Search Results for 'ኢትዮጵያዊ'

Home Forums Search Search Results for 'ኢትዮጵያዊ'

Viewing 15 results - 76 through 90 (of 124 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    ኢትዮጵያ ውስጥ የደረስንበትን የሞራል ድቀት፣ የዕውቀት ውድቀት እና የሰብዓዊነት ውርደት የሰሞኑ ሞት ፍንትው አድርጎ አሳይቷል
    (ሙሉዓለም ጌታቸው)

    የሞራል ድቀት

    • ገዳይ እና ሟች እኩል ጀግና የሚባልበት አገር ሆናለች ኢትዮጵያ። ዳቦ ስለራበኝ በዘላቂነት ዳቦ ለመብላት የዳቦ ቤቱን ባለቤት ገድዬ ዳቦውን ሁሉ ልውረስ የሚል ሌባ ወንጀለኛ ተብሎ ሀገር ካላወገዘው ወንጀለኛ ማን ሊባል ነው? ከእስር አስፈትተው ሹመት በሰጡ፣ 27 ዓመት ቃል ሳይተነፍሱ፥ ትላንት በተፈጠረ ዕድል ‘አማራ አማራ’ ብለው እንደ ጀግና ሲታዩ ዝም ባሏቸው በጥይት አረር ጨረሷቸው። እነዚህን የ21ኛው ዘመን አውሬዎችን በክብር መቅበር እና ጀግና ማለት ካላስነወረ ምን ሊያስነውር ነው? ‘የትም ፍጭው ዱቄቱን አምጭው፣’ ያነገብከው ዓላማ እንጂ ዓላማህን የምትፈጽምበት መንገድ ግድ አይሰጠኝም እንደሚል ሰው በዚህ ምድር ላይ አረመኔ የለም። ኦሳማ ቢን ላደን ያነገበውን ዓላማ ምናልባት ሁላችን የምንደግፈው እና በሞራልም ደረጃ ልክ የሆነ ነው። ያን ለመፈጸም የሄደበት መንገድ፣ የተጠቀመበት መሣሪያ ግን ርኩስ እና አረመኔ አስብሎታል። ሰብዓዊ የሆነ ሁሉ ሰው ይሄን ያምናል። ባዶ እጃቸውን የነበሩ፣ ለአገር ለወገን እረፍት አጥተው የሠሩ ግለሰቦችን አረመኔያዊ በሆነ መልኩ መግደል ሰይጣንነት ነው። የትኛውም ዓይነት ዓላማ ይሄን ግፍ ጽድቅ አያደርገውም። አሳምነው ጽጌን እንደ ጀግና የቆጠሩ ለእኔ ክርስቶስን እንደሰቀሉ መንጎች ናቸው። ክርስቶስን የሰቀሉ ግብዝ አይሁዶች እግዚአብሔርን እያገለገሉ ያሉ ይመስላቸው ነበር። ለዛ ግፋቸው መበተን እጣ ፈንታቸው ሆነ። ዛሬ ከእነዚህ ግፈኞች ጋር መተባበር የደም ዋጋን በራስ ላይ መሳብ ነው። ገዳይም ተገዳይም ጀግና ሊሆን አይችልም፤ ካልዞረብን በቀር።

    የዕውቀት እጥረት

    • የኢትዮጵያ መሪዎች በ21ኛው ክፈለ ዘመን ሀገርን የሚያክል ነገር በ“try and error” እየመሩ ነው። የእነሱን ነፍስ ብቻ ሳይሆን በፍጥነት አገሪቷን ገደል እየከተቱ ነው። 8 እና 9 ዓመት ከጨለማ በቀር ሌላ ነገር ያላዩን ግለሰቦች እና ከመንግስት ቢሮክራሲ ተለያይተው የነበሩ ሰዎችን በግዙፍ ስልጣን ላይ አሰቀመጡ። በሰለጠነው ዓለም ቢሆን ከፍተኛ የህክምና እርዳታ የሚደረግላቸውን ግለሰቦች በጡዘት ላይ ያለ አገርን እንዲመሩ ስልጣን አንበሻበሿቸው። ኤርትራ በርሀ ሊታገል የሄደን ወጣት ጉርጓድ ቆፍረው የሚቀብሩ ግለሰቦችን ሽግግር ምሩ ብለው ስልጣን ሰጡ። የቀደመው መንግስት ካጠፋው ይልቅ ይሄን ጥፋት ልናርም እየሄድንበት ያለው መንገድ የበለጠ ጥፋት እየከሰተ ነው።
    • ዲሞክራሲ ባህል ነው። ይሄ ባህል ፈጽሞ ባልገባው ማኅበረሰብ ፊት ሰው ሆኖ መታየት የደካማነት መገለጫ ነው። መሪዎቻችን ሆይ ዲሞክራሲ ያለንን ነገር እንዲያሳጣን ሳይሆን ባለን ነገር ላይ እንዲጨምርልን ተደርጎ መተግበር ካልቻለ፥ ዲሞክራሲ ለእኛ የሞት የሽረት ጉዳይ አይደለም። እባካችሁ በዲሞክራሲ ሳይሆን በዕውቀት ይሄን ሕዝብ ምሩት።

    የሰብዓዊነት ውርደት

    • ዘረኞች ስለሰው አንዳች ክብር እንደሌላቸው ድጋሚ ያየንበት ወቅት ነው። ጄነራል ሰዓረ መኮንን ድንቅ ኢትዮጵያዊ ነው። የሞተው ለኢትዮጵያዊነት በመቆሙ ነው። እንደነ አሳምነው ባለማበዱ ነው። እንደነሱ በዘር ልክፍት ገምቶ ዙሪያውን በራሱ ወገን እና ዘሮቼ በሚላቸው ሰዎች ተከቦ ቢሆን ኖር ዛሬ የተከሰተው ባልደረሰበት ነበር። አንዳንዶች ግን ዛሬም በሱ ሞት ፖለቲካ በመሥራት የእሱን ድንቅ ሰብዓዊነት ሊያራክሱ ይሞክራሉ። ምናለ ሞቱን እንኳ ቢያከብሩለት? ምናለ ለጥቂት ጊዜ እንኳ የሞተለትን ኢትዮጵያዊነት እና ሰብዓዊነት ከፍ ቢያደርጉ?
    • አንድ ቀን መንገድ ላይ የፈሰሰውን የአማራ የኔቢጤ እና መስኪን ለመርዳት፣ በየጎዳናው የወደቀውን የአማራን ተወላጅ ረሃብ ለመቅረፍ ገንዘብ አወጥቶ የማያቅ ሁላ ‘አማራ አማራ’ እያለ በውንድማማቾች መካከል ጥላቻን እየዘራ ያለ፥ ለሞታቸው ከቶ ደንታ የሌለው፣ በምዕራብ አገራት ሸሽቶ ተሰዶ እነሱ የከፈሉትን መስዋዕትነት በጣቱ ለመንካት አቅም የሌለው ሰው ‘ዘሬ!’ ሲል መስማት እጅግ ያማል። የግብዞች መዓት ኢትዮጵያን እያወካት ነው።

    ሙሉዓለም ጌታቸው

    የሞራል ድቀት፣ የዕውቀት ውድቀት እና የሰብዓዊነት ውርደት የሰሞኑ ሞት ፍንትው አድርጎ አሳይቷል


     

    Semonegna
    Keymaster

    ማለቂያ የሌላቸው ብዙ ብዙ የውሽት ትርክቶች ሰፊውን የአማራ ሕዝብ ጥቅምም ሆነ ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ለማስቀጠል ፈጽሞ የማይበጅ፣ እንዲያውም በአማራው ክልልም ሆነ በበርካታ አካባቢዎች በጎጥና በአካባቢም ጭምር ወርዶ የእርስ በእርስ ግጭቶች ሊወልድ የሚችል አደጋ ያዘለ ሁኔታ እያደገ መሆኑን የሰሞኑ ክስተት ያመላክታል።

    ኢትዮጵያ ሀገራችንን ከጥፋትና ከእልቂት ለማዳን ቆም ብለን በሰከነ ሁኔታ ማሰብና መራመድ እጅግ አስፈላጊና ወሳኝ ጊዜ ላይ እንገኛለን።
    (ነአምን ዘለቀ)

    የአማራ መሰረት ያላችሁ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ፣ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ሁሉ፥

    ዛሬ ከፊታችን ያፈጠጠው መሰረታዊ ጥያቄ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን እንደግፍ ወይንም አንደግፍ የሚለው አይደለም። የዛሬው ማዕከላዊ ጥያቄ፣ የዛሬው ዋና ጥያቄ ‘ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ትቀጥል ወይንስ አትቀጥል’ የሚለው ነው። አብይ መጣ፣ ከበደ፣ ዋቅጅራ፣ ወይንም ግደይ፣ እቺ ታሪካዊት ሀገር፣ እቺ መከረኛ ሀገር፣ እትብታችን የተቀበረባት፣ የምንወዳት፣ ሌት ተቀን የምንጨነቅላት ኢትዮጵያ ሀገራችን፣ በተማሩ ልጆቹ በተደጋጋሚ የተከዳና የተበደለ፣ በድህነትና በችጋር የሚማቅቀው፣ ነገር ግን ጨዋና ኩሩ የሆነው እብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ አብሮነት እንዴት ይቀጥል ነው ዋናው፣ መሰረታዊው፣ ማዕከላዊው ጥያቄ፣ የዛሬው ጥያቄ፣ የአሁን ሰዓት ዋነኛ ጥያቄ ይሄው ነው።

