር ያደረገውን አጭር ቃለ ምልልስ እዚህ ጋር ያዳምጡ

    ምንጭ፦ ዶይቸ ቬለ ራድዮ | Semonegna Business

    ራይድ

    Semonegna
    Keymaster

    የዘንድሮው የዓለም የስኳር ህመም ቀን  ቤተሰብ የስኳር ህመምን ለመከላከል ባለው ሚና ላይ ተመሥርቶና “የስኳር ህመም ይመለከተኛል” በሚል መሪ ሀሳብ ኅዳር 5 ቀን 2011 ዓ.ም. በብሔራዊ ትያትር ይከበራል።

    አዲስ አበባ (ኢ.ዜ.አ) – የጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ስኳር ህመም ማህበር ኅዳር 5 ቀን 2011 ዓ.ም. በዓለም አቀፍና በኢትዮጵያ ለ28ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም የስኳር ህመም ቀን አስመልክቶ በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።

    የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ ከዓለም አቀፉ ስኳር ህመም ፋውንዴሽን እና “Doctors with Africa CUAMM” ከተባለ ድርጅት ጋር በመተባበር ቀኑ ቤተሰብ የስኳር ህመምን ለመከላከል ባለው ሚና ላይ ተመሥርቶና “የስኳር ህመም ይመለከተኛል” በሚል መሪ ሀሳብ በብሔራዊ ትያትር ይከበራል።

    የኢትዮጵያ ስኳር ህመም ማህበር (EDA) ፕሬዚዳንት ዶ/ር አብዱራዛቅ አህመድ በኢትዮጵያ 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዜጎች ከስኳር ህመም ጋር እንደሚኖሩ ገልጸዋል።

    በኢትዮጵያ የስኳር ህመም ስሜትና ምልክት ሳይታይ የጤና ምርመራ የማድረግ ባህል አነስተኛ በመሆኑ ከስኳር ህመም ጋር እየተኖረ እንኳን ማወቅ ባለመቻሉ የችግሩን አሳሳቢነት እንደሚያጎላው ዶ/ር አብዱራዛቅ ተናግረዋል።

    በህመሙ ከተያዙት 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዜጎች በተጨማሪ ሌሎች 9 ነጥብ 1 ሚሊዮን ዜጎች በተለያየ አጋጣሚ የስኳር መጠን መዛባት እየጋጠማቸው መሆኑንና ይህም ችግር ካልተፈታ የታማሚዎች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ሊጨምር እንደሚችል አመልክተዋል። በአብዛኛው በኢትዮጵያ በስኳር ህመም የሚኖሩ ሰዎች በምርመራ የጤና ሁኔታቸውን ያላወቁ መሆናቸውን ነው ዶ/ር አብዱራዛቅ ያስረዱት።

    አሁን ባለው ሁኔታ የስኳር ህመም ስርጭት በቁጥጥር ስር ካልዋለ ህመሙ ልብን፣ ዓይንን፣ ኩላሊቶችን፣ ነርቮችንና የደም ቱቦዎችን ተግባር በመጉዳትና ተግባራቸውን በማስተጓጎል ከባድ የጤና ቀውስ እንደሚያስከትልም ጠቅሰዋል።

    የኢትዮጵያ ስኳር ህመም ማኅበር የህመም ስርጭቱን አሳሳቢነት በመገንዘብ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመሆን የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ፣ የመድኃኒት አቅርቦትና የህክምና ተደራሽነቱን ለማስፋትና ለጤና ባለሙያዎች ሙያዊ ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

    ጤናማ ያልሆነ የአኗኗርና የአመጋገብ ዘይቤ፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መቀነስ፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረትና የደም ግፊት ለስኳር ህመም አጋላጭ ሁኔታዎች እንደሆኑም ነው ዶ/ር አብዱራዛቅ ያስረዱት። በአጠቃላይ የስኳር ህመምን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ጤናማ የአኗኗር ዘይቤ መከተል በተለይ ሁለተኛውን የስኳር ዓይነት (Type 2 Diabetes) በ80 በመቶ ለመከላከል እንደሚያስችል ጠቅሰዋል።

