Search Results for 'አዲስ አበባ'

Home Forums Search Search Results for 'አዲስ አበባ'

Viewing 15 results - 466 through 480 (of 495 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ኢመባ) – የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን (ኢመባ) 600 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍኑ የስምንት መንገዶች ግንባታ ሥራ የኮንትራት ስምምነት ከ13.8 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ከተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ተቋራጮች ጋር ተፈራረመ።

    የሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን አካል የሆኑና 600 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍኑ የስምንት መንገዶች የመንገድ ግንባታ ሥራዎች የኮንትራት ስምምነት ከብር 13.8 ቢሊዮን በላይ በሆነ ወጪ ጥቅምት 14 ቀን 2011 ዓ.ም በሒልተን ሆቴል ተፈራርሟል። የመንገድ ፕሮጀክቶቹ ዝርዝር መረጃ የሚከተለውን ይመስላል።

    1. ጣርማበር–መለያ–ሰፈሜዳ መገንጠያ 1 መለያ–ሞላሌ–መገንጠያ 2 ሞላሌ–ወገሬ መንገድ (ርዝመት 118.87 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 1,906,200,296.75 ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 36 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ መከላከያ ኮንስትራክሽን

    2. ጂማ–አጋሮ–ዴዴሳ ወንዝ መንገድ (ርዝመት 79.07 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 1,306,509,305.57 ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 42 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ ቻይና ሬል ዌይ 21ኛ ቢሮ ግሩኘ
    o ቀድሞ የነበረው የመንገዱ ደረጃ፦ አስፋልት

    3. መሰል/ሞሲሊ–ኮራ/ቆሪ–84.2 ኪ.ሜ /ኮንት 1/ መንገድ (ርዝመት 84.2 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 1,536,235,563.54 ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 42 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ ቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን ኢንጂነሪንግ ኮ. ሊሚትድ

    4. መሰል/ሞሲሊ–ኮራ/ቆሪ–84.2–ጠሩ ኪ.ሜ /ኮንት 2/ መንገድ (ርዝመት 73.34 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 1,502,371,329.85 ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 42 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ ቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን ኢንጂነሪንግ ኮ. ሊሚትድ

    5. አርሲ–ሮቤ–አጋርፋ–አሊ ኮንትራት 1 አሊ ከተማ-ዋቤ ድልድይ መንገድ (ርዝመት 53.5 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 2,153,060,671.98 ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 36 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ኩባንያ (ሲሲሲሲ)

    6. አዲአርቃይ–ጠለምት መንገድ (ርዝመት 76.6 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 1,981,378,049.64 ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 36 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ የንኮማድ ኮንስትራክሽን

    7. እስቴ–ስማዳ መንገድ (ርዝመት 53.08 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 1,925,451,264.41ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 36 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ኩባንያ (ሲሲሲሲ)

    8. ውቅሮ–አጽቢ–ኮነባ መንገድ (ርዝመት 63 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 1,745,722,493.86 ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 42 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ ሱር ኮንስትራክሽን

    የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በመግለጫው እንዳስታወቀው መንገዶቹ ከዚህ በፊት በጠጠር ደረጃ የነበሩ ሲሆን አሁን ግን በአስፋልት ደረጃ የሚገነቡ ይሆናሉ። ለነዚህም ግንባታ ሙሉ ለሙሉ የኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ይሆናል።

    የመንገዶቹ ግንባታ በሚጠናቀቅበት ወቅት እንደ ጤፍ፣ ማር እና ፍየል እንዲሁም ሌሎች የግብርና ምርቶችንም ሆነ ሌሎች ምርቶችን ካለምንም ችግር ወደ ገበያ ለማውጣት ያስችላሉ። በተጨማሪም ከዚህ በፊት በአካባቢው የነበረውን የተቀላጠፈ የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍ የአካባቢው ህብረተሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ ወደ ፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትን ሁኔታ ያመቻቻሉ።

    እነዚህ መንገዶች በአገሪቱ ካለው ማ ኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲሁም መንግሥት ከያዘው የድህነትና የኋላቀርነት ቅነሳ ስትራቴጂ አንጻር ከፍተኛ አስተዋጽዖ እንደሚያበረክቱ ይታመናል። የመንገዶቹ ግንባታ በሚጠናቀቅበት ወቅት ከዚህ በፊት በአካባቢው የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍ የአካባቢው ህብረተሰብ በቀላሉ ወደ ፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ከመሆኑም ባሻገር ፣ በኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሃብቶች ያመረቱትን ምርት ወደ ገበያ ለማውጣት እንዲችሉና ሌሎች ባለሃብቶችም በአካባቢው ኢንቨስት ለማድረግ ተነሳሽነትን ከመፍጠር አኳያ የዚህ መንገድ መገንባት ጉልህ ሚና ይጫወታል።

    ከዚህም በተጨማሪ በአካባቢው የስራ ዕድል እንዲፈጠር በማስቻል ፣ በአካባቢው የሚገኙ ትንንሽ መንደሮች በከተማ ደረጃ እንዲስፋፉና እንዲያድጉ ከማድረግ እንዲሁም የጤና ፣ የትምህርት እና ሌሎች የማህበራዊ አገልግሎት ተቋማት በሰፊው እንዲስፋፉ ከማድረግ አንፃር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታሉ ተብሎ ይታመናል። ስለሆነም የመንገድ ኘሮጀክቶቹ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ በአካባቢው የሚገኙ የመስተዳድር አካላትና፣ የክልሉ ነዋሪዎች ከፍተኛ ትብብር እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ያሳስባል።

    የኮንትራት ስምምነቱን የፈረሙት በኢመባ በኩል አቶ ሃብታሙ ተገኝ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሲሆኑ በተቋራጮቹ የሥራ ተቋራጮቹ ሥራ አስኪያጆች እና ተወካዮቻቸው ናቸው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን (ኢመባ)

    የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን

    Semonegna
    Keymaster

    የኢፌዴሪ መንግስት የፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመን የመልቀቂያ ጥያቄ ከተቀበለ ከሀያ ዓመታት በላይ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስር በአምባሳደርነትና የኢትዮጵያ ተጠሪነት ያገለገሉት አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ፕሬዝዳንት ሆነው እንደሚሾሙ የተለያዩ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

    አዲስ አባባ – ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) ሀሙስ ጥቅምት 15 ቀን 2011 ዓ.ም. በሚውለው የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች 2ኛ አስቸኳይ መደበኛ ስብሰባ የሥራ መልቀቂያ እንደሚያቀርቡ ይጠበቃል። የአስቸኳይ ስብሰባው ዋና አጀንዳ የፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመን የሥራ መልቀቂያ መቀበልና አዲስ ፕሬዚዳንት መምረጥ እንደሚሆን ተገልጿል።

    ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት መስከረም 27 ቀን 2006 ዓ.ም ሲሆን ሶስተኛው ፕሬዚዳንትም (ከዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እና አቶ ግርማ ወልደጊዮርጊስ ቀጥሎ) ናቸው።

    ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ አርጆ ከተማ በ1949 ዓ.ም ነው የተወለዱት፤ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በቻይና የፖለቲካ ኢኮኖሚ ፍልስፍና፣ ሁለተኛውን በህግና ዲፕሎማሲ ከአሜሪካ፣ 3ኛ ዲግሪያቸውን ከቻይና ቤጂንግ ዩኒቨርስቲ በህግ አግኝተዋል።

    ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ በጃፓንና በቻይና የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን፤ ከ1993-1994 ዓ.ም የግብርና ሚኒስትር፣ ከጥቅምት 1994-1998 ዓ.ም የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ሆነውም አገልግለዋል። በፕሬዝዳንትነት እስከተመረጡበት ጊዜም በቱርክ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ነበሩ።

    ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ የተለያዩ የምርምር ሥራዎችን በተለያዩ መስኮች ያከናወኑና በመምህርነትም ያገለገሉ ሲሆን ከአገር ውስጥ አማርኛና ኦሮምኛ ከውጭ ደግሞ እንግሊዝኛ፣ ቻይንኛና ፈረንሳይኛ ቋንቋዎችን መናገርና መጻፍ ይችላሉ።

    በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 70 ንዑስ አንቀጽ 4 መሰረት የአንድ ፕሬዝዳንት አገልግሎት ጊዜ ስድስት ዓመት ሲሆን፥ አንድ ግለሰብ ከሁለት ጊዜ በላይ በርዕሰ ብሔርነት ሊመረጥ እንደማይችል ይደነግጋል። ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ የመጀመሪያ ቨፕሬዝዳትነት አምስተኛ ዓመታቸው ነው።

    ከዚህ ጋር በተያያዘ የተለያዩ የሀገር ውስጥ ሚዲያዎች ኢትዮጵያን ከሀያ ዓመታት በላይ በሚኒስቴርነትና በአምባሳደርነት ያጋለገሉት አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ቀጣዩ የኢትዮጵያ ርዕሰ ብሔር (ፕሬዝዳንት) ይሆናሉ ብለው ቅድመ ግምታቸውን እየሰጡ ነው። በዚህም አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ፕሬዝዳንት ሆነው ከተመረጡ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያዋ እንስት ፕሬዝዳንት ይሆናሉ ማለት ነው።

    ለመሆኑ አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ማን ናቸው?