    ሰሞኑን “ኣማራው ተጠቃ፣ ተበደለ፣ ተገፋ” በሚል ሽፋን፣ በአብይ አህመድ “የኦሮሞ/ የኦዴፓን የበላይነት” ለመጫን እየሠራ የሚገኝ የትሮጃን ፈረስ ተደርጎ በሰፊው የሚነዛው ጥላቻ፣ የሚረጨው ሰፊ መርዝና ቅስቀሳ ሰፊው የአማራ ሕዝብን ጥቅም (በአማራው ክልል ብቻ ሳይሆን በኦጋዴን፣ በሀረር፣ በባሌ፣ በአርሲ፣ በኢሉባቡር፣ በወለጋ፣ ወዘተ… በሌሎች አካባቢዎች የሚገኘውን ከ10 ሚሊዮን በላይ አማራኛ ተናጋሪ ማኅበረሰብ) የአማራውን ሕዝብ ደህንነትና ዋስትና ለማረጋገጥ ምን ያህል እንደሚጠቅም፡ ህልውናውንም እንደምን አርጎ ለማረጋገጥ እንደሚያገለግል ቆም ብሎ የታሰበበት አለመሆኑ ግልጽ ነው።

    በትናንሽና ፍጹም የማይናበቡ፣ የጋራ ራእይ፣ የጋራ ስልት (strategy) በሌላቸው በየጎጡ የተደራጁና አማራን እንወክላለን በሚሉ እንደ አሸን የፈሉ ቡድኖች የሚደረገው ይሄው በጣም የከረረ ጥላቻ፣ ማለቂያ የሌላቸው ብዙ ብዙ የውሽት ትርክቶች ሰፊውን የአማራ ሕዝብ ጥቅምም ሆነ ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ለማስቀጠል ፈጽሞ የማይበጅ፣ እንዲያውም በአማራው ክልልም ሆነ በበርካታ አካባቢዎች በጎጥና በአካባቢም ጭምር ወርዶ የእርስ በእርስ ግጭቶች ሊወልድ የሚችል አደጋ ያዘለ ሁኔታ እያደገ መሆኑን የሰሞኑ ክስተት ያመላክታል። ይህ ደግሞ የሶማሊያ፣ የሊቢያ፣ የሶሪያን እልቂትና መበታተን የሚደግም፣ የሚያስከነዳም የምድር ሲኦል እንደሚፈጥር በተረጋጋ አዕምሮ ልብ ያለው ሁሉ ልብ ሊል ይገባል።

    ይልቅዬ በዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ የአማራው ዘላቂ ጥቅም የሚጠበቅበት፣ የሁሉም ሕዝቦች አብሮነት የሚረጋገጥበት፣ የኢትዮጵያ እንድነት የምናስቀጥልበት ሁኔታዎችና መንገዶችን፣ ሰከን ብሎ ማሰብ፣ በስሜት ሳይሆን በስትሪቴጂያዊ አስተሳሰብ፣ በጥበብና በስልት፣ በጋራ፣ ሰጥቶ በመቀበል እንጂ፣ ሰሞኑን በሶሻል ሚዲያ እንደሚራገበው አማራውን እንወክላለን የሚሉ በልዩ ልዩ ቡድኖች የተደራጁም ያልተደራጁም አክራሪ ብሄርተኞች እጅግ በሚያጦዙት መንገድ ፈጽሞ ሊሆን እንደማይችል የሮኬት ሳይንስ አውቀት የማያስፈልገው ሃቅ ይመስለኛል።

    ሰደድ እሳቱ ሲጀመር እያንዳንዱ ቤት አንደሚያንኳኳ ቆም ብሎ ማሰብ፣ ከሌሎች ሀገሮች ውድመት፣ ውድቀትና፣ ምስቅልቅል መማር ሰዓቱ ከመድረሱ በፊት ቆም በሎ ማሰብ ብልህነት፣ አስተውሎትም ነው። ስለዚህ ሰላም፣ መረጋጋት፣ ማዕከላዊ መንግስት የተከፈተውን ምህዳር ተጠቅሞ በሰላማዊ፣ ሕጋዊ፣ ስልታዊና ስትራቴጅካዊ አካሄድ በሰላማዊና በተደራጀ መልክ የአማራውን ሕዝብ ጥቅም፣ ደኅንነት ለማሰጠበቅ መንቀሳቀስ እንጂ፥ የሰፈር የጦር አበጋዞች (በሶማሊያና በሊቢያ እንዳየነው “warlords”)፣ ከሕግና ከስርዓት ውጭ የራሳቸውን ፍላጎት በጉልበት ለመጫን የሚፈልጉ አፈንጋጮችን (በሶሪያ እንደተከሰተው “rogue military commanders”) በማጀገን የአማራውን ሕዝብ ተገፍቻለሁ፣ ተጠቅቻለሁ ብሎ እንዲነሳሳ ሰፊ ቅስቀሳ ማድረግ ታሪክ ይቅር የማይለው፣ የአማራውን ሕዝብንም ሆነ፣ የአማራው ማኅበረሰብ በደም፣ በሕይወቱ፣ በላቡ ገብሮ፣ ለግንባታዋ ብዙ የተዋደቀላት ትላቋና ታሪካዊቷ ኢትዮጵያን የማይበጅ፣ ወደ ጥፋት፣ ወደ እርስ በእርስ ጦርነት፣ አልፎም ወደ ውድመትና ወደ መበታተን ሊያደርሰን የሚችል ሂደት እየተመለከትን ነው።

    በዚህ ሁሉ ትርምስ ደግሞ ዛሬ የሚፈነጥዘው፣ ይህን ሰፊ ትርምስ (turmoil) ለራሱ በሚገባ እየተጠቀመ የሚገኘው፥ እንደ አንድ ሰው የቆመው፣ እስከ አፍንጫው የታጠቀውም ሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ሕወሃት) ብቻ ነው። ሌላው ተከፋፍሏል፣ በአብይ አህመድ ላይ በሚወርደው የጥላቻ ውርጅብኝም ሀገሪቷን እንደ ሙጫ አጣብቆ ደካማ ቢሆንም የያዘውን ስርዓተ መንግስት (state)፣ ማዕከላዊ መንግስቱንም ለማዳከም ብዙ የድንጋይ ናዳ አየወረደ ነው። በየዕለቱ በተደራጀም በአልተደራጀም መልኩ እየተደረገ የሚገኘው ይሄው ነው።

    ሕዝብን እርስ በእርስ ሊያባላ፣ ሊያጫርስ የሚችል፣ ምንም አማራጭ ሃሳብ፣ ራእይና፣ ድርጅትም ሆነ ስትራቴጂ ለማቅረብ የማይችሉ፣ ነገር ግን አማራውን እንወክላለን የሚሉ፣ እንዲሁም በአብይ አህመድ ላይ የግል ጥላቻና ጥርጣሬ ያላቸው በርካታ ግለሰቦችና ቡድኖች ጭምር ተሳታፊ የሆኑበት ይሄው በከፍተኛ ስሜት በማጦዝ፣ የተገፊነትን ስሜት በመቀስቀስ ላይ የተመሰረተ ሰፊ ዘመቻ ያነጣጠረውና እየሄደ ያለው በዚሁ ግብ ላይ ነው። የእነዚህ ቡድኖች ምንም መናበብም ሆነ፣ የጋራ አማራጭ፣ እንዲሁም ለሀገራችንና ለሕዝባችን አሻግሮ የሚያይ ራእይ ማቅረብ ያማይችሉ፣ እርስ በእርሳቸው እንኳን ተቀምጠው በአግባቡ በምክኒያታዊነት መነጋገርና መደማመጥ የማይችሉ፣ ግለሰቦች፣ ቡድኖችና ኃይሎች የሚገፋውና የሚረጨው መርዝ ሁሉንም (እነሱንም ጨምሮ) ወደ ፍጹማዊ ኪሳራ፣ የዜሮ ድምር ፓለቲካ (zero-sum game) የሚወስድ፣ ማንም ምንም ወደማያተርፍበት የሲኦል መንገድ አገራችንንና ሕዝባችንን እየገፋ መሆኑን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዛሬ ላይ በሚገባ መገንዘብ አስፈላጊ የሆነበት ወቅት ላይ የደረሰን ይመስለኛል። ነገ በጣም ይዘገያል የዘገየ (too little too late) ይሆናል።