    ህብረተሰቡ በተቻለው አቅም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማዘውተር እንደሚገባውና አትክልትና ፍራፍሬዎችን መመገብ እንዲሁም ህመም ቢሰማም ባይሰማም በዓመት አንድ ጊዜ የስኳር ህመም ምርመራ ማድረግ እንደሚገባውም ምክራቸውን አቅርበዋል።

    የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ባለሙያ አቶ አፈንዲ ኡስማን በበኩላቸው ሚኒስቴሩ አሁን ያለውን የስኳር ህመም ችግር አሳሳቢነት ለመከላከል የሚያስችሉ ጅምር ሥራዎችን እያከናወነ ነው ብለዋል።

    የስኳር ህመም መርሃ ግብር ከፌደራል እስከ ክልል ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች (non-communicable diseases) ላይ ከሚሰሩ ሥራዎች መካከል እንደ ዋና መርሃ ግብር በማካተት በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

    ሚኒስቴሩ የአምስት ዓመት አገር አቀፍ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ አቅድ የስኳር ህመምን በዋናነት ባከተተ መልኩ አዘጋጅቶ የመተግበር ሥራንም እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

    የጤና ባለሙያዎችን፣ የጤና ማኅበራትንና የባለድርሻ አካላትን ያካተተ ብሔራዊ የስኳር ህመምን መከላከልና መቆጣጠር አማካሪ ግብረ ኃይልም ተቋቁሞ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩንም ነው አቶ አፈንዲ ያስረዱት።

    በተጨማሪም የስኳር ህመምና ተጓዳኝ የጤና ችግሮች መድኃኒቶችን ተመጣጣኝ በሆነ ክፍያ እንዲገኝ ለማድረግም ሁኔታዎችን የማመቻቸት፣ በተቀናጀ መልኩ የስኳር ህመምን ለመከላከል በጤና ጣቢያዎችና ሆስፒታሎች የበሽታውን የመቆጣጠር መርሃ ግብር ሥራዎችና ሌሎችም ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል። የስኳር ህመምን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ሁሉም ባለድርሻ አካል አስፈላጊውን ጥረት እንዲያደርግም ጠይቀዋል።

    ዓለም አቀፉ የስኳር ህሙማን ቀን ኅዳር 5 ቀን 2011 ዓ.ም. በብሔራዊ ትያትር ሲከበር የፓናል ውይይት እንደሚካሄድና የህክምና ባለሙያዎችም ስለ በሽታው ገለጻ እንደሚያደርጉ በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ተጠቅሷል።

    የስኳር ህመም የሚከሰተው ሰውነታችን ለኑሮም ሆነ ለእድገት የሚያስፈልገውን ስኳር በትክክል ለመጠቀም ሳይችል ሲቀር ሲሆን አንድ ሰው የስኳር ህመም አለው የምንለው በደም ውስጥ ያለው የስኳር መጠን ከሚገባው በላይ ከፍ ብሎ ሲገኝ እንደሆነም የህክምና ባለሙያዎች ይገልጻሉ።

    እንደ ዓለም አቀፉ ስኳር ህመም ፌዴሬሽን እ.ኤ.አ በ2017 ባወጣው መረጃ መሠረት በዓለም ደረጃ ከ425 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ከህመሙ ጋር የሚኖሩ ሲሆን አስፈላጊው የበሽታው መከላከልና መቆጣጠር ካልተሰራ እ.አ.አ በ2045 የህሙማኑ ቁጥር 629 ሚሊዮን ሊደርስ እንደሚችል ቅድመ ትንበያውን አስቀምጧል።

    ዓለም አቀፉ የስኳር ህመም ፌዴሬሽን (IDF) እ.ኤ.አ ከ1991 ጀምሮ የያዝነው ኅዳር ወር በዓለም አቀፍ ደረጃ የስኳር ህመምና ተጓዳኝ ችግሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ወር በሚል ተሰይሟል።