    ተወልደው ያደጉት አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሲሆን የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን የተከታተሉት በሊሴ ገብረማርያም ትምህርት ቤት ነው። አራት ሴት ልጆች ለነበሯቸው ወላጆቻቸው የመጀመሪያ ልጅ የሆኑት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገና በ17 ዓመታቸው ነጻ የትምህርት ዕደል አግኝትው ወደ ፈረንሳይ በማቅናት ሞንትፔልየር (Montpellier) በምትባለው የፈረንሳይ ከተማ በሚገኘው ዮኒቨርሲቲ ኦፍ ሞንትፔልየር (University of Montpellier) የተፈጥሮ ሳይንስን አጥንተዋል። በሀገረ ፈረንሳይ ለዘጠኝ ዓመታት ከቆዩ በኋላ ወደ ኢትዮጵይ በመመለስ በትምህርት ሚኒስቴር ውስጥ የሕዝብ ግንኙነት ክፍልን ማገልገል ጀመሩ። ቆይተውም የሕዝብ ግንኙነት ክፍሉን በበላይነት መርተዋል። ከዚያም ወደ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመዘዋወር በተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶች አገልግለዋል።

    ወሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በአምባሳደርነት ለመሾም ከአምባሳደር ዮዲት እምሩ ቀጥሎ ሁለተኛዋ እንስት ናቸው። በመጀመሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው የተሾሙትም ሴኔጋል ሲሆን የአምባሳደርነት ስልጣናቸውም ሴኔጋልን ጨምሮ ማሊን፣ ኬፕ ቨርዴን፣ ጊዚ ቢሳውን፣ ጋምብያን እና ጊኒን (እ.ኤ.አ 1989–1993) ያጠቃልል ነበር። ቀጥሎም እ.ኤ.አ 1983–2002 በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደርና በኢጋድ (IGAD) የኢትዮጵያ ተጠሪ ሆነው አገልግለዋል። እ.ኤ.አ ከ2002 ጀምሮ እስከ 2006 ድረሰ በፈረንሳይ (ሞሮኮን ጨምሮ) የኢትዮጵያ አምባሳደርና በዩኔስኮ (UNESCO) የኢትዮጵያ ተጠሪ ሆነው አገልግለዋል። እ.ኤ.አ ከ2006 ጀምሮ እስከ 2009 ድረስ በአፍሪካ ህብረት (AU) እና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የኢትዮጵያ ተጠሪ ሆነው ሀገራቸውን አገልግለዋል።

    ከሀያ ዓመታት በላይ በተለያዩ ሀገራትና ዓለማቀፋዊ ድርጅቶች የኢትዮጵያ አምባሳደርና ተጠሪ በመሆን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤትን ያገለገሉት አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ እ.ኤ.አ በ2009 የተበባሩት መንግስታት ድርጅትን (ተመድ) በመቀላቀል የድርጅቱ በመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ የተቀናጀ ሰላም ግንባታ መሪ (Head BINUCA) በመሆን ማገልገል ጀመሩ። ይህ አገልግሎታቸውም ወደ ሚቀጥለው ኃላፊነት አሸጋግሯቸው እ.ኤ.አ በ2011 ዓም የዚያን ጊዜ የተመድ ጠቅላይ-ጸሀፊ ባን ኪ-ሙን (Ban Ki-moon) አዲስ ለተቋቃመው በናይሮቢ የተመድ ጽህፈት ቤት (UNON) የመጀመሪያዋ ጠቅላይ-መሪ አድርገው ሾማቸው። በዚያም ለሰባት ዓመታት ካገለገሉ በኋላ እ.ኤ.አ በሰኔ ወር 2010 የአሁኑ የተመድ ጠቅላይ-ጸሀፊ አንቶንዮ ጉቴሬስ (António Guterres) አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴን በተመድ ጠቅላይ-መሪ ስር (Under-Secretary-General) የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተጠሪ (UN’s Special Representative to the AU) እና በአፍሪካ ህብረት ውስጥ የተመድ ጽህፈት ቤት ዋና ኃላፊ (Head of UNOAU) አድርገው ሾሟቸው እስካሁን ድረስ በዚሁ ሹመታቸው እያገለገሉ ይገኛሉ።

    አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ባለትዳርና የሁለት ወንድ ልጆች እናት ናቸው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ሳህለወርቅ ዘውዴ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አባባ – የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ ጥቅምት 12 ቀን 2011 ዓ.ም በይፋ ገንዘብ መሰብሰብ መጀመሩን የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከሁለት ወር በፊት ለኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማህበረሰብ የትረስት ፈንዱ እንዲቋቋም ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበው እንደነበረ ይታወሳል።

    በይፋ የተቋቋመው ትረስት ፈንድ ጥቅምት 12 ቀን ገንዘብ መሰብሰብ መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ገልጸዋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ አማካሪ ምክር ቤት ተቋቁሞ በይፋ ሥራ እንዲጀምር ላደረጉት ትጋትና ጥረት አባላቱን በኢትዮጵያ ሕዝብ ስም አመስግነዋል።

    በአሁኑ ወቅት በትረስት ፈንዱ ገንዘብ የማሰባሰብ ሥራ የመጀመሪያ ደረጃ ላይ እንዳለና ከዚህም በኋላ ብዙ ሥራ መሥራት እንደሚገባ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹት።

    ———————————————-

    ———————————————-

    የትረስት ፈንድ አማካሪ ምክር ቤቱ የፈንዱን አቅምና ውጤታማነት ለማሻሻል በትጋት መሥራት እንዳለበትም ዶክተር አብይ ተናግረዋል።

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማህበረሰብ የሚሰጡትን የተወሰነ ገንዝብ በአንድ ወይም በሁለት ጊዜ ጠቅልለው በመክፈል በጣም ወሳኝ ለሚባሉ ፕሮጀክቶች የሚያስፈልገውን ድጋፍ እንዲያፋጥኑም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠይቀዋል።

    በቀን ከአንድ ዶላር በላይ መስጠት ለሚችሉ ዜጎች ድጋፋቸውን በፍጥነት እንዲያድርጉና ዓለም አቀፉ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማኅበረሰብ ከትረስት ፈንድ ምክር ቤቱ ጋር ትብብራቸውን እንዲያደርጉ ዶክተር አብይ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

    የኢትዮጵያ የዳያስፖራ ትረስት ፈንድ የዳይሬክተሮች ቦርድ የተመረጡ ሲሆን ስም ዝርዝራቸው በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግም መጠቆማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የላከው መግለጫ ያስረዳል።

    ፈንዱ የዳያስፖራውን ተሳትፎ ለማቀናጀትና የልገሳውን ገንዘብ ለማሰባሰብ የሚያስችል እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን የባንክ ሒሳብ ቁጥሩም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000255726725 (አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ) ነው። ከዚህ የባንክ የሒሳብ ቁጥር በተጨማሪ ተቋሙ በኢንተርኔትም ገንዘብ እንደሚያሰባስብና ኦፊሴላዊ ድረ ገጹም “https://www.ethiopiatrustfund.org” እንደሆነ ክስር በተመለከተው ጋዜጣዊ መግለጫ አሳውቋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በተለያዩ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን እንዲወጡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው ባደረጉት ንግግር ጥሪ ማቅረባቸው ይታወቃል።

    በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በቀን ቢያንስ 1 የአሜሪካ ዶላር በመለገስ ለተለያዩ የልማት ሥራዎች ድጋፍ እንዲያደርጉ መጠየቃቸው የሚታወስ ነው።

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ ተቋም ምክር ሰጪ ካውንስል መግለጫ (ጥቅምት 10 ቀን 2011 ዓ.ም)

    የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ዳያስፖራ ፈንድ ተቋም ሰኞ ጥቅምት 12 ቀን 2011 ዓ.ም (October 22, 2018) ለሕዝብ መዋጮ መሰብሰቢያ ይከፈታል።

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ፈንድ ተቋም ምክር ሰጪ ካውንስል (ኢዲቲኤፍ) ሰኞ ጥቅምት 12 ቀን 2011 ዓ.ም (October 22, 2018) ለሕዝብ መዋጮ መሰብሰቢያ ያዘጋጀዉን ዝግጅት ለሕዝብ ይፋ አድርጎ ሥራዉን በኦፊሴላዊ ድረ-ገጽ https://www.ethiopiatrustfund.org እንደሚጀምር በደስታ ያስታዉቃል።

    ባለፉት ሳምንታት ካውንስሉ የዲያስፖራ ፈንዱን ሕጋዊና መንግስታዊ ደንቦችን በተከተለ መንገድ ፈንዱን ለመመስረት በትጋት ሠርቷል።

    የፈንዱ ካውንስል ምክር ቤት በዓለም ያሉ ዲያስፖራ ኢትዮጵያውያን ክቡር ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ በቀን 1 ዶላር ለህዝብ አርዳታ አዋጡ ያሉትን ጥሪ ተመልከቶ መዋጮ ለመስጠትና ፈንዱን በስራ ላይ ለማዋል ከፍ ያለ ጉጉት አንዳላቸው ይገነዘባል።

    ይህን ፍላጎት ለሟሟላትና ፈንዱን በሥነ ስርዓት ሥራ ማስጀመር ምክር ቤቱ ለትርፍ ያልተቋቋመ የበጎ አድራጎት ድርጅት ማቋቋም የባንክ ሂሳብ ቁጥር መክፈት ከኢንተርኔት ክፍያ ስርዓቶች እና ሌሎች የፋይናንስ መድረኮችን ጋር መደራደር አና የተለያዩ ደንቦችን ሟላትና አስተዳደራዊ እና የአፈፃፀም ሂደቶችን ለመቆጣጠር እና ግልጽነትን ለማረጋገጥ ምክር ቤቱ እነዚህን ሥራዎች በፍጥነት መወጣት ችሏል።

    ካውንስሉ ዓለምአቀፍ ዲያስፖራዎች ማኅበረሰቦች ለፈንዱ ላሳዩት መታገስና የማያወላዉል ድጋፍ ከፍተኛ ምስጋናዉን ያቀርባል።

    ካውንስሉ የኢትዮጵያ ዲያስፖራን የኢትዮጵያ ወዳጆች እና ሌሎች ነፃነት ዲሞክራሲ ሰብአዊ መብቶችን እና መልካም አስተዳደርን በኢትዮጵያ ማበልፀግ የሚፈልጉን ሁሉ በቀን 1 ዶላር መዋጮቻቸዉን በአንድ ጊዜ በጠቅላላው 365 የአሜሪካን ዶላር እንዲከፍሉ ባክብሮት ይጠይቃል። ይህንም በማድረግ አስፈላጊ ፕሮጀክቶችን ባፋጣኝ ለማስጀመር ይቻላል።

    ስለ ፈንዱ ለመማር እና መዋጮ ለማድረግ ወድዚህ ድህረ ገፅ ይሂዱ (ይጫኑ) https://www.ethiopiatrustfund.org/