    ከዚህ አሳፋሪና ለሀገራችን ህልውና ብሎም ለኢትዮጵያ 105 ሚሊዮን ሕዝብ አብሮነት፣ ለኢትዮጵያ አንድነት ቀጣይነት እጅግ አስጊ ሁኔታ በተፈጠረበት በአሁኑ ወቅት አሸናፊ የሚሆነው ማነው? ሁሉንስ ድልና ወርቅ አፋሽ የሚሆነው ማነው? ብቸኛ ተጠቃሚስ ይኖራል ወይ? በሰላም ደሴት በደስታና በፍሰሃ ሊኖር የሚችለውስ ማነው? ስለእውነት፡ ስለሀቅ ለመናገር ማንም እንደማይሆን፣ ማንም እንደማይተርፍ በእርግጠኝነት መተንበይ ይቻላል። ሁላችንም ተያይዘን ወደ እልቂት፣ ወደ ሁለንተናዊ ውድቀት፣ ወደ ሲኦል እያዘገምን ይመስለኛል።

    ስለዚህ ወግኖቼ፥ ቆም ብለን ማሰብ ብልህነት ነው። ነገን ማሰብ፣ በተረጋጋና በምክንያታዊነት ዛሬን በትዕግስትና በስልት መራመድ አሰፈላጊና ወሳኝም ናቸው። የአማራውንም ጥቅምና ደኅንነት፣ የሌላውን ኢትዮጵያዊ ማኅበረሰቦች/ብሄሮች፣ አብሮነት፣ የአማራውንም ሆነ የሌላውን እኩልነት፣ መብት፣ ደህንነት፣ ለማምጣት በጥንቃቄ፣ በሕግ አግባብ፣ በሰላማዊ መንገድ፣ አስቦ፣ በአስተውሎ መራመድ የነገን ውድመት፣ የሀገር መበታተን፣ የሕዝብንም እልቂት የሚከላከል ሁሉም ሕዝቦች በጋራ በሰላም፡ በዴሞክራሲ፣ በሕግ የበላይነት፡ በእኩልነት የሚኖሩባት ኢትዮጵያን የሚያረጋግጥልን ብቸኛ መንገድ መሆኑን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ፣ ሁሉም የአማራ መሰረት ያለው ኢትዮጵያዊ ሁሉ በውጭም በሀገር ውስጥም ሊያጤነው የሚገባ ይመስለኛል። የመጨረሻው ደወል እያቃጨለ መሆኑ እየተሰማኝ ነው። ኢትዮጵያ እንደ ሀገር፣ ሁሉም ሕዝቦች፣ ማኅበረስቦች፣ በእኩልነት፣ በፍትህ፣ በሕግ የበላይነት የሚኖርባት ኢትዮጵያን ሁሉም ኢትዮጵያዊ፣ የአማራ መሰረት ያለው ኢትዮጵያውያን ሁሉ በጥሞና አስበን፣ አስተውለን፣ አቅደን መንቀሳቀስና ሀገራችንን ከጥፋት የማዳኛው ወቅት አሁን ነው፣ ዛሬ ነው።

    እግዚአብሔር ሀገራችንና ሕዝባችንን ይጠብቅልን፤ ስላሙን ያውርድልን።
    ነአምን ዘለቀ

    የአማራ ሕዝብ


    Anonymous
    Inactive

    በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ላይ የተደረገውን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ የፌደራል መንግሥት አወገዘ
    —–

    በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ላይ የተደረገው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ የሀገሪቱን ሕገ መንግሥት የሚፃረር፣ የክልሉ ሕዝብና መንግሥት ለረጅም ጊዜ የታገሉለትን ሰላምና መረጋጋት ለመንጠቅ የተደራጀ በመሆኑ የፌደራል መንግሥት ሙሉ በሙሉ እንደሚያወግዘው የጠቅላይ ሚንስትር ፅህፈት ቤት አስታወቀ።

    የፌደራል መንግሥት የጸጥታ መዋቅር የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራውን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ሥር አውሎ በፈጸሙት አካላት ላይ ተገቢውን ርምጃ እንዲወስድ ትእዛዝ ተቀብሎ ተፈጻሚ በማድረግ ላይ ይገኛል። ይህ ጥቃት በመንግሥት መዋቅር ላይ ብቻ ሳይሆን በአማራ ሕዝብ ላይ የተቃጣ መሆኑን በመገንዘብ የክልሉ ሕዝብ አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅና ተረጋግቶ ሁኔታዎችን እንዲመለከት ጥሪ ቀርቧል።

    ይህን ሕገ ወጥ ሙከራ ክልሉ ብቻ ሳይሆን ማንኛውም ክልልና መላው ኢትዮጵያዊ ሊያወግዘው የሚገባ ሲሆን የፌደራል መንግሥት የታጠቁ ቡድኖችን ሕገ ወጥ እንቅስቃሴ የመቀልበስ፣ የመግታትና በቁጥጥር ሥር የማዋል ሙሉ ዐቅም ያለው መሆኑን ያረጋግጣል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን

    Anonymous
    Inactive

    ቄሮ ነጻ ያወጣው እስክንድር ነጋን ሳይሆን እድሜያቸውን ሙሉ የህወሃት ተላላኪና ማላገጫ ሆነው የኖሩትን አቶ አዲሱ አረጋን እና ሌሎች የኢህአዴግ (የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር) ካድሬዎችን ነው።

    አቶ አዲሱ አረጋን ነጻ ያወጣችው የእስክንድር ፌስታል
    ያሬድ ኃይለማርያም

    ከወያኔ ጋር የተደረገው የነጻነት ትግል የዛሬ ሦስት ዓመት የተጀመረ የመሰላቸው አንዳንድ የኦዴፖ (የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ) አመራሮች አልፎ አልፎ የሚሰጡት መግለጫ እጅግ አስተዛዛቢ እና አስነዋሪም ነው። ባላፊት ሃያ ሰባት ዓመታት ብዙዎች የህወሃት (ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ) የማፈኛ መሣሪያ እና አሽከር ካድሬ ሆነው የገዛ ሕዝባቸውን ሲያሰቃዩ፣ ሲገድሉ፣ ሲገርፉ እና ሲያሰድዱ እንዳልኖሩ፤ በብዙ ሚሊዮኖች ‘ጎመን በጤና’ ብለው የአፈና እንቆቋቸውን እየተጋቱ ሁሉንም ነገር እንዳላየ እና እንዳልሰማ መስለው ለሥርዓቱ ጉልበት እንዳልሆኑ፤ ዛሬ በለውጥ ማግስት ያንን የአፈና ሥርዓት ያለፍርሃት ሲታገሉ፣ ሲታሰሩ እና ሲገረፉ የቆዩ የእስክንድር ነጋ አይነት የነጻነት ታጋዮችን ሲያጣጥሉ፣ ሲያንኳስሱ፣ ሲያስፈራሩ እና ሊያሸማቅቁ ሲሞክሩ ማየት እጅግ ያማል።

    አቶ አዲሱ አረጋ፥ ያ’ኔ!

    እነ ቄሮ፣ ፋኖ፣ ዘርማ እና ሌሎችም የመንደር ነጻ አውጪ ቡድኖች ሳይፈጠሩ ወይም መኖራቸው ሳይታወቅ በፊት ከወያኔ ጋር የነበረውን የሃያ ሰባት ዓመት ትንቅንቅ እና እልህ አስጨራሽ ትግል ብቻቸውን የተጋፈጡት እስክንድርን ጨምሮ በጣት የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ የመብት አቀንቃኞች እና ተሟጋቾች፣ ጥቂት ምሁራን እና ጥቂት የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓሪቲ ድርጅቶች አመራር እና አባላት ናቸው። የዛሬዎቹ ሹማምንት የህወሃት ጥርስ እና ክርን ሆነው የገዛ ሕዝባቸውን ይገዘግዙ እንደነበር እንዲህ በአጭር ጊዜ መዘንጋታቸው የሚያስገርም ነው። ከህወሃት ጫና ተላቀው ዛሬ እንደልብዎ እንዲናገሩ ያደረገችዎት ነጻነት ከእነ እስክንድር ነጋ እና ሌሎች ለዜጎች መብት መስዋዕትነት የከፈሉ ኢትዮጵያዊያን በመከራ ጊዜ ከሸከፏት ፌስታል መመንጨቷን ያወቁ አልመሰለኝም።

    የእስክንድር እና የጃዋር ኢትዮጵያን ሳስባት

    ቄሮ ነጻ ያወጣው እስክንድር ነጋን ሳይሆን እድሜያቸውን ሙሉ የህወሃት ተላላኪና ማላገጫ ሆነው የኖሩትን አቶ አዲሱ አረጋን እና ሌሎች የኢህአዴግ (የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር) ካድሬዎችን ነው። እስክንድር ነጋ እና ሌሎቹ በግፍ ታስረው የነበሩ የመብት ታሟጋቾች እና የነጻነት አቀንቃኞች ነጻ የወጡት ራሳቸው በከፈሉት መስዋዕትነት ነው። ያጣጣሏት የእስክንድር ነጋ ፌስታል ለእርሶም ነጻ መውጣት ትልቅ ድርሻ አላት።