    በኢትዮጵያ በበሽታው ከተያዙ 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዜጎች ውስጥ 90 በመቶው በሁለተኛው የስኳር ዓይነት (Type 2 Diabetes) የተያዙ ሲሆን የተቀሩት በአንደኛው የስኳር ዓይነት (Type 2 Diabetes) የተያዙ ናቸው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) | Semonegna Health

    የስኳር ህመም

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በሙስና ወንጀል እና በሰብዓዊ መብት ጥሰት ተጠርጥረው እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦችን ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

    በዚህም መሠረት በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት፦

    1. ብርጋዴር ጄኔራል ጠና ቁርንዴ ኢጄታ – በብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የማርኬቲንግ ኃላፊ
    2. ብርጋዴር ጄኔራል ብርሃ በየነ – የሜቴክ ኦዲትና ኢንስፔክሽን ኃላፊ
    3. ብርጋዴር ጄኔራል ጥጋቡ ፈትላ መረሳ – የሜቴክ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኮርፖሬት ሎጂስቲክስና ሰፕላይ ኃላፊ
    4. ብርጋዴር ጀኔራል ሃድጉ ገብረጊወርጊስ ገብረስላሴ – የሜቴክ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኮርፖሬት ኒው ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ኃላፊ
    5. ኮሎኔል ሸጋው ሙሉጌታ ተስፋሁን – የሜቴክ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የወታደራዊ ምርቶች ኦፕሬሽን ኃላፊ
    6. ኮሎኔል ሙሉ ወልደገብርዔል ገብረእግዛብሄር – የሜቴክ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኒው ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ኃላፊ የነበሩ
    7. ኮሎኔል ዙፋን በርሄ ይህደግላ – የመከላከያ ጤና ኮሌጅ ሠራተኛ
    8. ሌተናል ኮሎኔል አስምረት ኪዳኔ አብርሃ – የጋፋት አርማመንት ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ተወካይ ኃላፊ የነበሩ
    9. ኮሎኔል አለሙ ሽመልስ ብርሃን – የሜቴክ ሎጂስቲክስና ሰፕላይ የትራንስፖርት ኃላፊ
    10. ኮሎኔል ያሬድ ሃይሉ – የሜቴክ በኮርፖሬት ኒው ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት የፕሮጀክት ኃላፊ
    11. ኮሎኔል ተከስተ ሀይለማሪያም አድሃኑ – የሜቴክ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኒው ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ኃላፊ የነበሩ
    12. ኮሎኔል አዜብ ታደሰ – የሜቴክ በኮርፖሬት ማርኬቲንግ የሽያጭ ኃላፊ
    13. ሻለቃ ሰመረ ሀይሌ ሀጎስ – የሜቴክ በደጀን አቪዬሽን የኢንዱስትሪ ኦፕሬሽን ኃላፊ
    14. ሻምበል ይኩኖአምላክ ተስፋዬ – የሜቴክ በኮርፖሬት ማርኬቲንግና ሽያጭ የፕሮሞሽን ኃላፊ
    15. ኮሎኔል ደሴ ዘለቀ ብርሃን – የሜቴክ የአዳማ እርሻ ስራዎች ኢንዱስትሪ ሥራ አስኪያጅ
    16. ሌተናል ኮሎኔል ሰለሞን በርሄ – የሜቴክ በብረታ ብረት ፋብሪኬሽን ኢንዱስትሪ የፋይናንስ ኃላፊ
    17. ሻለቃ ይርጋ አብርሃ – የሜቴክ በህብረት ማሽን ቢዩልዲንግ ኢንዱስትሪ የፋይናንስ ኃላፊ
    18. ኮሎኔል ግርማይ ታረቀኝ – የሜቴክ በኮርፖሬት ሎጂስቲክስና ሰፕላይ የንብረት አስተዳደር ኃላፊ
    19. ሻምበል ገብረስላሴ ገብረጊዮርጊስ – የሜቴክ የኮርፖሬት ትራንስፎርሜሽን የአቅም ግንባታ ማዕከል ኃላፊ
    20. ሻምበል ሰለሞን አብርሃ – የሜቴክ በኮርፖሬት ትራንስፎርሜሽን የስልጠና ኃላፊ
    21. ሻለቃ ጌታቸው ገብረ ስላሴ – የሜቴክ የደን ምንጣሮ ክትትል ኃላፊ
    22. ሌተናል ኮሎኔል ይሰሃቅ ሀይለማሪያም አድሃኖም – የሜቴክ በኮርፖሬት ኮሜርሻልና ሲቪል ምርቶች ኦፕሬሽን የፕላኒንግና ኮንትሮል ኃላፊ
    23. ሻለቃ ክንደያ ግርማይ – የሜቴክ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የፋይናንስ ኃላፊ
    24. ሌተናል ኮሎኔል አዳነ አገርነው – የሜቴክ በኮርፖሬት ሎጂስቲክስና ሰፕላይ የንብረት ክፍል ኃላፊ
    25. ሻለቃ ጌታቸው አጽብሃ – የሜቴክ ኢንፍራስትራክችርና ኮርፖሬሽን ማሽነሪ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኦፕሬሽን ኃላፊ
    26. ቸርነት ዳና – የዋይ ቲ ኦ ኩባንያ ባለቤትና ከብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን አመራሮች ጋር የጥቅም ትስስር የነበራቸው ደላላ
    27. አያልነሽ መኮንን አራጌ – ማስረጃ ልታጠፋ ስትል በቁጥጥር ስር የዋለች