    ልዩ ማስታወሻ – የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ በሚል ስም አንዳንድ በግል የተደራጁ ሰዎች ገንዘብ ለመሰብሰብ ጥረት እንደሚያደርጉ የፈንዱ ምክር ቤት ይረዳል። ነገር ግን ኦፊሴላዊ የሆነው በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ እ.ኤ.አ. ነሐሴ 9, 2018 በካውንስሉ የተቋቋመው ኤድቲኤ (EDTF) ብቸኛና መደበኛ በሕግ የታወቀው ነው።

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ

    Semonegna
    Keymaster

    በኢትዮጵያውያን የኪነ ጥበብ አድናቂዎች ዘንድ ተወዳጅነት እያተረፈ የመጣው ለዛ የአድማጮች ምርጫ ሽልማት ዘንድሮ ለስምንተኛ ጊዜ ጥቅምት 13 ቀን 2011 ዓ.ም በሂልተን ሆቴል፣ አዲስ አበባ፣ እጅግ በደመቀ ሁኔታ ተከናውኗል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – በሀገራችን የሙዚቃ ታሪክ እጅግ መቀዛቀዝ፣ የሙዚቃ አልበምም ህትመት መፍዘዝ፣ ፊልም ሠሪዎችም ሥራዎቻችውን ተመልካቾች ፊታቸውን ባዞሩባቸው በዚያ ወቅት እንደ አንድ የኪነጥበብ አባልና የሚዲያ ባለሙያ አቅማቸው በፈቀደ የበኩላቸውን አስተዋጽዖ ለማበርከት፣ እንዲሁም አድማጭ ተመልካቹን ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ለማነቃቃት በማሰብ ነበር ጋዜጠኛ ብርሀኑ ድጋፌ እና ባልደረቦቹ በሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ላይ “ለዛ የአድማጮች ምርጫ ሽልማት” ሥነ ስርዓትን የየጀመሩት።

    በእርግጥ ኪነ ጥበብና ኢትዮጵያ ሀገራችን በባህላዊውም ሆነ በዘመናዊው መንገድ እጅግ ብዙ ዓመታትን ያስቆጠረ ቁርኝት ቢኖራቸውም ቅሉ የኪነ ጥበብ ሙያዉን እንደተከበረ ሙያ ባለሙያዉንም የተከበረ ሙያ እንዳለው ቆጥሮ ወቅት ጠብቆ በተገደበ የጊዜ ኡደት ለሙያውና ለባለሙያው ተገቢውን ዕውቅና፣ ብሎም ክብር የሚሰጥ ቋሚ ተቋም ባለመኖሩ ያለመኖሩን በማስገንዘብ የሥነ ስርዓቱ ሀሳብ ጠንሳሾች “ለምን እኛ የቻልነውን አናደርግም?” በሚል ነበር የኪነ ጥበብ ሰዎችን በዓመት አንድ ጊዜ እያሰባሰቡ ለማወያየት፣ በዓመቱ በሙያውና በሙያቸው ጉልህ አስተዋጽዖ ያደረጉትን “በጎ ሥራ ሠርታችኋል! ይበል!” ለማለት ለዛ የኤድማጮች ምርጫ ሽልማትን በ2003 ዓ.ም የጀመሩት።




    በ2003 ዓ.ም በተደረገው የመጀመሪያ ሽልማት ‘የዓመቱ ምርጥ ነጠላ ዜማ’፣ ‘ምርጥ ተዋናይት’፣ ‘የዓመቱ ምርጥ ተዋናይ’፣ ‘የዓመቱ ምርጥ ፊልም’ እና ‘የዓመቱ ምርጥ አልበም’ በሚሉ አምስት ዘርፎች (ዘውጎች) ኢትዮጵያውያን የኪነ ጠበብ ሰዎች ተመርጠው የተሸለሙ ሲሆን ሽልማቱም ያገኙትም ከያኒት ዘሪቱ ከበደ “አርቴፍሻል” በሚለው ነጠላ ሙዚቃዋ፣ ተዋናይት ሰሃር አብዱልከሪም “ያንቺው ሌባ” በተሰኘ ፊቸር ፊልም ላይ ባሳየችው ትወና፣ ጋሽ አበበ ባልቻ “ሄሮሺማ” በተሰኘ ፊቸር ፊልም ላይ ባሳየው ትወና፣ “ሄሮሺማ” ፊቸር ፊልም በምርጥ በፊልምነት፣ እንዲሁም ከያኒ ናትናኤል አያሌው (ናቲ ማን) በመጀመሪያው አልበሙ በአምስቱ የተዘረዘሩት ዘርፎች አሸናፊዎች ሆነው የሥነ ስርዓቱ የበኩር ተሸላሚዎች ሆኑ።

    በዚህ መልኩ የተጀመረው ለዛ የአድማጮች ምርጫ በየዓመቱ ከጥቅምት ወር ጀምሮ እስከ ሃምሌ ድረስ የሚወጡ የኪነ ጥበብ ሰዎችንና ሥራዎችን በአድማጮች ምርጫ አወዳድሮ ዕውቅና እየሰጠ፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተሳታፊዎችን እያበዛ፣ በባለሙያዉም፣ በመራጭነት በሚሳተፈውም ይሁን በየበይ ተመልካችነት በሚከታተለው ኢትዮጵያዊ ዘንድም ተወዳጅነት እያተረፈ ዘንድሮ ለስምንተኛ ጊዜ ጥቅምት 13 ቀን 2011 ዓ.ም በሂልተን ሆቴል፣ አዲስ አበባ፣ እጅግ በደመቀ ሁኔታ ተከናውኗል። ከሁለት ወራት በፊት በተካሔደው ዘጠነኛው አዲስ የሙዚቃ ፌቲቫል ላይ የዓመቱ ምርጥ አርቲስት ተብሎ የተሸለመው ድምጻዊ ሮፍናን ኑሪ በዚህ ሥነ ስርዓትም ላይ ተመሳሳይ ሽልማት፣ ሌሎች ሁለት ሽልማቶችን ጨምሮ አሸንፏል። በስምንተኛው ለዛ የአድማጮች ምርጫ ሽልማት፦

    ● ምርጥ ነጠላ ዜማ፦ “ጨረቃ” (ሮፍናን ኑሪ)፣
    ● ምርጥ አዲስ ድምፃዊ፦ ሮፍናን ኑሪ (“ነፀብራቅ” በተባለው የሙዚቃ አልበሙ)
    ● ምርጥ የሙዚቃ አልበም፦ ነፀብራቅ (ሮፍናን ኑሪ)
    ● ምርጥ የሙዚቃ ክሊፕ፦- የመጀመርያዬ (ናትናኤል አያሌው/ናቲ ማን):-
    ● ምርጥ ተዋናይት፦ አዚዛ አህመድ “ትህትና” በተሰኘ ፊቸር ፊልም ላይ ባሳየችው ትወና፣
    ● ምርጥ ተዋናይ፦ አለማየው ታደሰ “ድንግሉ” በተሰኘ ፊቸር ፊልም ላይ ባሳየው ትወና፣
    ● ምርጥ ፊልም፦ “ድንግሉ”
    ● ምርጥ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ፦ ምን ልታዘዝ?

    አሸናፊ ሆነው ተሸልመዋል። በዚህ ሥነ ስርዓት ላይ እጅግ ለበርካታ ሙዚቀኞች የዘፈን ግጥም በመስጠት በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ ስሙ እጅጉን ጎልቶ የሚታወቀው የሙዚቃ ግጥም ገጣሚ (lyricist) ይልማ ገብረአብ “የ2010 ዓ.ም የኪነ ጥበባ በለውለታ” ሆኖ ልዩ የክብር ሽልማት ተሸልሟል። ገጣሚ ይልማ ገብረ አብ ከአንድ ሺህ በላይ የሙዚቃ ግጥሞችን ጽፎ ለተለያዩ ድምጻውያን አበርክቷል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ለዛ የአድማጮች ምርጫ


    Semonegna
    Keymaster

    የአሜሪካ ድምፅ ለባለሞያዎቹ ሥልጠና ሲሰጥ ያገር ውስጥ ጋዜጠኞችንም ቢያካትት ፍላጎታቸው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ስልጠና ለመስጠት አዲስ አበባ ከሚገኙ የአሜሪካ ድምጽ ጋዜጠኞች ጋር በተገናኙበት ጊዜ አስታውቀዋል።

    አዲስ አበባ – የአሜሪካ ድምፅ ለባለሞያዎቹ ሥልጠና ሲሰጥ ያገር ውስጥ ጋዜጠኞችንም ቢያካትት ፍላጎታቸው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የአሜሪካ ድምፅ የአፍሪካ ዲቪዥን ዳይሬክተር አቶ ንጉሤ መንገሻን እና የአፍሪካ ቀንድ ማኔጂንግ ኤዲተር ጋዜጠኛ ትዝታ በላቸውን በቢሯቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

    የአሜሪካ ድምፅ በኢትዮጵያና በጎረቤት ሃገሮች ለሚገኙ ዘጋቢዎቹ እስካለፈው ዓርብ የቆየ የአንድ ሣምንት ሥልጠና አዲስ አበባ ላይ ሰጥቷል።

    በኢሕአዴግ መንግሥትና በአሜሪካ ድምፅ መካከል ላለፉት 27 ዓመታት ከዘለቀ ውጣ ውረድ ያልተለየው ግንኙነት በኋላ አንድ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር የጣቢያውን ኃላፊዎች ተቀብሎ ሲያነጋግር ይህ የመጀመሪያው ነው።

    ለተጨማሪ መረጃ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ። ዘጋቢ እስክንድር ፍሬው ለአሜሪካ ድምጽ የአማርኛ ዝግጅት ክፍል