    የመብት ተሟጋቾችን፣ በክፉ ቀን ለሕዝብ ነጻነት ዋጋ የከፈሉ ጋዜጠኞችን፣ ሲታሰሩና ሲሰቃዩ የኖሩ የፖለቲካ መሪዎችን፣ ምሁራንን እና የአገር ባለውለተኛ የሆኑ ግለሰቦችን ባልተገራ የካድሬ አንደበት መዝለፍም ሆነ ክብራቸውን መንካት እና መብታቸውን ማፈን ለውጥ እንመራለን ከሚሉ አካላት አይጠበቅም።

    ያሬድ ኃይለማርያም

    አቶ አዲሱ አረጋን ነጻ ያወጣችው የእስክንድር ፌስታል


    #11158
    Anonymous
    Inactive

    አቶ አዲሱ አረጋ የዛሬ ሁለት ዓመት፥ ሕዝባዊ እንቢተኝነቱ እንዳይቀጥል “አይደገምም” በማለት ታሳሪዎችን በማስተማር¡¡ የተጀመረው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ኒዮሊበራሎች በአገራችን “የቀለም አብዮት” ለማስነሳት እንደሆነ፣ የተፈጠውን የመልካም አስተዳደር ችግር ለመፍታት ጥረት እየተደረገ እንደሆነ ነግረውን ነበር።

    አቶ አዲሱ አረጋ፥ ያ’ኔ!
    (ይድነቃቸው ከበደ)

    የህወሃት መራሹ የኢህአዴግ የአገዛዙ ሥርዓት በሕዝባዊ እንቢተኝነት የዛሬ ሦስት እና ሁለት ዓመት በሚናጥበት ወቅት፤ መስከረም ወር 2009 ዓ.ም. የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ ሕዝባዊ ትግሉን ለመቀልበስ፣ በአገዛዙ በኩል የመጨረሻ እና ትልቁ የተባለ አፋኝ አዋጅ ታውጆ ነበር።

    የአዋጁን መውጣት ተከትሎ፤ ቁጥሩ ቀላል የማይባል ዜጎች በተለያዩ ቦታዎች በኃይል በማስገደድ እስራት ተፈጽሟል። በአዋሽ አርባ፣ አዋሽ ሰባት፣ ብርሸለቆ፣ ጦላይ፣ ሰንከሌና ሌሎች ካምፖች ውስጥ ለ‹ተሃድሶ ስልጠና› በሚል ለመግለፅ የሚከብዱ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት በእነዚህ ካምፖች ውስጥ ተፈጽሟል። በተለይ ከአዲስ አበባ ተይዘን ወደ አዋሽ 7 ከገባን ታሳሪዎች በፊት አንድ ወር ቀድመው እዚሁ ካምፕ የገቡ ከኦሮሚያ ክልል የተያዙ ወጣቶች የደረሰባቸው በደል ለመግለጽ እጅግ በጣም የሚከብድ ሰቅጣጭ ነው።

    በማጎሪያ ካምፖች ውስጥ በሺዎች በማሰር ይፈጸም የነበረው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት፣ በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ተቋማት፣ በአገር ወዳደ ኢትዮጵያዊያን ዘንድ ትልቅ መነጋገሪያ ሆነ። ይህ ደግሞ በወቅቱ በአገዛዙ ሥርዓት ላይ ጫና በመፍጥር የተጀመረው ሕዝባዊ እንቢተኝነት ሌላ ተጨማሪ ጉልበት ሆነ።

    ከጥቂት ቀናት በኋላ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መኖር አለመኖሩን እናጣራለን ያሉ “በመንግስት” ፍቃድ ታጉረን የምንገኝበት ካምፕ እንዲመጡ ተደርጓል። እንዲያናግራቸው ከተመረጡ ታሳሪዎች ጋር እኛን ወክለው ያዩትን እና የደረሰባቸውን የመብት ጥሰት ተናግሯል። በወቅቱ የመንግስት ሚዲያዎች ዜና ሲያቀርብ መሠረታዊውን የመብት ጥሰት ወደ ጎን በመተው፣ በጥሩ ሆኔታ ላይ እንደምንገኝ እና ስልጠና እየተከታተልን እንደሆነ ይገልጹ ነበር።

    በዚያን ጊዜ አቶ አዲሱ አረጋ፥ ያ’ኔ በአዋሽ አርባ፣ አዋሽ ሰባት፣ ብርሸለቆ፣ ጦላይ፣ ሰንከሌና ሌሎች ካምፖች ውስጥ በመዘዋወር፤ ‘መንግስት’ ወጣቶችን አላሰረም ‹ተሃድሶ ስልጠና› እየሰጠ ነው¡¡ ለማስባል በሚደረገው ጥረት፣ መንግስታዊ ድራማ አስመስሎ ለመከወን የአንበሳውን ድርሻ በታታሪነት ከፈጸሙት መካከል አቶ አዲሱ አረጋ አንዱ ናቸው።

    በተለይ እኔ በነበርኩበት ካምፕ አዋሻ 7፤ “አይደገምም” ኢትዮጵያ ካስመዘገበችው ዕድገት አንፃር አሁን የገጠማት “ሁከትና ብጥብጥ” አይገባትም፤ የሚል እንድምታ ያለው፣ “እኛ ታሳሪዎች” ሁከትና ብጥብጥ ማቆምና ማስቆም እንዳለብን የሚያትት። ሌላኛው ደግሞ “የቀለም አብዮት” ኒዮሊበራሎች፣ ግብጽ እና ኤርትራ ኢትዮጵያ ውስጥ ብጥብጥ እና አለመረጋጋት ለመፍጠር ስለሚፈልጉ “እኛ ታሳሪዎች” ከዚህ “የቀለም አብዮት” እራሳችንን እንድንጠብቅ የሚያሳስብ “የስልጠና” አርዕስት ላይ አቶ አዲሱ አረጋ ስልጠና በመስጠት በእኛ ታሳሪዎች ላይ “እጅግ በጣም” ጎብዘውብን ነበር¡¡

    አቶ አዲሱ አረጋ፥ ያ’ኔ ማለትም የዛሬ ሁለት ዓመት፥ ሕዝባዊ እንቢተኝነቱ እንዳይቀጥል “አይደገምም” በማለት ታሳሪዎችን በማስተማር¡¡ የተጀመረው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ኒዮሊበራሎች በአገራችን “የቀለም አብዮት” ለማስነሳት እንጂ፣ መጪው ጊዜ የኢትዮጵያ ሕዳሴ መሆኑ፣ ኢትዮጵያ ቁጥር አንድ ጠላቷ ድህነት እንደሆነ እና በወቅቱ የተፈጠው የመልካም አስተዳደር ችግር ለመፍታት ጥረት እየተደረገ እንደሆነ። አቶ አዲሱ ለመናገር እንጂ ለማዳመጥ ወይም ለመጠየቅ ቅንጣት ፍላጎታ ሳይኖራቸው እሳቸው እና “መንግስታቸው” ብቻ የሚፈልጉትን ነግረውን ያ’ኔ ሄደዋል።

    እኚህ ሰው አሁን ላይ “የለውጥ ኅይል” ከሚባሉት ውስጥ አንዱ ናቸው።

    ይድነቃቸው ከበደ

    አቶ አዲሱ አረጋ


    Semonegna
    Keymaster

    ሰናይ መልቲሚዲያ በበሳል ባለሙያዎችና በፕሬስ እድገት ውስጥ ከፍተኛ ሚና በተጫወቱ አንጋፋና ወጣት ጋዜጠኞች አስተባባሪነት የተቋቋመ የሕዝብ የሚዲያ ነው።

    ትላንት፣ ዛሬ እና ነገን እንደ ድልድይ የሚያስተሳስር ፣ የኢትዮጵያን ታሪክ፣ የዛሬን ተጨባጭ ሁኔታ ከግምት አስገብቶ፣ ነገ ላይ የተሻለች ኢትዮጵያን ለመፍጠር የሚረዱ አዳዲስ መርሀግብሮችን (ፕሮግራሞች) እና አቀራረቦችን ማስተዋወቅና አሁን በሥራ ላይ ያሉ የመገናኛ ብዙኃን ክፍቶችን መሙላት ዋንኛ ዓላማዉ በማድረግ፣ ሕዝብ በእኩልነት ሃሳቡን መግለጽ የሚቻልበት ሚዲያ ነው። ለዚህም “ሰናይ” ብለን ብዙኃኑ ባለው አቅሙ የድርሻው ባለቤት ሆኖ የእኔ የሚለውን ታላቅ የመልቲሚዲያ ተቋም ይፋ ለማድረግ እንወዳለን።