    በሰብዓዊ መብት ጥሰት ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት፦

    1. አቶ ጉሃ አጽበሃ ግደይ – የአዲስ አበባ የደህንነት ኃላፊ
    2. አቶ አማኑኤል ኪሮስ መድህን – የሃገር ውስጥ ደህንነት ጥበቃ ዋና መምሪያ ዳይሬክተር
    3. አቶ ደርበው ደመላሽ – የውስጥ ደህንነት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩና የኢኮኖሚ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ
    4. አቶ ተስፋዬ ገብረጻዲቅ – የውስጥ ደህንነት ጥናትና የወንጀል ምርመራ መምሪያ ኃላፊ
    5. አቶ ቢኒያም ማሙሸት – በውስጥ ደህንነት ጥበቃ ዋና መምሪያ የኦፕሬሽን ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ (በዋናነት የግንቦት 7 ጉዳይ ክትትል)
    6. አቶ ተሾመ ሀይሌ – የአማራ ክልል የደህንነት ኃላፊ የነበሩና የጥበቃ ዋና መምሪያ ዳይሬክተር
    7. አቶ አዲሱ በዳሳ – በሃገር ውስጥ ደህንነት የኦሮሚያ ክልል ደህንነት ኃላፊ 
    8. አቶ ዮሃንስ ወይም ገብረእግዚአብሄር ውበት – የውጭ መረጃ
    9. አቶ ነጋ ካሴ – በጸረ ሽብር መምሪያ የኦነግ ክትትል ኃላፊ
    10. አቶ ተመስገን በርሄ – በጸረ ሽብር መምሪያ የኦነግና ኦብነግ ክፍል ዋና ኃላፊ
    11. አቶ ሸዊት በላይ – በሃገር ውስጥ ደህንነት ኦፕሬሽን መምሪያ የግንቦት 7 ክትትል ምክትል መምሪያ ኃላፊ
    12. አቶ አሸናፊ ተስፋሁን – በሃገር ውስጥ ደህንነት የአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ደህንነት አስተባባሪ
    13. አቶ ደርሶ አያና – በውጭ መረጃ የአማራ ክልል ክትትል
    14. አቶ ሰይፉ በላይ – በውስጥ ደህንነት የደቡብ ክልል ክትትል ኦፊሰር
    15. አቶ ኢዮብ ተወልደ – በውስጥ ደህንነት የደቡብ ክልል ደህንነት ኃላፊ
    16. አቶ አህመድ ገዳ – በውስጥ ደህንነት የኦሮሚያ ክልል ክትትል ምክትል ኃላፊ
    17. ምክትል ኮማንደር አለማየሁ ሀይሉ ባባታ – ቀድሞ የፌደራል ፖሊስ የሽብር ወንጀል ምርመራ ምክትል ዳይሬክተር የነበረና ዋና ዳይሬክተር ሆኖ ያገለገለ
    18. ምክትል ኢንስፔክተር የሱፍ ሀሰን – የሽብር ወንጀል መርማሪ
    19. ዋና ሳጅን እቴነሽ አራፋይኔ – የሽብር ወንጀል መርማሪ
    20. ኢንስፔክተር ፈይሳ ደሜ – የሽብር ወንጀል መርማሪ
    21. ምክትል ኢንስፔክተር ምንላርግልህ ጥላሁን – የሽብር ወንጀል መርማሪ
    22. ዋና ሳጅን ርዕሶም ክህሽን – የሽብር ወንጀል መርማሪ
    23. ኦፊሰር ገብረማሪያም ወልዳይ
    24. ኦፊሰር አስገለ ወልደጊዮርጊስ
    25. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት አሰፋ ኪዳኔ
    26. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት ገብረ እግዚአብሔር ገብረሐዋርያት – የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የጥበቃና ደህንነት ኃላፊ
    27. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት ተክላይ ኃይሉ – የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሠራተኛ
    28. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት አቡ ግርማ – የሸዋ ሮቢት ማረሚያ ቤት ኃላፊ የነበረና በዝዋይ ማረሚያ ቤት ኃላፊ ሆኖ ሲያገለግል የነበረ
    29. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት አዳነ ሐጎስ – የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ሠራተኛ
    30. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት ተስፋሚካኤል አስጋለ – በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከፍተኛ የደህንነት ባለሙያ
    31. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት ገብራት መኮንን – የዝዋይ ማረሚያ ቤት የጥበቃና ደህንነት ኃላፊ የነበረና የሸዋ ሮቢት ማረሚያ ቤት ጥበቃና ደህንነት ኃላፊ ሆኖ ሲያገለግል የነበረ
    32. ረዳት ኢንስፔክተር አለማየሁ ኃይሉ ወልዴ – በአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል መርማሪ
    33. ረዳት ኢንስፔክተር መንግስቱ ታደሰ አየለ – በአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል መርማሪ
    34. አዳነች ወይም ሃዊ ተሰማ ቶላ
    35. ጌታሁን አሰፋ ቶላ
    36. ሙሉ ፍሰሃ