    ጋዜጠኛ ንጉሤ መንገሻ
    ትውልደ ኢትዮጵያዊው ንጉሤ መንገሻ ከ2014 (እ.ኤ.አ) ጀምሮ የአሜሪካ ድምጽ የአፍሪካ ዲቪዥን ዳይሬክተር (Africa Division Director) ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። ጋዜጠኛ ንጉሤ ወደ አሜሪካ የመጣው እ.ኤ.አ በ1981 ዓም ሲሆን በ1982 የአሜሪካ ድምጽን በሲኒየር ኤዲተርነት ተቀላቅሏል። ቀጠሎም የአሜሪካ ድምጽ የመካከለኛው አፍሪካ ሰርቪስ ቺፍ (Service Chief)፣ የአፍሪካ ዲቪዥን ፕሮግራም ማናጀር (Africa Division Program Manager)፣ አሁን ደግሞ ሆኖ የአፍሪካ ዲቪዥን ዳይሬክተር አገልግሏል/እያገለገለ ይገኛል።

    ጋዜጠኛ ትዝታ በላቸው
    በ ኤሉባቡር ዞን (የቀድሞው ኤሉባቡር ክፍለሀገር) ያዮ ወረዳ ውስጥ የተወለደችው ጋዜጠኛ ትዝታ በላቸው ወደ አሜሪካ የመጣችው እ.ኤ.አ በ1973 ሲሆን፥ ትምህርቷን ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ (Howard University) ተከታትላ የአሜሪካ ድምጽን የተቀላቀለችው የአማርኛ ዝግጅት ክፍሉ በተመሠረተ በሁለት ዓመቱ (እ.ኤ.አ በ1984) ነበር። በአሜሪካ ድምጽ (የአማርኛ ዝግጅት ክፍሉን ጨምሮ) በተለያዩ የጋዜጠኝነት ሙያ እርከኖች ያገለገለች ሲሆን በአሁኑ ወቅት የአፍሪካ ቀንድ ማኔጂንግ ኤዲተር (Horn of Africa Managing Director) ሆና እየሠራች ነው።

    የአሜሪካ ድምፅ

    Semonegna
    Keymaster

    ኢትዮጵያውያን የፋሽን ዲዛይነሮች ለዓለም ገበያ የኢትዮጵያን ምርት ይዘው ሲወጡ ምርቱን ብቻ ሳይሆን ሜድ ኢን ኢትዮጵያ በሚለው ሳያሜ ኢትዮጵያዊነትንም በማስተዋወቅ ደረጃ ጉልህ አስተዋጽዖ አያደረጉ እንደሆነ እንደሚሰማቸው ይናገራሉ።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ)– ኢትዮጵያውያን ዲዛይነሮች በኢትዮጵያ የተመረተ ሜድ ኢን ኢትዮጵያ በተሰኘው መለያ አገራቸውን ለማስተዋወቅ ተስፋ ሰንቀዋል።

    ዲዛይነር ሳምራዊት መርሲኤሓዘን ኢትዮጵያ ውሰጥ የተሰራ ሜድ ኢን ኢትዮጵያ የተሰኘ መለያን የያዙ ቦርሳዎችና ሌሎች የቆዳ ውጤቶችን በማምረት አገሯን የማስተዋወቅ ራዕይ ይዛ እየሰራች ትገኛለች።

    በእንስሳት ሃብት ከአፍሪካ ቀዳሚ እየተባለች ለዘመናት የምትታወቀው ኢትዮጵያ ከቆዳ ውጤቶች እምብዛም አለመጠቀሟ ዲዛይነር ሳምራዊትን ያስቆጫታል። እንደ እርሷ አገላለጽ አሁንም ቢሆን በቁጭት ከተሠራ በእንስሳት ሃብት ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ በተመረቱ የቆዳ ውጤቶች አገርን ለማስጠራት ጊዜው አልረፈደም።

    ለዚህ የእርሷ የቆዳ ቦርሳ፣ ምንጣፍና ሌሎች ምርቶች ተደራሽ በሆኑባቸው አገራት ያለውን ተቀባይነት በማንሳት ታብራራለች። ለዓለም ገበያ የኢትዮጵያን ምርት ይዛ ስትወጣ ምርቱን ብቻ ሳይሆን ሜድ ኢን ኢትዮጵያ በሚለው ሳያሜ ኢትዮጵያዊነትንም እየሸጠች መሆኑን እንደሚሰማት ነው የተናገረችው።

    ሥራዋን ከጀመረች ስድስት አመታትን ያስቆጠረችው ዲዛይነሯ፤ ጀርመን፣ ጃፓንና ሆላንድ ምርቷን ከምታቀርብባቸው አገሮች መካከል ሲሆኑ በቀጣይም የዱባይና እንግሊዝ ገበያን ለመድረስ ዕቅድ አላት።

    የውጭ ገበያን ሰብሮ ለመግባት መጀመሪያ የራሳችንን መቀበልና የራሳችንን ማድነቅ መጀመር አለብን የሚል ሃሳብም አንስታለች።

    በቆዳ ምርቶች ያደጉ አገሮች ለዲዛይን፣ ለአሠራርና አጨራረስ የሚጠቀሙበትን ዘዴ ልምድ በመውሰድ መወዳደር አለብን የሚል እሳቤም አላት ዲዛይነር ሳምራዊት።

    “በውጭ ባህል ጥገኛ ከመሆን የብሔር ብሔረሰቦችን የአለባበስ ስርዓት ከዓለም አቀፍ ፍላጎት ጋር በማመጣጠን መለያ በማድረግ ልንታወቅበት የምንችል የገበያ ዘርፍ ነውም” ስትል ትገልጻለች።

    የቀደምት ኢትዮጵያውያን እናቶች መገለጫ ከሆነው “ፈትል” በተሠሩ የአገር ባህል ልብሶችም ኢትዮጵያን ለዓለም ለማስተዋወቅ ተስፋ ማድረጋቸውን “የፈትል ዲዛይነር” ሽያጭ ሠራተኛ ወጣት ፌቨን ተስፋዬ ትናገራለች።

    የኢትዮጵያ ፈትል በማንኛውም ሰዓት ሊለበስ በሚችል መልኩ በማምረት አሜሪካን ጨምሮ ሌሎች አገሮች ምርቱን ካገኙ በጉጉት እንደሚወስዱ ታዝባለች። ልብሱ የተሠራበት ጥሬ እቃ ከፈትል መሆኑ በተለያዩ አገራት አድናቆትን እያገኘና ባህልን እያስተዋወቀ መሆኑንም ፌቨን ትናገራለች።

    ሌላዋ አስተያየት ሰጪ ዲዛይነር ቁንጅና ተስፋዬ ዘወትር የሚለበሱ የኢትዮጵያን ባህል የሚገልጹ ልብሶችን በመሥራት ለአገር ውስጥና ለውጪ ገበያ በማቅረብ ላይ ትገኛለች።

    ቪድዮ፦ የኢትዮጵያ አልባሳትና ባህላዊ ዲዛይኖች የዓለም ገበያን ሰብረው እንዲገቡ ለማድረግ ብዙ መሠራት አለበት

    የምትሠራቸው አልባሳት የኢትዮጵያን አንዱን ብሔረሰብ አለባበስ በሚገልጽ መልኩ በመሆናቸውም በእያንዳንዱ ልብስ የኢትዮጵያ ብሔረሰቦችን ባህል እያስተዋወቀች መሆኗን ተናግራለች።

    ከዚህ በፊት በዓለም ላይ የተሰሩት የአለባበስ ዲዛይኖች እየተደጋገሙ በመሆናቸውና አሁን አሁን እነሱ በሠሩት ዲዛይን መሠረት ዓለም ወደ አፍሪካ ፊቱን እያዞረ መሆኑን በመግለጽ ይህን ዕድል አገራችንን ለማስተዋወቅ መጠቀም አለብን የሚል አስተያየትም ሰጥታለች።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    ሜድ ኢን ኢትዮጵያ

    Semonegna
    Keymaster

    ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ለ13ኛ ጊዜ በሚያካሂደው ዓመታዊ የኪነ ህንጻ አውደ ርዕይ “ኪነ ህንጻና የከተማ ፕላን” በሚል መሪ ሀሳብ ከጥቅምት 8 ቀን እስከ ጥቅምት 11 ቀን 2011 ዓ.ም በብሔራዊ ቲያትር ይካሄዳል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ በየዓመቱ የሚያካሂደው ዓመታዊ የኪነ ህንጻ አውደ ርዕይ ጥቅምት 8 ቀን 2011 ዓ.ም. ይጀመራል።

    ለ13ኛ ጊዜ በሚካሄደው አውደ ርዕዩ “ኪነ ህንጻና የከተማ ፕላን” በሚል መሪ ሀሳብ በብሔራዊ ቲያትር ይካሄዳል።
    የዩኒቨርሲቲው የኪነ ህንጻና የከተማ ፕላን የትምህርት ክፍል ሃላፊ አቶ ቴዎድሮስ ገብረጻዲቅ ለኢዜአ እንደገለጹት አውደ ርዕዩ የትምህርት ክፍሉ ተማሪዎች የሥራ ውጤቶቻቸውን የሚያቀርቡበት ነው።

    አውደ ርዕዩ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አጠናቅቀው ወደ ዘርፉ ኢንዱስትሪ ከመቀላቀላቸው በፊት ሥራዎቻቸውን ለኅብረተሰቡ፣ ለመንግስት ተቋማትና ለዘርፉ ባለድርሻ አካላት በማቅረብ ልምድ የሚቀስሙበት እንደሚሆን አቶ ቴዎድሮስ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ ተማሪዎቹ እርስ በእርስ እንዲማማሩም መልካም አጋጣሚ ይፈጥርላቸዋል።

    የተሻለ አቅም ያላቸው ተማሪዎች ወደ ሥራ ዓለም ሲገቡ በዘርፉ ያለውን የሰለጠነ የሰው ሃይል እጥረት ከመቅረፍ አንጻር አስተዋጽዖ እንደሚያበረክቱም ነው አቶ ቴዎድሮስ ያስረዱት።

    አውደ ርዕዩ በየዓመቱ ሲካሄድ በአማካይ እስከ ሁለት ሺህ ሰው እንደሚጎበኘውና ዘንድሮም ከአንድ ሺህ በላይ ተሳታፊዎች እንደሚጎበኙት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።

    ALSO: EVENT: The 9TH ADDISBUILD: International Construction, Steel, Construction Machinery & Infrastructure Exhibition