    ሰናይ መልቲሚዲያ የሕዝብ፣ ለሕዝብ፣ በሕዝብ የሆነ የመጀመሪያ ሚዲያ፤ እያንዳንዱ ዜጋ ያለብሔር ልዩነት፣ ያለጾታ፣ ያለእድሜና ክልል ገደብ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሰናይ ቴሌቪዥን (ሰናይ ቲቪ)፦

    • የተሻለ ፕሮግራም የሚሰራበት የራሱ ቲቪ አክስዮን ባለድርሻ ይሆናል ፤ምርትና አገልግሎት የሚያስተዋውቅበት ቲቪ አክስዮን ባለድርሻ ይሆናል፤የመረጃ፣ የቁም-ነገር እና የመዝናኛ ፍላጎትንና ጥምን የሚያረካ ቲቪ አክስዮን ባለድርሻ ይሆናል፤
    • የሰናይ ቲቪ የመጀመሪያው የሕዝብ ሚዲያ ኔትወርክ (network) ሲሆን በመጀመሪያ በቴሌቭዥን ሳተላይት ስርጭት ጀምሮ በመቀጠል ወደ ሬድዮ፣ ድረ-ገፅ እና በሶሻል ሚዲያ (social media) የሚያካትት ይሆናል፤
    • በሰናይ ቲቪ እያንዳንዱ ዜጋ ካለበት ቦታ የኔ በሚለው መልኩ በቀጥታ እንዲሳተፍና እቅድ ውስጥ መካተት የሚችልበትን ሁኔታ ይፈጥራል፤ እውነተኛና ነፃ አማራጭ ሚዲያ ይሆናል። ድምፅ አልባ ለሆነውም ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሃሳቡን በነፃነት የሚገልጽበት መንገድ ይከፈታል፤ የተለያዩ አመለካከቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት ጭምር ይሆናል።

    ሰናይ መልቲሚዲያ የተመሰረተው እየታሰሩ፣ እየተፈቱ ለሕዝብ መሰዋዕትነት ሲከፍሉ በቆዩ ነባር የነፃው ፕሬስ ጋዜጠኞች አስተባባሪነት፤ ብዙኃኑ ሕዝብ ሊገዛው በሚያስችል መልኩ ሰላሳ አምስት ሺህ (35,000) አክስዮኖችን በማቅርብ ሲሆን፤ እያንዳንዳቸው አንድ ሺህ ብር ዋጋ ያላቸው በአጠቃላይ የሰላሳ አምስት ሚሊዮን ብር ዕጣ ለሽያጭ አቅርበዋል። በዚህም መሰረት የአንድ አክስዮን ዋጋ 1,000.00 (አንድ ሺህ) ብር ሲሆን፤ ዝቅተኛውና አንድ ሰው ሊገዛ የሚችለው የአክስዮን መጠን 5,000.00 ብር (አምስት ሺህ ብር) ዋጋ ያላቸው አምስት ዕጣዎች ሲሆን፤ አንድ ሰው ሊገዛ የሚችለው ከፍተኛው የአክስዮን ብር መጠን 2,800,000.00 ( ሁለት ሚሊየን ስምንት መቶ ሺህ ብር) ዋጋ ያላቸው 2,800 ( ሁለት ሺህ ስምንት መቶ) የአክስዮን ዕጣዎች ናቸው። ይህ ማለት፤ ማንም ወገን ከስምንት ከመቶ በላይ አክስዮን አንዳይገዛ ገደብ አለበት። ሰናይ መልቲሚዲያ በአንድ ወገን ቁጥጥር ስር እንዳይወድቅ የሚደረግበት ማዕቀፍ ተበጅቷል።

    ሰናይ ቲቪ የማንኛውንም የፖለቲካ ወገንተኝነትን የማያስተናግድ፣ የግለሰቦች የፖለቲካ እምነት የማያንጸባርቅ፣ ፍጹም ገለልተኛ ሚዲያ ነው። በመሆኑም፤ ማንኛውም ሰው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች እና የሃይማኖት ተቋማት በስተቀር፣ የአክስዮን ባለድርሻ መሆን ይችላል። ለበለጠ መረጃ የፕሮጀክት አማካሪውን “ጌት አማካሪዎች” (GET Business & Investment Consultants) የንግድና ኢንቨስትመንት ማማከር፣ ድርጀቱን በግንባር በመቅረብ ወይም በስልክ-ቁጥር +251 (011) 8 12 12 33/34 በመደወል መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ።

    ምንጭ፦ ጌት አማካሪዎች/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ሰናይ መልቲሚዲያ


    Semonegna
    Keymaster

    በአሁኑ ጊዜ የግዕዝ ቋንቋን ትምህርት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከሚሰጥባቸው መካከል መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣ ደሴ ዩኒቨርሲቲ፣ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ አክሱም ዩኒቨርሲቲ እና ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የየኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢ.ፌ.ዲ.ሪ.) ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከብሔራዊ ቤተ መፃሕፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ፣ ከመቐለ ዩኒቨርሲቲ ቅዱስ ያሬድ ጥንታዊ ብራና ጽሑፎች ጥናትና ምርምር ማዕከል፣ የትግራይ ክልላዊ መንግስት ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር ከሰኔ 1-2 ቀን 2011 ዓ.ም. ድረስ “ግዕዝ እና ሥነ-ፈውስ” በሚል መሪ ቃል በመቐለ ከተማ ለሚካሄደው 5ኛውን የግዕዝ ጉባኤ ቀንን አስመልክቶ መረጃውን አስቀድሞ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ጋዜጣዊ መግለጫ በሚኒስቴሩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ግንቦት 26 ቀን 20011 ዓ.ም. ተሰጥቷል።

    ጋዜጣዊ መግለጫውን በጥምረት የሰጡት የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የቋንቋና የባህል እሴቶች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዓለማየሁ ጌታቸው፣ የብሔራዊ ቤተ መፃሕፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ይኩኖአምላክ መዝገቡ፣ ከመቐለ ዩኒቨርሲቲ ቅዱስ ያሬድ ጥንታዊ ብራና ጽሑፎች ጥናትና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሐጎስ አብርሃ ናቸው።

    እንደኃላፊዎቹ መግለጫ፥ በግዕዝ ቋንቋ ውስጥ ያሉ ሀገር በቀል ዕውቀቶች በርካታ በመሆናቸው ልንማርበት፣ ልንጠቀምበትና ልትውልድ በማሸጋገር ወደ ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ማምራት ይቻላል። በመሪ ቃሉ “ግዕዝ እና ሥነ-ፈውስ” ስንል እንደየባህሉ ሥነ-ልቦናን፣ ፀሎትን፣ ሥነ-ቃልን ለማወቅና መዳንን የሚያበረታታታ ሀገር በቀል ዕውቀት መሆኑንማወቅ ስላለብን፣ ብሎም ስለግዕዝ ያለንን ግንዛቤ ለማስፋት ነው ሲሉ ገልጸዋል።

    እንዲሁም በሀገራችን በርካታ ጥንታዊ የጽሑፍ ሀብቶቻችን የምናገኝበት በግዕዝ ቋንቋ የተፃፉ በመሆኑ፣ ጥንታዊ የስልጣኔ መገለጫ ሆኖ የሚያገለግል ነው። በአሁኑ ጊዜ የግዕዝ ቋንቋን ትምህርት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከሚሰጥባቸው መካከል መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣ ደሴ ዩኒቨርሲቲ፣ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ አክሱም ዩኒቨርሲቲ እና ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው። በሀገራችን በግዕዝ ቋንቋ በተሠሩ ሥራዎች ላይ እስካሁን የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት 750,000 በብራና ላይ የተፃፉ መጽሕፍት መኖሩ ታውቋል።

    ምንጭ፦ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    መቐለ ዩኒቨርሲቲ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ከፍተኛ አመራሮች አሜሪካ ውስጥ በካሊፎርንያ ግዛት ሎስ አንጀለስ ከተማ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ጋር አዲስ በተቋቋመው ፓርቲ አጠቃላይ ሁኔታና የሀገራችን ኢትዮጵያን (የፖለቲካ) ነባራዊ ሁኔታን በተመለከተ ተወያዩ።

    የኢዜማ መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የሕዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ናትናኤል ፈለቀ በሰሜን አሜሪካ በሚገኙ ሦስት ከተሞች ከሚያደርጉት ውይይቶች የመጀመሪያው በሆነው የሎስ አንጀለስ ውይይት፣ የፓርቲው አመሠራረት፣ ለመሥራት የታቀዱ ሥራዎች እና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በፓርቲው እና በአጠቃላይ ሀገሪቷ ውስጥ እንዲገነባ የሚፈለገው የተረጋጋ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንዴት ማገዝ እንደሚችሉ ውይይት ተደርጓል። በቪዛ መዘግየት ምክንያት ለስብሰባው መድረስ ያልቻሉት የኢዜማ ምክትል መሪ አቶ አንዱዓለም አራጌ የመክፈቻ የቪዲዮ መልዕክት አስተላልፈዋል።