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    በቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦች ዝርዝር

    Semonegna
    Keymaster

    ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው በቁጥጥር ስር ውለው ወደ አዲስ አበባ እየመጡ ነው
    ****************************************************

    የቀድሞ የብረታ ብረት እና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው በቁጥጥር ስር ዋሉ።

    ከኮርፖሬሽኑ አሰራር ጋር በተያያዘ በወንጀል ተጠርጣሪ የሆኑት የሜቴክ ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው በምዕራባዊ ትግራይ በኩል ባታር በተሰኘው አካባቢ ነው በህብረተሰቡ እና በመከላከያ ኃይል ትብብር የተያዙት።

    በአሁኑ ሰዓትም ወደ አዲስ አበባ ተይዘው እየመጡ ነው።

    በትናንትናው እለት የጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ከፍተኛ የገንዘብ ምዝበራ በመፈፀማቸው የተጠረጠሩ 27 ከፍተኛ የሜቴክ አመራሮች እና ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ማስታወቁን ሪፖርተራችን አብዲ ከማል ከስፍራው ዘግቧል።

    Semonegna
    Keymaster

    ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ አቶ ብርሀኑ ጸጋዬ በሰጡት መግለጫ፥ እስካሁን ድረስ በጥቅሉ 63 የሚደርሱ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፥ ከእነዚህም 27 ግለሰቦች በሙስና፣ 36 ደግሞ በሰብዓዊ መብት ጥሰት ምክንያት በቁጥጥር ስር የዋሉ ናቸው።

    አዲስ አበባ – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ህዳር 3 ቀን 2011 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በተለያዩ ቦታዎች የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም በተከሰተው የቦምብ ጥቃት እንዲሁም በሜቴክ አመራሮች በተፈፀመው የሙስና ወንጀል በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ።

    ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ በሰጡት መግለጫ መሰረት እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋሉት በጥቅሉ 63 የሚደርሱ ናቸው። ከእነዚህም 27 በሙስና፣ 36 ደግሞ በሰብዓዊ መብት ጥሰት ናቸው። በሙስና ወንጀል የተጠረተሩትን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ከማዋላችን በፊት ማስረጃዎችን በማሰባሰብ ሂደት ላይ እያለን እንዚህን ማስርጃዎች ማለትም ሊብሬ፣ የአክስዮን ደብተር፣ የቤት ካርታዎች ፣ የባንክ ደብተር የቤት ሽያጭ ውሎች፣ ጦር መሣሪያዎች ማግኘትት ተችሏ በኤግዚብትነትም ተይዘዋል ብለዋል።

    ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ አሁንም የምንጠረጥራቸው ነገር ግን በአገር ውስጥና በውጪ ተሸሽገው ያሉ አሉ። በውጪ ያሉትን መንግስታቶቹ አሳልፈው እንዲሰጡን ተንጋግረር አገራቱ አሳልፈው እንደሚሰጡን ቃል ገብተውልናል ሲሉ ሀገር ውስጥ ያሉት ደግሞ ራሳቸውን ወደ ሕግ እንዲያቀርቡ እንዲሁም ህብረተሰቡ በመተባበር ጥቆማ እንዲሰጥ እና ሰላማዊ በሆነ መልኩ የፍትህ ሂደታቸውን እንዲከታተሉ ጥሪ እናቀርባለን ብለዋል።

    በቁጥጥር ስር ስለ ዋሉ ግለሰቦች አቃቤ ሕጉ በመግለጫው ካነሷቸው አንኳር ነጥቦች መካከል ምርመራው ከ5 ወር በላይ የፈጀ ሲሆን የዚህ ምክንያቱም በቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦችን አስረን ከማጣራት አጣርተን ለማሰር ስለሞከርን ነው። ማንንም ተጠርጣሪ ሳንይዝ ነው ያጣራንው። በቁጥጥር ስር ከዋሉ ግለሰቦች መሀል የተሰጣቸውን ኃላፊነት ወደ ጎን በመተው ያለአግባብ ሀብት ያከማቹ፣ ሀብት ያሸሹ፣ በሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ላይ የተሳተፉ፣ በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች ላይ የተከሰቱ ብጥብጦች ያስተባበሩ ይገኙበታል ተብሏል።

    በሌላ በኩል ደግሞ በብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አባላት መካከል በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በስውር እስር ቤት ግለሰቦችን በማሰር እና በማሰቃየት ተጠርጥረው የተያዙ አሉ። በአዲስ አበባ ብቻ ከሰባት በላይ እስር ቤቶች ተገኝተዋል። እንዲሁም በሰብዓዊ መብት ጥሰት ተጠርጥረው ከተያዙ ግለሰቦች መሀል ግለሰቦችን ከፖለቲካ ፓርቲ አባልነት እራሳቸውን እንዲያገሉ ማድረግ እና ማሰቃየት፣ በአንቡላንስ እያፈኑ ሰዎችን መሰወር፣ ሕገ-ወጥ መሣሪያዎችን የራሴ ነው ብሎ እንዲፈርሙ ማድረግ፣ የብልት ቆዳዎችን በፒንሳ መሳብ፣ ጫካ ማሳደር፣ ከአውሬ ጋር ማሰር፣ አፍንጫ ውስጥ እስክርቢቶ መክተት፣ ግብረሰዶማዊ ጥቃት መፈፀም፣ ሴቶችን መድፈር የመሳሰሉ አረመኔያዊ ድርጊቶችን ፈፅመዋል።

    የሰኔ 16ቱ የቦንብ ጥቃት በተመለከተ በዋናነት የተቀነባበረው የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አባል በሆኑ ግለሰብ ነው። ኬንያ ከምትገኝ ገነት ቶሎሺ ከተባለች ግለሰብ ጋር በመሆን ነበር።

    የብረታብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ድርጅትን በተመለከተ የውጪ ሀገር ግዥዎችን ያለጨረታ መስጠት፣ ግዥ አፈፃፀሙ ከኮርፖሬሽኑ የበላይ አመራሮች ጋር የጥቅም ትስስር እና ዝምድና ያላቸው ሰዎች የድለላ ሥራ ሠርተው የሚከፈላቸውና እነዚህ የውጪ ኩባንያዎችን የሚያመጡት ደላሎች ለአመራሩ ቅርብ የሆኑ ናቸው። እነዚህ በድለላ ያሉ ሰዎች በሀገር ውስጥ ካካበቱት ሃብት በላይ ወደ ዉጪ ሃብት አሽሸዋል። ከመደበኛው ዋጋ እስከ 400% ተጨማሪ ዋጋ እየተጨመሪ ግዢ ይፈፀም ነበር ተብሏል። ከዚህም ጉዳይ የሀገር ውስጥ ግዢም በግልፅ ጨረታ መፈፀም ሲገባው እስካሁን በዚህ መልኩ የተፈፀመ የለም። ከኮርፓሬሽኑ አመራሮች ጋር የዝምድናና የጥቅም ትስስር ካላቸው ሰዎች በብዙ እጥፍ በተጋነነ ዋጋ ይገዛ ነበር። ከአንድ ድርጅት 21 ጊዜ፣ ከሌላው ደግሞ 15 ጊዜ ግዥ ተፈፅሟል። ለአብነት ያህል ከአንድ ድርጅት በአንድ ጊዜ ብቻ የ205 ሚሊዮን ብር ግዢ ያለጨረታ ተፈፅሟል በማለት አቶ ብርሀኑ ጸጋዬ ጠቅሰዋል። ከተቋሙ ተልዕኮ ውጪ የተፈፀሙ ግዥዎችም አሉ። ከዚህም ውስጥ የመርከብ ግዢ ይገኝበታል። በማይመለከተውም ሥራ ገብቶ ወደ ንግድ ሥራ አስገብቷቸዋል ሲሉ ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ አቶ ብርሀኑ ጸጋዬ ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ | ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አቶ ብርሀኑ ጸጋዬ

    Semonegna
    Keymaster

    ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ሜቴክ ከተቋቋመበት ተልዕኮ ውጭ አገልገሎት መስጠት የማይቸሉ ሁለት መርከቦችና አምስት አውሮፕላኖችን ገዝቶ በመንግስት ላይ ከ24 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ደርሷል።

    አዲስ አበባ (የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት)– የብረታብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ከተቋቋመበት ተልዕኮ ውጭ አሮጌ ሁለት መርከቦችና አምስት አውሮፕላኖችን ያለአዋጭነት ጥናት ገዝቶ በመንግስት ላይ ጉዳት ማድረሱን ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቀ።

    ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ አቶ ብርሀኑ ጸጋዬ ህዳር 3 ቀን 2011 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፥ ሜቴክ ከተቋቋመበት ተልዕኮ ውጭ አገልገሎት መስጠት የማይቸሉ ሁለት መርከቦችና አምስት አውሮፕላኖችን ገዝቶ በመንግስት ላይ ጉዳት አድርሷል።

    ተቋሙ የተቋቋመበት የራሱ ደንብና መመሪያ ያለው ነው፤ ነገር ግን ከተልዕኮው ውጭ የሆኑ ያለምንም አዋጭነት ጥናት ትልልቅ ግዥዎችን ፈጽሟል ያሉት ጠቅላይ ዐቃቤ ህጉ፥ የግዥዎችን አይነትና የነበረውን ሂደት ዘርዝረው አስረድተዋል።

    ሜቴክ እና የመርከቦች ግዥ

    ቀድሞ የመርከብ ድርጅት ይባል የነበረው የአሁኑ የየባህር ትራንዚትና ሎጅስቲክ ድርጅት አባይ እና አንድነት የሚባሉ ከ28 ዓመት ባለይ ያገለገሉ መርከቦች ነበሩት። እነዚህ መርከቦች በባለሙያ በማስጠናት ከዚህ በላይ መርከቦቹ አገልገሎት ላይ መቆየት የለባቸውም፤ ከቆዩ ከገቢያቸው ወጪያቸው ይበልጣል ስለተባለ እንዲሸጡ የሥራ አመራር ቦርዱ ይወስናል። በዚህ መነሻነት ገዥ ተፈልጎ አንድ የውጭ ድርጅት በሶስት ነጥብ ሶስት ሚሊዮን ዶላር አንዷን መርከብ ለመግዛት ቀረበ።