    በአውደ ርዕዩ የዩኒቨርሲቲው የዘንድሮ የትምህርት ክፍሉ 60 ተማሪዎች የሥራ ፕሮጀክቶቻቸውን እንደሚያቀርቡና የተሻለ ሥራ ያቀረቡ ተማሪዎች የኢትዮጵያ የኪነ ህንጻ ባለሙያዎች ማኅበር (Association of Ethiopian Architects) በሚያዘጋጀው ዓመታዊ ውድድር እንደሚሳተፉም ጠቁመዋል።

    በዚህ አውደ ርዕይ ሌሎች የመንግስትና የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንደሚሳተፉም ተናግረዋል።

    በብሔራዊ ቲአትር አዳራሽ የሚካሔደው አውደ ርዕይ ከጥቅምት 8 ቀን እስከ ጥቅምት 11 ቀን 2011 ዓ.ም የሚቆይ ይሆናል።

    ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ከሚሰጣቸው የትምህርት ዘርፎች አንዱ “ኪነ ህንጻና የከተማ ፕላን” ሲሆን በዚሁ ትምህርት ዘርፍ ተማሪዎችን በመጀመሪያ ዲግሪ (bachelors degree) አስተምሮ ያስመርቃል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    አዲሱ የካቢኔ አባላት ሹመት የቀረበው የአስፈፃሚ አካላት ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣውን አዋጅ እንደገና ለማሻሻል የቀረበውን አዲስ ረቂቅ አዋጅ በምክር ቤቱ መፅደቁን ተከትሎ መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት  አስታውቋል።

    አዲስ አበባ – የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከ20 አዳዲስ የካቢኔ አባላት ሹመት ውስጥ 50 በመቶ ሴቶች ሆነው እንዲያገለግሉ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) የቀረበውን ሹመት ጥቅምት 6 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ አፀደቀ።

    የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን እያደረገ የሚገኝ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከሚሾሙት 20 ካቢኔዎች ውስጥ 10 ሴቶች ሆነው በተሰጣቸው ኃላፊነት እንዲያገለግሉ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

    አዲሱ የካቢኔ አባላት ሹመት የቀረበው የአስፈፃሚ አካላት ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣውን አዋጅ እንደገና ለማሻሻል የቀረበውን አዲስ ረቂቅ አዋጅ በምክር ቤቱ መፅደቁን ተከትሎ ነው።

    በዚህም መሠረት የሹመቱ ዋና መስፈርት ብቃት፣ የትምህርት ዝግጅትና ለውጥን የመምራት አቅም መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ከሚሾሙት ካቢኔዎች 50 በመቶ (በቁጥር፥ ወይም ከ20ዎቹ 10 ሴት) ካቢኔዎች መሆናቸውንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልፀዋል።

    ይህም በኢትዮጵያ ምናልባትም በአፍሪካ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑም በምክር ቤቱ ተገልጿል።

    በዚህ በተደረገው የካቢኔ ሹመት ለውጥ ውስጥ ከዚህ በፊት “የፐብሊክ ሰርቪስ እና ሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር” ተብሎ ይጠራ የነበረው ሚኒስቴር ተለውጦ አሁን “ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን” (Civil Service Commission) በሚል እንደተተካ ታውቋል። ከዚህ በተጨማሪ ሶስት ኮሚሽኖችም በአዲስ መልክ ተካተዋል፤ እነዚህም (1) የሥራ ፈጠራ ኮሚሽን (Job Creation Commission)፣ የአካባቢ፣ የደንና የአየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽን (Environment, Forestry and Climate Change Commission) እና የፕላንና እድገት ኮሚሽን (Plan and Development Commission) ናቸው።

    አዲስ በተዋቀረው ካቢኔ ውስጥ የተሰየሙት ባለስልጣናትና የተሰየሙበት ስልጣን ዝርዝር

    1. ዶ/ር ሂሩት ካሳው ― የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር
    2. ዶ/ር ሂሩት ወልደማርያም ― የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር
    3. ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ― የሰላም ሚኒስቴር
    4. ዶ/ር ሳሙኤል ሆርቃ ― የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር
    5. ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ― የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር
    6. አቶ ብርሃኑ ጸጋዬ ― ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ
    7. አቶ አህመድ ሺዴ ― የገንዘብ ሚኒስቴር
    8. ዶ/ር አሚን አማን ሐጎስ ― የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር
    9. ወ/ሮ አዳነች አበበ ― የገቢዎች ሚኒስቴር
    10. ኢ/ር አይሻ መሀመድ ሙሳ ― የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር
    11. አቶ ኡመር ሁሴን ― የግብርና ሚኒስቴር
    12. ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ ― የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር
    13. ወ/ሮ የዓለምፀጋይ አስፋው — የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር
    14. ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ― የትራንስፖርት ሚኒስቴር
    15. አቶ ጃንጥራር አባይ ― የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
    16. ዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን መኩሪያ ― የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር
    17. ዶ/ር ጥላዬ ጌጤ ― አምባዬ የትምህርት ሚኒስቴር
    18. ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ― የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
    19. ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረ-እግዚአብሔር ― የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር
    20. ዶ/ር ፍፁም አሰፋ ― የፕላን ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የካቢኔ አባላት ሹመት

    Semonegna
    Keymaster

    ሱማሌላንድ ውስጥ የሚገኘው የበርበራ ወደብ በባለቤትነት ደረጃ የኤምሬቱ ዲፒ ወርልድ 51 በመቶ፣ የሶማሌላንድ አስተዳደር 30 በመቶ እና የኢትዮጵያ መንግስት ደግሞ 19 በመቶ ድርሻ አላቸው።

    አዲስ አበባ (ሶማሌላንድ ሰን/ ኢዜአ) – ኢትዮጵያ 19 በመቶ ባለድርሻ የሆነችበት የሶማሌላንድ የበርበራ ወደብ ግንባታ ተጀመረ።

    ጥቅምት 1 ቀን 2011 ዓ.ም የግንባታ ማስጀመር ሥነ ስርዓቱ ሲካሄድ በሥነ ስርዓቱ ላይ የሶማሌላንድ አስተዳድር እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እና የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች ተካፍለዋል።

    መቀመጫውን ዱባይ ያደረገው ዲፒ ወርልድ (DP World) የተባለው የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች (UAE) ኩባንያ በ420 ሚሊዮን ዶላር የበርበራ ወደብ ግንባታን ለማካሄድ ውል ገብቶ ሥራውን ጀምሯል።

    በስምምነቱ መሠረት በወደቡ ግንባታ የኤምሬቱ ዲፒ ወርልድ 51 በመቶ፣ የሶማሌላንድ አስተዳደር 30 በመቶ እና የኢትዮጵያ መንግስት ደግሞ 19 በመቶ ድርሻ ይዘዋል ተብሏል።

    ከግንባታ በኋላ የሶማሌላንድ መንግስት፣ የኢትዮጵያ መንግስት እና ዲፒ የበርበራ ወደብ ላይ ያላቸው ውል ለ30 ዓመት የሚቆይ መሆኑንም ተመልክቷል።

    የሶማሌ ላንድ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ (Muse Bihi Abdi) በሥነ ስርዓቱ ላይ እደንደተናገሩት የበርበራ ወደብ ግንባታ እውን መሆን የሶማሌላንድ ኢኮኖሚን ከማነቃቃት ባሻገር ለቀጠናው የንግድና ኢኮኖሚ ትስርስር ፋይዳው የጎላ ነው።

    በተያያዘ ዜና ሞጆ ደረቅ ወደብ ላይ የሚገነባው የኢትዮጵያ ንግድ ሎጂስቲክስ ፕሮጀክት የዲዛይን ጥናት እየተጠናቀቀ መሆኑን የኢትዮጵያ ማሪታይም ጉዳይ ባለስልጣን ገለጸ።

    ባለስልጣኑ አስመጪዎች፣ ላኪዎችና የተለያዩ ደንበኞች በሞጆ ደረቅ ወደብ ላይ የሚደርስባቸውን መጉላላት ለመቀነስ አሰራሩን ዘመናዊ ለማድረግ የሞጆ ሎጂስቲክስ ማዕከልን ሊገነባ መሆኑ ይታወቃል።

    ተመሳሳይ ዜና፦ ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ላይ የአሰብ እና የምጽዋ ወደቦችን መጠቀም ለመጀመር ዝግጅቷን እያጠናቀቀች ነው

    በዚህም ባለስልጣኑ እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር ሐምሌ 2017 ከዓለም ባንክ የዲዛይን ፈቃድ አግኝቶ በመጀመሪያ የዲዛይን ጥናቱ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያደረገ ነው።

    በማሪታይም ጉዳይ ባለስልጣን የኢትዮጵያ ንግድ ሎጂስቲክስ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ዶክተር መንግስት ኃይለማርያም እንዳሉት፤ ግንባታው የሚከናወነው ከዓለም ባንክ በተገኘ 150 ሚሊዮን ዶላር ነው። የዓለም ባንክ ይህንን ገንዘብ ለኢትዮጵያ በክሬዲት መልክ የሰጠው እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር መጋቢት 31 ቀን 2017 ነበር።

    ግንባታው እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ2022 እንደሚጠናቀቅና የዲዛይን ጥናቱም በተያዘለት የጊዜ ገደብ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

    በዲዛይን ጥናቱ በመጀመሪያው ምዕራፍ ዓለም ባንክን ጨምሮ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ከተደረገበት በኋላ ሁለተኛው የግንባታ ምዕራፍ ይጀምራል ብለዋል።

    ግንባታው ሲጠናቀቅም በሞጆ ደረቅ ወደብ ላይ ያለውን አሰራር ወደ ኤሌክትሮኒክስ በመቀየር ቀልጣፋ፣ ፈጣንና ዘመናዊ አሠራር ይኖረዋል ነው ያሉት።

    የሞጆ ደረቅ ወደብ የመሰረተ ልማት አቅርቦት እጥረት፣ የአስተዳደርና አገልግሎት አሰጣጥ ችግርና የተሟላ የኤሌክትሮኒክስ ስርዓት ችግር እንዳለበት ገልጸዋል።