    ኢዜማ ባደረገው በዚህ ውይይት፥ የሀገራችንን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እና የተረጋጋ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመፍጠር እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችም የውይይቱ አካል ነበሩ። ኢትዮጵያ ውስጥ የመጣውን ለውጥ “ሁለንተናዊ መሻሻል” ተብሎ የሚፈረጅ (reform) እንጂ አብዮት (revolution) አለመሆኑን መረዳት ያስፈልጋል ሲሉ መልዕክት ያስተላለፉት የኢዜማ መሪ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)፣ ለውጡ ያልገባቸው (የሚያስጨንቃቸው) የመንግሥት መዋቅር ውስጥ ያሉ ሰዎች የሚፈጥሩት እንቅፋት፣ በየክልሉ ያሉ የታጠቁ ኃይሎች እና ብዛት ያለው ሥራ ፈላጊ ወጣቶች ቁጥር የለውጡ ከፍተኛ ተግዳሮቶች እንደሆኑ እና በየደረጃው መፍትሄ መስጠት እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።

    በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በኢዜማ እንቅስቃሴዎች ላይ ቀጥተኛ ተሳታፊ መሆን የሚችሉበት አደረጃጀት (ቻፕተሮች) በሁሉም የዓለማችን አካባቢዎች የሚዋቀሩ ሲሆን በሀገራችን ዜግነትን መሠረት ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት እንዲፈጠር እና ማኅበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን የሚፈልጉ በውጭ ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ በነዚህ መዋቅሮች ውስጥ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ ተላልፏል።

    ከፓርቲው ዜና ጋር በተያያዘ፥ የኢዜማ ግብረ-ኃይል በአምስት አቅጣጫ ተንቀሳቅሷል። ከአዲስ አበባ በመነሳት በአምስት አቅጣጫ መዳረሻውን ያደረገ ግብረ-ኃይል ግንቦት 24 ቀን 2011 ዓ.ም. እንቅስቃሴ ጀምሯል።

    መነሻውን ከመስቀል አደባባይ ያደረገው ግብረ-ኃይል የኢዜማ ምክትል የፓርቲ መሪ አቶ አንዱዓለም አራጌና የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ አሰፋን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች በተገኙበት መሸኛ ተደርጎለታል።

    ግንቦት 24 ቀንጉዞውን የጀመረው ግብረ ኃይል፣ በኢዜማ ለተደራጁ ለ216 የምርጫ ወረዳዎች ጊዚያዊ የእውቅና ደብዳቤ፣ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ደረሰኝ፣ የአባላት ፎርም እና የድርጅት ጉዳይ መመሪያዎቹን ተደራሽ ለማድረግ በአምስት አቅጣጫዎች ጉዞ ጀምሯል። በየመጀመሪያው ዙር ጉዞ ተደራሽ የሚደረግባቸው፡-
    1. ከአዲስ አበባ – ደብረ ብርሃን፣ ደሴ፣ ወልዲያ መዳረሻውን ሰቆጣ
    2. ከአዲስ አበባ – ፍቼ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ፍኖተ ሰላም፣ ባህር ዳር አድርጎ መዳረሻውን ጎንደር
    3. ከአዲስ አበባ – ሻሸመኔ፣ ሀዋሳ፣ ጌድኦ፣ አለታ፣ መዳረሻውን አዶላ (ክብረ መንግስት)
    4. ከአዲስ አበባ – አምቦ፣ ነቀምት፣ ጊምቢ፣ ጅማ፣ መዳረሻውን ቤንች ማጂ
    5. ከአዲስ አበባ – አዳማ፣ አሰላ፣ ወላይታ፣ ሀዲያ፣ ዳውሮ፣ ወልቂጤ፣ መዳረሻውን ጉራጌ በማድረግ ሲሆን በቀጣይም በቅርብ ጊዜ ውስጥ ሌሎች አዳዲስ ቦታዎችንና ከተማዎችን ተደራሽ የሚያደርግ ጉዞ እንደሚኖር ታውቋል።

    የሀገር መረጋጋትን ቀዳሚ ዓላማ አድርጎ የሚሠራው ኢዜማ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ አባላቱና ደጋፊዎቹ ይህንኑ ዓላማ ተፈፃሚ ለማድረግ እንዲሠሩ በሁሉም አቅጣጫ የሚጓዙት የግብረ ኃይሉ አባላት አፅዕንዎት ሰጥተው የሚያስገነዝቡ ይሆናል። በየአካባቢው የሚገኙ አባላትና ደጋፊዎች እንዲሁም የየአካባቢው ሕዝብ ለግብረ -ኃይሉ አባላት አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉላቸው ጥሪ ተላልፏል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ኢዜማ


    Semonegna
    Keymaster

    ከኢሳት (ESAT TV) የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ

    ጉዳዩ፦የኢሳትን (ESAT TV) መዋቅርና አሠራር ማስተካከልን ይመለከታል

    ጊዜው ኢሳትን የመሰሉ የኢትዮጵያዊነትና የዲሞክራሲ ድምጾችን አገራችን ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ የምትፈልግበት ነው። ኢሳትም (ESAT TV) ለዚህ አገራዊ ጥሪ መልስ ለመስጠት በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጭ ተጠናክሮ ለመሥራት ቃል መግባቱን በድጋሚ ለማስታወስ እንፈልጋለን።

    የኢሳት ቦርድ (ESAT TV Executive Board) ባለፈው ኤፕሪል ወር (April 2019) ውስጥ ይህንን ጥሪ በወጉ ለመመለስ በስድስት አስፈላጊ የሆኑ ኢሳትን የማጠናከሪያና የማሻሻያ አቅጣጫዎች ከተቋሙ ሠራተኛና የድጋፍ ኮሚቴ ተወካዮች ጋር በመመካር መወሰን እንደሚጀመር አስታውቆ ነበር። በዚህ መሰረት ሜይ 28፣ 2019 (ግንቦት 20 ቀን 2011 ዓ.ም.) ቦርዱ ከመላው ዓለም አቀፍ የኢሳት ባልደረቦች ጋር በመሰብሰብ የመጀመሪያውን ውሳኔ ይፋ አድርጓል።

    ይህ ውሳኔ ያተኮረው ኢሳት ኢንተርናሽናልን በባጀት፣ በሰው ኃይል፣ በፕሮግራሞች ይዘትና አቅጣጫዎች እንዲሁም በአስተዳደር አቅም ከዘላቂነት ጋር እንዲጣጣም ማድረግን ይመለከታል። ውሳኔው እንደማንኛውም ተቋማዊ የመዋቅር የማስተካከያ እርምጃ ጊዜያዊ ችግሮችን ሊፈጥር ቢችልም በዘላቂነት ግን ኢሳትን (ESAT TV) በሁሉም ዘርፍ አቅሙንና ሕዝባዊነቱን በማጠናከር የተመሰረበትን መሰረታዊ ዓላማ እውን ማድረግ ነው።

    ይህንን መሰረተ ሃሳብ በደንብ ተገነዘቦ በሚሠራ የኢሳት አስተዳደርና ባለሙያዎች የተወሰነን ውሳኔ የፖለቲካ ፉክክር ጨዋታ ውስጥ እያስገቡ መተርጎም ትክክል አይሆንም። ይህ ውሳኔ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሰሞኑን እንደሚወራው በኢሳት ውስጥ ያሉ የጋዜጠኞች የሃሳብ ልዩነቶች ጋር የተያያዘ አይደለም። ኢሳት የፖለቲካ ፓርቲ አይደለም። በባለሙያዎቹ ውስጥ እንደማንኛችንም የህብረተሰብ አባላት የተለያየ የግል እምነትና የፓለቲካ አመለካከቶች እንደሚንጸባረቁ ግልጽ ነው። ሆኖም እንደ ሚዲያ ተቋም የኢሳት ሚና የመንግሥትን ወይም የማንንም አንድ ወገን ፍላጎትን መቃወም ወይም መደገፍ ሳይሆን ሙያዊ ብቃት ያለው አስተማማኝና የተጣራ መረጃ የሚያቀርብ የህዝብ ሚዲያ ሆና ማገልገል ነው።

    የኢሳት ግብ በነጻነት፣ በሙያዊ የጋዜጠኝነት ሥነ-ምግባር፣ እንዲሁም በሕዝባዊ ዓላማ ላይ ተመስርቶ የሚዲያ ምርቶችን በማምረት፡ በፓለቲካዊ፣ በኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና፣ ባህላዊ ርዕሰ ጉዳዮች እንዲሁም የተጣሩ መረጃዎች በማቅረብ ሕዝብን ማገለገል ነው። በተለይ አሁን ሀገራችን ባለችበት ሁኔታ ደግሞ የኢትዮጵያን ሕዝብ አንድነት ማበረታታት፣ የሀገሪቱም ችግሮችና ተግዳሮቶች በዲሞክራሲያዊ መንገድና በውይይት የመፍታትን ባህል እንዲስፋፋ መርዳት ነው።