    ነገር ግን ለውጭ ድርጅት ከሚሸጥ ሜቴክ ቆራርጦ ብረቱን ይጠቀምበት በሚል ድርጅቱ ባቀረበው ዋጋ መሰረት በሶስት ነጥብ 276 ቢሊዮን ብር ሜቴክ እንዲገዛው ይደረጋል። ይሁን እንጂ ሜቴክ መርከቦቹን ቆራርጦ ብረቱን መጠቀም ትቶ መርከቦቹ አዋጭ አይደሉም የሚል ጥናት እያለ ወደ ንግድ ሥራ አስገብቷቸዋል።

    ወደ ንግድ ሥራ ከማስገባቱም በፊት መስከረም 15 ቀን 2005 ዓ.ም. የሜቴክ ሥራ አመራር ቦርድ ተሰብስቦ መርከቦቹ ጅቡቲ ወደብ ላይ ለረጅም ጊዜ ከቆዩና ተጨማሪ ወጭ ካስወጡ በኋላ ለጥገና ወደ ዱባይ ተልከዋል። ለጥገናውክ ከኮርፖሬሽኑ 513 ሚሊዮን 837 ሺህ ብር ወጪ ተደርጎ መርከቦቹ እንዲጠገኑ ተደርጓል። ጥገናውን የሚያከናውኑ ሰዎችን የሚያፈላልጉ ተብለው የተመረጡትም ሜቴክ ውስጥ ያሉ የድልለላ ሥራ የሚሠሩ ከተቋሙ ኃላፊዎች ጋር የስጋ ዝምድና ያላቸው ግለሰቦች ናቸው።

    በመጨረሻም መርከቦቹ ተጠግነው ወጥተዋል ተብለው ወደ ንግድ ገብተዋል። ነገር ግን የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ አድረገው መንቀሳቀስ ስለማይችሉ ለጥገና ብለው የተንቀሳቀሱበትን ፈቃድ የዘው ከኢራን ወደ ሞቃዲሾ በማድረግ እሰከ 500 ሺህ ዶላር አካባቢ ይሠራሉ። ይህ ገንዘብ ግን ወደሜቴክ ያልገባበት ሁኔታ አለ። ሥራውም ቢሆን ሕገ-ወጥ ነው። በመጨረሻ መርከቧ ሥራ መሥራት እንደማትችልና ፈቃድ እንደማታገኝ ሲታወቅና ተቃውሞ ሲያጋጥማቸው መርከቧ በሁለት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ብረ ተሽጣለች።

    ሜቴክ እና የአውሮፕላን ግዥ

    ይሄ ግዥ የተፈጸመበት ዓላማ በራሱ ችግር የለበትም። “አገራዊ ፐሮጀክቶችን በአውሮፕላን ታግዞ ለመከታተል” በሚል ያለምንም ጨረታ ከአንድ የእሥራኤል ኩባንያ በ11 ሚሊዮን 732 ሺህ 520 ብር ነው ግዥው የተፈጸመው። ነገር ግን ወደ ንግድ መግባት አለብን ተብሎ ፈቃድ በማውጣት ለመሥራት ተሞክሮ አልተሳካም።

    አውሮፕላኖቹ ከ50 ዓመት በላይ ያገለገሉ፣ የሚጠቀሙት ነዳጅ እጅግ ውድ፣ የቴክኒክ ችግርም ያለባቸውና ጥቅም ላይ ሊውሉ የማይቸሉ ናቸው ተብለው አራቱ ተቀምጠዋል። አንደኛው ግን እስካሁን የት እንዳለ አልታወቀም።

    በአጠቃላይም በሁለቱ ግዝዎች በመንግስት ላይ ከ24 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ደርሷል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

    ሜቴክ

Viewing 15 results - 436 through 450 (of 495 total)