    በመሆኑም የሚገነባው የኢትዮጵያ ንግድ ሎጂስቲክስ ፕሮጀክት እነዚሀን ችግሮች በዘመናዊና በተቀናጀ መንገድ ማከናወን ያስችላል ብለዋል።

    ምንጭ፦ ሶማሌላንድ ሰን እና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    የበርበራ ወደብ

    Semonegna
    Keymaster

    በጥቅምት ወር ዓም የጸደቀው የኢትዮጵያ የፊልም ፖሊሲ የፊልም ኢንዱስትሪውን ዘርፍ በአግባቡ እንዲያሳድገው ከተፈለገ የማስፈጸሚያ ሰነድ ሊዘጋጅለት ይገባልበሀገሪቱ ውስጥ በፊልም ሥራ ላየ እንደተሰማሩ ባለሙያዎች ማብራሪያ።

    በጌትነት ተስፋማርያም (የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት)

    አዲስ አበባ – የኢትዮጵያ የፊልም ፖሊሲ ዘርፉን በአግባቡ እንዲያሳድገው ከተፈለገ የማስፈጸሚያ ሰነድ ሊዘጋጅለት እንደሚገባ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ገለጹ።

    የኢትዮጵያ ፊልም ሠሪያዎች ማህበር የቀድሞ ፕሬዚዳንት አርቲስት ደሳለኝ ኃይሉ እንደገለጸው፤ የዘርፉን ችግሮች ለማቃለል የሚያስችል አ ሠራር ይኖረዋል የተባለው ፖሊሲ ባለፈው ዓመት ጸድቋል። ነገር ግን ፖሊሲው ዝርዝር ጉዳዮችን የማይዝ በመሆኑ እያንዳንዱን የዘርፉን ችግሮች ሊቀርፍ የሚችል የማስፈጸሚያ ሰነድ ሊዘጋጅ ይገባል።

    እንደ አርቲስት ደሳለኝ ገለጻ፤ የፊልም ኢንዱስትሪው ለአምስት መቶ ሺህ ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠር የሚችል መሆኑን በጥናት ተረጋግጧል። ነገር ግን እስካሁን በአግባቡ ስላልተሠራበት ውጤቱ እምብዛም ነው። ከአጠቃላይ የአገሪቷ ገቢ ውስጥ ያለው ድርሻም ዝቅተኛ ነው። የፊልም ፖሊሲው አስፈጻሚ አካል ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ካለው የሰው ኃይል፣ የፊልም ጥበብ ዕውቀት ችግር እና አደረጃጀት አኳያ ዘርፉን በሚገባው ልክ እያገዘ አይደለም። በመሆኑም የፊልም ባለሙያዎች ዋነኛውን ድርሻ በመውሰድ ለፖሊሲው ማስፈጸሚያ ስትራቴጂ ለማውጣት ሌት ከቀን መሥራት ይጠበቅባቸዋል።

    የፊልም ባለሙያው ዮናስ ብርሃነ መዋ በበኩሉ፤ እንደ አንድ የፊልም ባለሙያ ፖሊሲው ሲጸድቅ በኢንዱስትሪው ያሉት ችግሮች ይቀረፋሉ ብሎ እንደጠበቀ ገልጿል። ዝርዝር ጉዳዮችን ለማስተካከል እና ወጥ አሠራር ለማምጣት የማስፈጸሚያ ሰነዱ የግድ መዘጋጀት እንዳለበት ባለሙያዎች ሊገነዘቡ እንደሚገባ ተናግሯል። የማስፈጸሚያ ሰነዱንም ለማዘጋጀት የሚያስችል ቡድን ከባለድርሻ አካላት ተውጣጥቶ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴርን በር በየጊዜው በማንኳኳት ለተግባራዊነቱ መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግ ጥሪ አቅርቧል።

    የኢትዮጵያ የፊልም ሠሪዎች የዘርፍ ማኀበር ፕሬዚዳንት አቶ ቢንያም አለማየሁ እንደገለጸው፤ የማስፈጸሚያ ሰነዱ ቢዘጋጅ በመጀመሪያ ኢንዱስትሪው በማደጉ ተጠቃሚ የሚሆነው ባለሙያው ነው። በመሆኑም አርቲስቶች፣ ዳይሬክተሮች እና በፊልም ኢንዱስትሪው ውስጥ የሚሳተፉ ግለሰቦች ሳይሰለቹ ለፖሊሲው የማስፈጸሚያ ሰነዱ ዝግጅት መሥራት አለባቸው። በዘርፉ ያለውን የዕውቀት፣ የገቢ እና የአሠራር እድገት ለማስመዝገብ ማስፈጸሚያ ሰነዱ ቁልፍ ሥራ መሆኑን በመረዳት ማንኛውም ባለሙያ በንቃት ሊሳተፍ እንደሚገባ ገልጿል።

    የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ ሰላም ኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያ የፊልም ሠሪዎች የዘርፍ ማኅበር በጋራ ያዘጋጁት የኢትዮጵያ ፊልም ፖሊሲ ትግበራ ላይ ያተኮረ ውይይት ሰሞኑን በብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አዳራሽ ማካሄዱ ይታወሳል። በውይይቱ መጨረሻ ከ20 ያላነሱ በኪነጥበቡ ላይ ተሳትፎ ያላቸው በጎፈቃደኛ ባለሙያዎች የፊልም ፖሊሲው ማስፈጸሚያ ሰነድ ለማዘጋጀት በሚደረገው ጥረት ቀጥተኛ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ተመርጠዋል።

    እንደ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር መረጃ፥ የኢትዮጵያ የፊልም ፖሊሲ በኢፌዴሪ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ጥቅምት 24 ቀን 2010 ዓ.ም. መጽደቁ ይታወሳል።

    በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀውን የፊልም ፖሊሲ እና ስትራቴጂ ሙሉ ዶሴ (ፋይል) በፒ.ዲ.ኤፍ (PDF) እዚህ ጋር ያገኙታል

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

    የኢትዮጵያ የፊልም ፖሊሲ

    Semonegna
    Keymaster

    የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 የስኳር ፋብሪካ የምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ጨምሮ የተለያዩ የክልል፣ የፌደራል እና የውጭ ሀገር ባለስልጣናት ተገኝተዋል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድና የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 የስኳር ፋብሪካ መርቀው ከፈቱ።

    በኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን ንብረትነት በተገነባው በዚሁ ፋብሪካ የምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ የኤርትራው ፕሬዝዳንት አማካሪ የማነህ ገብረአብ፣ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወርቅነህ ገበየሁየቻይና ልማት ባንክ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ቡ ዪ እንዲሁም የደቡብ ክልል ርዕስ መስተዳደር አቶ ሚሊዮን ማቲዮስን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት ባለስልጣናትም ተገኝተዋል።

    ከቻይና ልማት ባንክ በተገኘው 8 ቢሊዮን ብር ብድር የተገነባው ይህ ፋብሪካ በቻይናው ቻይና ኮምፕላንት ግሩፕ ተቋራጭነት የተገነባ ሲሆን የሙከራ ምርቱን ዛሬ ይጀምራል። ፋብሪካው የሙከራ ሥራውን የሚጀምረው ከ2ሺህ እስከ 3ሺህ ቶን ሸንኮራ አገዳ በመፍጨት ነው።

    ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ መሥራት ሲጀምር በቀን ከ8 ሺህ እስከ 10 ሺህ ኩንታል ስኳር የማምረት አቅም የሚኖረው ሲሆን የዓለም ገበያን ፍላጎት መሠረት በማድረግም ጥሬ ስኳር (raw sugar)፣ ነጭ ስኳር (plantation white sugar) እና የተጣራ ስኳር (refined sugar) ማምረት ይችላል። ከሁለት ወር በፊት በተደረገው ፍተሻ የፋብሪካው ማምረቻ ማሽኖች ወደ ምርት ለመሸጋገር ዝግጁ መሆናቸው ተረጋግጠዋል።

    በኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት ስር በሚገኙ አራቱም ፋብሪካዎች በ100 ሺህ ሄክታር በላይ የሸንኮራ አገዳ ለማልማት የመስኖ መሠረተ ልማት ተከናውኗል፤ እስካሁንም ባለው ሂደት 30ሺህ ሄክታር መሬት የመስኖ ውሃ እንዲያገኝ ማድረግ ተችሏል። የመስኖ ውሃ ካገኘው መሬት ውስጥም 16ሺህ ሄክታር በሚሆነው መሬት ላይ ሸንኮራ አገዳ መተከሉም ተገልጿል።

    ዜና፦ ቬሎሲቲ አፓረልዝ ኩባንያ ኢትዮጵያ ውስጥ የመጀመርያ የሆነውን የግል የኢንዱስትሪ ፓርክ ሊገነባ ነው።

    የአሞ ኩራዝ ቁጥር ሁለት ስኳር ፋብሪካ ወደ ምርት በተሸጋገረበት በመጋቢት ወር 2008 ዓ.ም የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ፋብሪካ ግንባታ በይፋ መጀመሩ ይታወሳል። ግንባታውም የተከናወነው ከቻይና ልማት ባንክ በተገኘ ከ8 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ነው።

    ፕሮጀክቱ ወደ አገልግሎት መግባቱ በአገሪቱ ስኳር ወደ ማምረት የተሸጋገሩ ፋብሪካዎችን ቁጥር ወደ ስምንት (ወንጂ ሸዋ፣ መተሐራ፣ ፊንጫአ፣ ከሰም፣ ተንዳሆ፣ አርጆ ዲዴሳ፣ ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 2 እና 3) ያደርሰዋል።

    በኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት ስር ከሚገነቡት አራት የስኳር ፋብሪካዎች አንዱ የሆነው ይህ ፋብሪካ፤ በደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል የኦሞ ወንዝን በሚያዋስኑት በከፋና ቤንች ማጂ ዞኖች መሃል ይገኛል።

    ኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት ከተቋቋመ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ ከ110 ሺህ በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ከኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 የስኳር ፋብሪካ ተመረቀ

     