    ይህንን መሰረተ ሃሳብ በደንብ ተገነዘቦ በሚሠራ የኢሳት አስተዳደርና ባለሙያዎች የተወሰነን ውሳኔ የፖለቲካ ፉክክር ጨዋታ ውስጥ እያስገቡ መተርጎም ትክክል አይሆንም። ዛሬ የተጀመረው የኢሳት ማጠናከሪያ በቅርቡም በቦርድ፣ በአስተዳደር፣ በኤዲቶሪያልና በአጠቃላይ የኢሳት አሠራር ላይ ይቀጥላል። ኢሳት በመጀመሪያ የሥራ ምዕራፉ ማለትም በሀገራችን ከ 27 ዓመታት በላይ የተሰራፋውን አፋኝና ዘረኛ ስርዓት በማስወገድ ሂደት ያበረከተውን አስተዋጽኦ በሚቀጥለውም የሀገርና የሕዝብ አንድነትና የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሥራ ምዕራፍ ውስጥም እንደሚቀጥል ጥርጥር የለንም። ለዚህም የኢሳት ቤተስቦችና የድጋፍ ኮሚቴዎች እንደወትሮው ኢሳት የህዝን ዓይንና ጆሮ ሆና እንዲቀጥል የበኩላችሁን እንድታደረጉ ትብብራችሁን በአክብሮት እንጠይቃለን።

    ጁን 1 ቀን፣ 2019 (ግንቦት 24 ቀን 2011 ዓ.ም.)፣ ዋሺንግተን ዲሲ
    የኢሳት (ESAT TV) ቦርድ ሥራ አስፈጻሚ
    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ኢሳት (ESAT TV)


    Semonegna
    Keymaster

    ፊቼ ጫምባላላ በዩኔስኮ ከማይዳሰሱ የዓለም ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ከተመዘገቡ ቅርሶቻችን ውስጥ አንዱ ነው። የፊቼ ጨምበላላ በዓል የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት በዓል መሆኑን የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ ገልጸዋል።

    ሀዋሳ (ሰሞነኛ) – የሲዳማ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው ፊቼ ጫምባላላ በሀዋሳ ከተማ በድምቀት ተከብሯል። በበዓሉ ላይ ከተለያዩ ወረዳዎች የመጡ የሲዳማ አባቶች የቄጣላ ሥነ-ስርአት አድርገዋል።

    በሀዋሳ ጉዱማሌ አደባባይ በልዩ ሁኔታ የተከበረው በዓል ላይ የሲዳማ ሴቶች በባህላዊ አለባበስ እና ባህላዊ የፀጉር አሰራር አሸብርቀው የበዓሉ ድምቀት ሆነዋል።

    በበዓሉ ላይ ከተለያዩ ክልሎች የተጋበዙ ልዑካንም የተገኙ ሲሆን፥ ከደቡብ ክልልም ከተለያዩ ብሄረሰቦች የተውጣጡ ልዑካን ታዳሚዎች ሁነው ነበር።

    የፊቼ ጫምባላላ በዓል በዩኔስኮ ከማይዳሰሱ የዓለም ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ከተመዘገቡ ቅርሶቻችን ውስጥ አንዱ ነው። የፊቼ ጨምበላላ በዓል የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት በዓል መሆኑን የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ ገልጸዋል።

    በዓሉ በጋራና በድምቀት እንዲከበር ዋጋ ከፍለው በዓሉን እዚህ ላደረሱት አባቶች ምስጋና አቅርበዋል – አቶ ሚሊዮን። አክለም በዓሉ በይቅርታና በፍቅር የምናከብረው በዓል በመሆኑ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በፍቅር እንዲያከብረውም ጥሪ አቅርበዋል።

    የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በበኩላቸው፥ ፊቼ ጫምበላላ የኛም ባህል በመሆኑ ለማድመቅ ሳይሆን ለማክበር ነው ወደ ሀዋሳ የመጣነው ሲሉ ገልጸዋል። ባህሉ ተጠብቆ የዓለም ቅርስ ሆኖ እንዲቆይ አባቶቻችን ታላቅ ሚና በመጫወታችሁ ምስጋና ይገባችሀል በማለትም ተናግረዋል።

    አቶ ሽመልስ መልዕክታቸውን ከማጠቃለላቸው በፊት የሲዳማና የኦሮሞ ህዝብ አብሮ ብዙ መስዋዕትነትን የከፈለና ድል ያስመዘገበ ህዝብ ነው ሲሉም ገልጸዋል – አቶ ሽመልስ። እኩልነትን፣ ነፃነትንና ወንድማችነትን በማጠንከርና በማሳደግ የተገኘውን ድል ለማስቀጠል መሥራት እንደሚገባም ገልጸዋል። ልዩነታችንን ጠብቀን አንድ በሚያደርጉን ነገሮች ላይ በመሥራት ለበለጠ ድል መትጋት ይጠበቅብናል ብለዋል። በዚህም የሁለቱም ወገኖች የሆኑት ኤጀቶና ቄሮዎች ተባብረው ለክልሎቻቸውም ሆነ ለኢትዮጵያ እድገት መሥራት እንደሚጠበቅባቸውም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

    የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሂሩት ካሳው በበኩላቸው፥ ባህሉ ከትውልድ ትውልድ ተጠብቆ እንዲተላለፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ተገቢውን ሥራ እንደሚሠራ ገልጸዋል። ከቀደምት አባቶቻችንና እናቶቻችን የወረስናቸውን እንደ ፍቼ ጫምበላላ ያሉ ባህሎቻችንን ጠብቀንና ተንከባክበን ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ ተናግረዋል።

    የፖለቲካ አክቲቪስትና የኦሮሚያ ሚድያ ኔትዎርክ (ኦ.ኤም.ኤን) ቴሌቭዥን ጣቢያ መሥራች የሆነው አቶ ጃዋር መሀመድ በበኩሉ፥ ፊቼ ጫምበላላ በዓልን ያለ አንዳች ችግር ማክበር መቻሉ እንደሚያስደስት ገልጿል። በዓሉ ቀደምት አባቶች በከፈሉት መስዋዕትነት እዚህ ደረጃ ላይ ደርሶ እየተከበረ ያለ ቅርስ መሆኑን ተናግሯል። በዓሉ እንዲህ እንዲከበር ኤጀቶና ቄሮዎች ለሰላም ያደረጉት ትግል ውጤት መሆኑንም ገልጿል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ፊቼ ጫምባላላ


    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያቀረበውን ይህን ከወለድ ነፃ የዳያስፖራ የቤት መግዣ የፋይናንስ አገልግሎት በውጭ የሚኖሩ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ሌሎች በዚህ አገልግሎት መጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ ሊጠቀሙበት ይችላሉ።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ኢትዮጵያ ውስጥ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለማድረግ የሚያስችል ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ይፋ አደረገ። አገልግሎቱ ሙስሊሙን ህብረተሰብ ጨምሮ ሌሎች የወለድ አገልግሎትን የማይፈልጉ ዳያስፖራዎችም እንዲጠቀሙበት የተዘጋጀ ነው።

    የባንኩ የጥራት ቁጥጥር ምክትል ፕሬዚዳንት ወይዘሮ እመቤት መለሰ አዲሱን ከወለድ ነፃ የዳያስፖራ ፋይናንስ አገልግሎት አስመልክተው በሰጡት አስተያየት “ለመኖሪያ ቤት መግዣ የሚውለው ከወለድ ነፃ የዳያስፖራ ፋይናንስ አገልግሎት ከዚህ ቀደም ከቀረቡትና ዳያስፖራውን ከሚመለከቱ የባንክ አገልግሎቶች በተለየ መንገድ ይተገበራል” ብለዋል።

    ዳያስፖራው ወዲዓ’ህ የቁጠባ ሒሳብን በመጠቀም ቢያንስ 20 በመቶ የሚሆነውን ገንዘብ በእንግሊዝ ፓውንድ፣ በአሜሪካን ዶላርና በዩሮ መቆጠብ ከቻለ፣ የፋይናንስ ጥያቄውን ለባንኩ በማቅረብ መስተናገድ እንደሚችል ወይዘሮ እመቤት ተናግረዋል።

    ግንባታው የተጠናቀቀና ጅምር ቤት ለመግዛት የሚውለው የፋይናንስ አገልግሎት በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የመኖሪያ ቤት ችግር እንቅፋት እንዳይሆንባቸው ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ታስቦ ለዳያስፖራው የተዘጋጀ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎት ነው። የፋይናንስ አገልግሎቱን መስፈርቶች ማሟላት የሚችሉ ዳያስፖራዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ወይም በሚኖሩበት አገር በሚገኝ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል ቀርበው የወዲዓ’ህ ቁጠባ ሒሳብ በመክፈት መቆጠብ የሚችሉ ሲሆን፣ ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ቅድመ ክፍያ በአንድ ጊዜ ወይም በተለያዩ ጊዜያት በመቆጠብ መክፈል ይችላሉ። ለቤት መግዣ የሚውለውን ፋይናንስ እስከ 20 ዓመት በሚደርስ የቆይታ ጊዜ ከፍለው መጨረስ እንዲችሉም ተመቻችቷል።