    Semonegna
    Keymaster

    እንደ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ገለጻ፥ እስካሁን ባለው ተሞክሮ የአንድ ፓርክ ግንባታ ከዘጠኝ ወር እስከ አንድ ዓመት ይጠናቀቃል፤ በዚህ መሠረት  አሁን በግንባታ ላይ ያሉት የኢንዱስትሪ ፓርኮች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ይጠናቀቃሉ።

    አዲስ አበባ – እስከ አሁን ወደ ምርት የገቡትን አራቱን የኢንዱስትሪ ፓርኮችና በቅርቡ የተመረቀውን የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ጨምሮ በ2012 ዓ.ም ማጠናቀቂያ 15 የኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ማምረት እንደሚገቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ።

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኦፕሬሽንና ማኔጅመንት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ሰለሞን በተለይ እንደተናገሩት፤ እስካሁን የሀዋሳ፣ የቦሌ ለሚ ቁጥር አንድ አይሲቲ፣ የመቐለ እና ኮምቦልቻ ፓርኮች ግንባታቸው ተጠናቆ ወደ ሥራ ገብተዋል። ከቀናት በፊት የተመረቀውን የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ጨምሮ የጅማና የደብረ ብርሃን በሁለት ወራት ውስጥ ወደ ሥራ ይገባሉ።

    የቦሌ ለሚ ቁጥር ሁለት፣ የባህር ዳር፣ የድሬዳዋና የቂሊንጦ ፋርማስቲዩካል ፓርኮች በተያዘው በጀት ዓመት የሚጠናቀቁ መሆናቸውን ገልፀው ከዚህ በተጨማሪ የአይሻ፣ የአረርቲ የአሶሳና ሠመራ ፓርኮች በዚሁ ዓመት ግንባታቸውን ለመጀመር የአዋጭነት ጥናቶቻቸው ተጠናቆ ወደ ስምምነት እየተገባ መሆኑን ተናግረዋል። እስካሁን ባለው ተሞክሮ የአንድ ፓርክ ግንባታ ከዘጠኝ ወር እስከ አንድ ዓመት ይጠናቀቃል ያሉት ኃላፊው ሌሎቹም በዚሁ መሠረት በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ይጠናቀቃሉ ብለዋል።

    ተያያዥ ዜና፦ ቬሎሲቲ አፓረልዝ ኩባንያ ኢትዮጵያ ውስጥ የመጀመርያ የሆነውን የግል የኢንዱስትሪ ፓርክ ሊገነባ ነው።

    ፓርኮቹ የተለያዩ ምርቶችን የሚያመርቱ ቢሆንም በዋናነት መንግሥት በኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ ባስቀመጠው መሠረት በአልባሳትና ጨርቃ ጨርቅ፣ በህክምና መገልገያዎችና የኮንስትራክሽን ግብዓቶች ላይ የሚያተኩሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል። እነዚህ ዘርፎች በአነስተኛ ካፒታል የሚንቀሳቀሱ ሲሆን ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚያስችሉም ናቸው። በተጨማሪም ፓርኮቹ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችን ከማበረታታት ባሻገር የውጭ ባለሀብቶችን በስፋት ለመሳብ የሚያስችሉ እንደሚሆኑም ጠቁመዋል።

    እንደ አቶ ሽፈራው ገለፃ፤ ፋብሪካዎቹ በሙሉ አቅማቸው ወደ ሥራ ሲገቡ በውጭ ምንዛሬ የሚገቡትን ምርቶች የሚተኩና ለውጭ ገበያ በማቅረብ የውጭ ምንዛሬ የሚያሳድጉ ይሆናሉ። በዚህ ረገድ የቂሊንጦ ኢንዱስትሪያል ፓርክ በመድኃኒት ምርት፣ የድሬዳዋና የአዳማ ደግሞ በኮንስትራክሽን ማቴርያልና ከውጭ የሚገቡ ኬሚካሎችን በአገር ውስጥ ለመተካት የተያዙ ሲሆን፤ በአልባሳትና ጨርቃ ጨርቅ ዘርፍ የሚሰማሩት የወጪ ንግድ ላይ የሚያተኩሩ እንደሆኑም ገልፀዋል።

    በ2006 ዓ.ም. የተቋቋመው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን (IDPC) ሀገሪቱ ውስጥ በመንግስት ውጪ የሚገነቡትናና ወደ ሥራ የገቡትን የኢንዱስትሪ ፓርኮች በበላይነት ይቆጣጠራል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬሥ ድርጅት

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች

    Semonegna
    Keymaster

    በመቀሌ ከተማ በ147 ሚሊዮን ብር ካፒታል ሙሉ ብርሃን ኢንዱስቱሪና ንግድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ያቋቋመው ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ምሶሶ ማምረቻ ፋብሪካ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ፈጥሯል።

    መቀሌ (ኢዜአ) – በ147 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተቋቋመው ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ገመድ ተሸካሚ የኮንክሪት ምሶሶ ማምረቻ ፋብሪካ ምርት ማከፋፈል መጀመሩን አስታወቀ።

    “ሙሉ ብርሃን ኢንዱስቱሪና ንግድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር” በሚል የተቋቋመው ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ምሶሶ ማምረቻ ፋብሪካ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ፈጥሯል።

    የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ አቶ እሥራኤል ብርሃኑ ለኢዜአ እንደገለጹት ፋብሪካው በአገር አቀፍ ደራጃ ያለውን የኮንክሪት ምሶሶ ችግር ለመፍታት ታሳቢ ተደርጎ የተቋቋመ ነው።

    ፋብሪካው በአሁኑ ወቅት በቀን እስከ 90 የሚደርስ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ተሸካሚ ምሶሶዎችን በማምረት ላይ ሲሆን በሙሉ አቅሙ ሥራ ሲጀምር በቀን እስከ 300 የተለያዩ ደረጃ ያላቸው ምሶሶዎችን የማምረት አቅም እንደሚኖረው ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።

    ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመነጋገር ፋብሪካው ምርቶቹን ለትግራይአማራአፋር ክልሎች ማከፋፈል መጀመሩን አቶ እሥራኤል አስታውቀዋል።

    ፋብሪካው ከአገር ውስጥ ስሚንቶ፣ አሸዋና ጠጠር የሚጠቀም ሲሆን ለምሶሶው መሥሪያ የሚውሉ ብረቶችን ከውጭ በማስገባት ለአገልግሎት ያውላል።

    ፋብሪካው በሚያመርተው ምርት መንግስት በከተማና በገጠር የኤሌክትሪክ ሽፋን ለማዳረስ እያከናወነ ላለው ሥራ አጋዥ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።

    የክልሉ መንግስት በቦታ አቅርቦትና ብድር በማመቻቸት እገዛ እንዳደረገላቸው የገለጹት አቶ እሥራኤል ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ማምረት እንዲችል ከውጭ ለሚመጡ ጥሬ ዕቃዎች መግዣ የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት እንዲመቻችላቸው ጠይቀዋል።

    በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የትግራይ ቅርንጫፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ገብረመድህን የኮንክሪት ምሶሶ ማምረቻ ፋብሪካው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ምርቶች ማምረት መጀመሩን ተናግረዋል።

    የኮንክሪት ምሶሶ ማምረቻ ፋብሪካው በመቀሌ ማምረት መጀመሩ ከአሁን ቀደም ከአዲስ አበባ ለማጓጓዝ ለትራንስፖርት ይወጣ የነበረውን ወጪ ይቀንሳል ብለዋል።

    ከፍትኛ የኤሌክትሪክ ምሶሶዎች ለ20 ዓመታት ዋስትና ያላቸው መሆኑን የገለጹት ሥራ አስፈፃሚው ካሁን በፊት ለአገልግሎት ይውሉ የነበሩ የባህርዛፍ ምሶሶዎች በጉዳት ምክንያት ያደርሱ የነበሩትን አደጋና የኤሌክትሪክ መቆራረጥ የሚቀንስ ነው።

    የትግራይ ክልል ኢንቨስትመንት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሃፍቶም ፋንታሁን እንደገለጹት የምሶሶ ማምረቻ ፋብሪካው በመቀሌ ከተማ ለተለያዩ የኢንቨስትመንት ሥራዎች ቦታ ከተሰጣቸው ባለሀብቶች መካከል በፍጥነት ወደ ማምረት ሥራ መሸጋገር መቻሉ በአርያነቱ እንዲቀመጥ የሚያደርገው ነው።

    የትግራይ ክልል የተረጋጋ ሰላም ያለው በመሆኑ በርካታ የውጭና የአገር ውስጥ ባለሀብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት ሥራዎች እየተሳተፉ መሆናቸውን የጽህፈት ቤት ኃላፊው ገልጸዋል።

    በመካኒካል ምህንድስና የተመረቀው ወጣት አማኑኤል ሀይሉ በፋብሪካው በመቀጠር በወር 6ሺህ ብር የወር ደሞዝ እየተከፈለው ይሠራል። በፋብሪካው የሥራ እድል በማግኘቱ ደስተኛ መሆኑን የሚናገረው ወጣት አማኑኤል ገቢ ማግኘት መጀመሩ ከቤተሰብ ጥገኝነት ወጥቶ የራሱን ቤተሰብ ለመመስረት መቻሉን ገልጿል።

    ወጣት ዙፋን ኪዳኑ በበኩሏ “ማኅበሩ በዘርፉ ኢንቨስት በማድረጉ የአካባቢውን ወጣቶች የሥራ አድል ተጠቃሚ አድርጎናል” ብላለች።

    በትግራይ ክልል በ2010 ዓ.ም 24 ቢልዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 1ሺህ 328 ባለሀብቶች በሥራ እንዳሉ ከክልሉ ኢንቨስትመንት ጽህፈት ቤት የተገኘ መረጃ ያመልክታል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    የኤሌክትሪክ ምሶሶ

    Semonegna
    Keymaster

    የአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (በተለምዶው አማኑኤል ሆስፒታል) ኢትዮጵያ ውስጥ የአዕምሮ ህክምና የሚሰጥ ትልቁ ሆስፒታል ሲሆን፥ የተቋቋመውም በጣልያኖች እ.ኤ.አ በ1937 ዓ.ም አካባቢ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ። 

    አዲስ አበባ – በየዓመቱ እ.ኤ.አ ጥቅምት 10 ቀን የሚከበረውን የዓለም የአዕምሮ ጤና ቀን የአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በአገራችን ለ26ኛ ጊዜ “ወጣቶች እና የአዕምሮ ጤና በተለዋዋጭ ዓለም ውስጥ” በሚል መሪ ቃል የተለያዩ ምሁራን፣ የህክምና ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም የሆስፒታሉ ሠራተኞች በተገኙበት መስከረም 30 ቀን 2011 ዓ.ም በአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ውስጥ በድምቀት ተከበረ።

    የዓለም የአዕምሮ ጤና ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች የተከበረ ሲሆን ቀኑን አስመልክቶ የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ኢዳኦ ፈጆ በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ “ወጣቶች ብዙ ጊዜያቸውን የሚያሳልፉት የዓለም መረጃ መረብ ላይ በመጠመድ የሳይበር ወንጀልን በመለማመድ፤ ይህንኑ የመገናኛ መረብ በመጠቀም ህዝብን ወደ አልተፈለገ የእርስ በርስ ግጭቶች ውስጥ በማስገባት እና ከዚህም ሲያልፍ ከማኅበረሰቡ ባህልና ሞራል ውጭ የሆኑ ባዕዳን ቪዲዮዎችን በመመልከት ላይ ነው” ሲሉ አስገንዝበዋል።

    አያይዘውም ራሳቸውን የሚያጠፉና በአደንዛዥ እፅ ሱስ ስር እየወደቁ የሚገኙ የማኅበረሰብ ክፍሎች ቁጥር እያሻቀበ መምጣቱ እማኝ የሚያሻው ጉዳይ እንዳልሆነ በመጥቀስ በዚህ አዙሪት ውስጥ የሚያልፉት ደግሞ አብዛኛውን ወጣቶች መሆናቸው እጅግ አስደንጋጭ ነው ብለዋል። ዋና ሥራ አስኪያጁ እንደገለፁት አብዛኛው የአዕምሮ ህመሞች በወጣትነት የእድሜ ክልል ውስጥ የሚከሰቱ መሆናችውና ወጣቶቹ ደግሞ ስለ አዕምሮ ጤና ያላቸው ግንዛቤ እና አስተምህሮ አናሳ መሆኑ ይበልጥ ተጋላጭ ያደርጋቸዋል ሲሉ አክለዋል።

    በመጨረሻም “ይህ ቀን ወጣቶቻችን እንዴት ጠንካራ፣ ችግር ፈች፣ ከሱስ አዙሪት፣ ከእርስ በርስ ግጭቶች፣ ከእፅ ተጠቃሚነት እና ከልክ ያለፈ የኢንተርኔት ተጠቃሚነት (substance abuse and internet overload) ሰብረው መውጣት የሚችሉበትን መፍትሄ የምናፈላልግበትና የምንመክርበት ጊዜው አሁን ነው” በማለት ለታሳታፊዎቹ መልእክታቸውን በአንክሮ አስተላልፈዋል።

    በዝግጅቱ ላይ ቀኑን አስመልክቶ የአዕምሮ ጤና ምንነት፤ በአዕምሮ ጤና ላይ የማኅበረሰቡ የግንዛቤ ደረጃ ፤ በአገር አቀፍ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው የስርጭት ሁኔታ እንዲሁም ወጣቶች እና የአዕምሮ ጤና በአሁኑ ወቅት ምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ስፔሻሊስት በሆኑት በዶ/ር ሙሃመድ ንጉሴ እና በዶ/ር ዮናስ ላቀው ለተሳታፊዎቹ ገለፃ ቀርቧል። በመቀጠልም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በእንግድነት የተገኙት ፕሮፌሰር አታላይ ዓለም እንደተናገሩት በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ እየንተሰራፋ የመጣውን የአዕምሮ ጤና ችግር ለመቀነስና መፍትሄ ለማበጀት መንግስት፤ ባለድርሻ አካላት እና ሚዲያዎች የአንበሳውን ድርሻ ሊወስዱ እንደሚገባ ገልፀዋል።

    በመጨረሻም በተለያየ የአዕምሮ ህመም ተጠቂ ሆነው አማኑኤል ሆስፒታል ውስጥ ህክምና ተደርጎላቸው በመልካም ጤና ላይ የሚገኙ ሶስት ፈቃደኛ ግለሰቦች ሆስፒታሉን ከማመስገን ባለፈ በአዕምሮ ጤና ላይ የነበራቸውን ግንዛቤ እና ልምድ ለተሳታፊዎች ያካፈሉ ሲሆን በመልእክታቸውም የአዕምሮ ህመም እንደማንኛውም ህመም ውጤታማ ህክምና ያለው መሆኑን በማስተላለፍ በማኅበረሰቡ ዘንድ ስለ አዕምሮ ህመም ያለውን የተዛባ ግንዛቤ ለመቅረፍ መንግስት እና ህዝብ በጋራ ሊሰሩ እንዲሚገባ አስተላልፈዋል።

    ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ስር የሚተዳደረው የአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (በተለምዶው አማኑኤል ሆስፒታል) ኢትዮጵያ ውስጥ የአዕምሮ ህክምና የሚሰጥ ትልቁ ሆስፒታል ሲሆን፥ የተቋቋመውም በጣልያኖች እ.ኤ.አ በ1937 ዓ.ም አካባቢ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሆስፒታሉ ዘርፈ ብዙ ማስፋፋቶችን እያከናወነ ሲሆን፥ በየካቲት ወር 2009 ዓ.ም. በሆስፒታሉ ስር ሆኖ የየካ ኮተቤ ሆስፒታል የአዕምሮ ህክምና መስጠት ጀምሯል

    ምንጭ፦ የአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

    አማኑኤል ሆስፒታል

    Semonegna
    Keymaster

    የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአገር ውስጥ ሰላም እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን በሕዝቡ ፈቃድ ላይ የተመሠረተ አንድ የፖለቲካ ማኅበረሰብ በጋራ መገንባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራ የሰላም ሚኒስቴር እንዲቋቋም ተወስኗል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የሚኒስትሮች ምክር ቤት መስከረም 30 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የፌደራል መንግሥትን አስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በተዘጋጀ ረቀቅ አዋጅ ላይ መክሮ እንዲጸድቅ ለተወካዮች ምክር ቤት እንዲላክ ወስኗል።

    በውይይቱ ላይ የአስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን ያስፈለገበት ዋና ዋና ምክንያቶች እንደሚከተለው ቀርቧል፦

    1. የሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በቀሪው ጊዜ ያልተጠናቀቁ ሥራዎችን አካክሶ ለመፈጸም የሚያስችል አደረጃጀት በማስፈለጉ፤
    2. አገራችን የተያያዘችውን የለውጥ ጉዞ ለማስቀጠልና የማይቀለበስበት ደረጃ ላይ ለማድረስ የሚያስችል አደረጃጀትን መከተል በማስፈለጉ፤
    3. የአስፈጻሚ አካላትን ቁጥር ቀልጣፋ፣ ወጪ ቆጣቢና ውጤታማ ለማድረግ በማስፈለጉ፤
    4. ተደራራቢና ድግግሞሽ ሥልጣንና ተግባር የያዙ የመንግሥት ተቋማትን መቀነስ ወይም ለሥራቸው ቅርብ ከሆነ ሌላ የመንግሥት ተቋም ጋር እንዲዋሃዱ ማድረግ በማስፈለጉ፤

    እንደሆነ በስብሰባው ላይ ተብራርቷል።

    በምክር ቤቱም ውሳኔ የካቢኔ አባላት ቁጥር ከ28 ወደ 20 እንዲቀንስ ተደርጓል፤ ዋና ዋናዎቹ ለውጦችም:-

    • የንግድ ሚኒስቴር እና የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተዋህደው – የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እንዲሆን ፤
    • በየሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተዋህደው – የኢኖቬሽንና የቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንዲሆን ፤
    • የከተማ ልማት ሚኒስቴር እና የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ተዋህደው – የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር እንዲሆን
      ወስኗል።

    ሌሎች ተጠሪ ተቋማትም በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲዋሃዱ ውሳኔ የተሰጠባቸው ይገኛሉ።

    ሌላው ቁልፍ ውሳኔ በአገር ውስጥ ሰላም እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን በሕዝቡ ፈቃድ ላይ የተመሠረተ አንድ የፖለቲካ ማኅበረሰብ በጋራ መገንባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራ የሰላም ሚኒስቴር እንዲቋቋም ተወስኗል።

    ከትምህርት ሚንስቴር ሁሉንም ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን በመውሰድ እንዲሁም ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር ስር የሚገኙት ሁለቱን ዩኒቨርሲቲዎች በመጨመር “የከፍተኛ ትምህርትና የሳይንስ ሚንስቴር” ተብሎ እንዲደራጅ ተወስኗል።

    በተጨማሪም የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የገቢዎች ሚኒስቴር እና ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ የሆነ የጉምሩክ ኮሚሽን በመሆን ሁለት ተቋማት ሆነው እንዲደራጁ ተወስኗል።

    በአዲሱ አደረጃጀት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሚንስቴር ቀርቶ በቀጣይነት የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ለማስተዳደር መሠረታዊ ሚናቸው ንግድ የሆኑትን በመለየት የመንግስትን የባለቤትነት ሚና በተገቢው ሁኔታ የሚያስተዳደር “የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ” በገንዘብ ሚኒስቴር ሥር እንዲቋቋም ተወስኗል። ይህም የመንግሥት ቁልፍ ሚና የሆነው ቁጥጥር (regulation) በልማት ድርጅቶች ላይ ካለው የባለቤትነት ሚና ተለይቶ እንዲታይ እንደሚያግዝ ታምኖበታል።

    ረቂቅ አዋጁ ሌሎች መለስትኛ ለውጦችንም የያዘ ሲሆን፥ በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍጹም አረጋ የፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የሰላም ሚኒስቴር

Viewing 15 results - 466 through 480 (of 495 total)