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያቀረበውን ይህን ከወለድ ነፃ የዳያስፖራ የቤት መግዣ የፋይናንስ አገልግሎት በውጭ የሚኖሩ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ሌሎች በዚህ አገልግሎት መጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ እንዲጠቀሙበት ወይዘሮ እመቤት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ከወለድ ነፃ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር በአገራችን በሁሉም አቅጣጫ የተጠናከረ የመዳረሻ ልማት፣ የቅርስ ጥገናና እንክብካቤ ሥራዎችን በተቀናጀ መልኩ ለማከናውን እንዲያስችል በሙያው የተሠማሩ ከመሀንዲሶች እና የሥነ-ሕንፃ ባለሙያዎች ጋር ግንቦት 6 ቀን 2011 ዓ.ም. አዲስ አበባ ውስጥ በጌት ፋም ሆቴል ምክክር ተካሄደ።

    በመክፈቻው ላይ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት ክብርት ዶ/ር ሂሩት ካሳው የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ሲሆኑ፣ በመክፈቻ ንግ ግራቸውም የመርሐ ግብሩን ዓላማ “በኢትዮጵያ ሥነ-ሕንፃ ዲዛይን ጥበብ ከጥንት አባቶቻችን ዘመን ጀምሮ የነበረን ብሎም ዓለምን እስከ ዛሬ ድረስ የሚያስደምሙ ሕንፃ ጥበቦች አሁንም አሉን። እንደሚታወቀው በዓለም የሥነ-ሕንፃ ጥበብ ታሪክ የባቢሎናዊያን፣ የግሪኮች፣ የሮማውያን፣ የባይዛንታይን፣ የመካከለኛ ዘመን፣ የዘመናዊው (modern) ሥነ-ሕንፃ ብለን ማየት የምንችል ይሆናል። በኢትዮጵያ ሥነ-ሕንፃ ታሪክ ቅድመ አክሱም (የዳዓማት)፣ የአክሱማውያን ስልጣኔ፣ የዛጉዌ ስርወመንግስት ሥልጣኔ፣ የሰሎሞኒክ፣ የጎንደሮች ዘመን ሥልጣኔን ማውሳት ይቻላል። አንድ ሥነ-ሕንፃ ሲታነፅ በዋናነት የዚያን ዘመን ማኅበራዊ አደረጃጀት እና የተደረሰበትን አጠቃላይ የዕድገት ደረጃ ከማሳየቱም በላይ በየዘመኑ ያሉ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሁኔታዎችን ፍንትው አድርጎ የማሳየት ጥበብ አለው” ብለዋል።

    ክብርት ሚኒስትሯ አክለውም “በሀገራችን የአርክቴክቱና የኢንጂነሩ የጥበብ አሻራዎች ለዚህ ላለንበት ዓለም እያበረክቱት ያለው ሙያዊ ድጋፍ ቀላል ግምት የሚሰጠው አለመሆኑንና በሀገር በቀል የሥነ-ሕንፃ ጥበባችን ዓለም ወደኛ እንዲመለከተን አስተዋጽኦቸው ከምንም በላይ የሚደነቅ ነው። አርክቴክቱና አንጂነሩ በሙያው የማኅበረሰቡን እምነት፣ ታሪክና ማንነት በሥነ-ሕንፃ ጥበብ ውስጥ በማኖር ማሳየት በመቻሉ ዘመን ተሸጋሪ አደርጎታል። ስለሆነም በዛሬው ዕለት የምናካሂደው ውይይት በመዳረሻ ልማት፣ በቅርስ ጥገናና እንክብካቤ እንዲሁም በኢትዮጵያ እየተገነቡ ያሉ ሕንፃዎች ኢትዮጵያዊ መገለጫነት የሌላቸው በመሆኑ እንዴት አብረን እንሥራ ብለን ስንነሳ በመጀመሪያ ከአርክቴክቶችና አንጂነሮች ጋር በመሆን የጋራ ቅርሶቻችንን የማወቅ፣ የመለየትና የማስተዋወቅ ሥራ፣ የቅርስ ጥገናና እንክብካቤ ሥራ በራስ ዕውቀት እንዲሆን በማድረግ በቅርስ ጥበቃ ኢትዮጵያዊ መልክ እንዲኖራቸው፣ የዕውቀት ሽግግርና ሕዝብ ሕህዝብ የማገናኘት ሥራ በአንድ ላይ ተሰባስበን የምንሠራበትና የጋራ አቅጣጫ የምንይዝበት ነው በማለት መድረኩን ክፍት አድርገዋል።

    SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest | Video | Forum

    በመቀጠል ሦስት ርዕሰ ጉዳዮች የመወያያ ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን፣ እነዚህም በአገራችንን ቅርሶች ነባራዊ ሁኔታ ዳሰሳዊ ጥናት በአቶ ኃይሉ ዘለቀ ከቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን፣ በዘመናዊ የቅርስ አመራርና አስተዳደር ወቅታዊ ቁመና በረ/ፕሮፌሰር ሀሰን ሰዒድ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በተጠናከረ የመዳረሻ ልማት በአቶ ቴዎድሮስ ደርበው ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የቱሪስት አገልግሎቶች ብቃት የማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ናቸው።

    ጥናታዊ ጽሑፎችን ያቀረቡ ባለሙያዎች ተንተን ባለመልኩ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የቅርስ አስተዳደር ሁኔታ ምን ይመስል እንደነበረ ከታሪካዊ ዳራው ጀምሮ የሀብቱ ጥበቃና እንክብካቤ የመንግስትና የሕዝብ ፍላጎት ላይ የተመሠረቱ መሆኑ አመላክተዋል። የሀብቱ ጥበቃና እንክብካቤ በግለሰብ፣ በማኅበረሰብ እና የባለሙያው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን በተያዘላቸው ጊዜ ቅደም ተከተል ገለፃ አድርገዋል።

    በውይይቱም እያንዳንዱ ባለሙያው በቅርስ ጥገናና እንክብካቤ ዙሪያ በዕውቀትም፣ በሀሳብም በጉልበትም መደግፍ እንዲችል በተደራጀ መልኩ አቅም እንዲፈጠርለት የተጠየቀ ሲሆን በመዳረሻ ልማት (በከተማ ግንባታ) እየታዩ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በውይይቱ የተሳተፉ መሀንዲሶች እና የሥነ-ሕንፃ ባለሙያዎች እንደአገር የሚሠሩ የሥነ-ሕንፃ ሥራዎችን የዲዛይን ውድድር ውስጥ መሳተፍ እንዲችሉ ዕውቅና በመስጠት አገራዊ ቅርጽ እንዲይዙ ማድረግ ወሳኝ መሆኑ፣ በመዳረሻ ልማት ዘርፍ የሚሠማሩ ዜጎች የኢትዮጵያዊ ማንነት መገለጫ ያላቸው ሕንፃዎች እንዲኖረን በሕንፃ ግንባታ መስክ ትኩረት የሚሰጥ አስገዳጅ ቅድመ ትኩረታዊ ስልት (strategy) እንደአገር ሊኖረን ይገባል።

    ምንጭ፦ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር


    Semonegna
    Keymaster

    በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በተካሄደው የሰላም ንቅናቄ ላይ ከተለያዩ ቦታዎች የመጡ እና በተለያዩ ሙያዎች ላይ የተሰማሩ የአገራችን ታዋቂ ሰዎች ስለ ሰላም እና በሰላም እጦት ምክንያት የሚከሰቱ አስከፊ ጉዳቶች ለታዳሚው አቅርበዋል።

    ወልቂጤ (ሰሞነኛ)– “ጥበብ ለሰላም” በሚል መሪ ቃል በጉራጌ ዞን ከሚገኙ 17 ወረዳዎችና ከ4 ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ የአገራችን ታዋቂ የኪነ ጥበብ ሰዎች፣ አመራሮች፣ የሲቪል ሰርቪስ (civil service) ሠራተኞች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በወልቂጤ ከተማ ትልቅ ስብሰባ/ውይይት በድምቀት ተካሂዷል።

    በዚህም ዞን አቀፍ የሰላም ንቅናቄ የአገራችን ታዋቂ ሰዎች (በጥቂቱ ለመጥቀስ ያህል ደራሲና መምህር ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፣ ደራሲ እንዳላጌታ ከበደ፣ ደራሲ ህይወት ተፈራ፣ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት ዳይሬክተር ጀነራልና የሙዚቃ ሀያሲው አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት እና ደራሲ ተስፋዬ ጎይቴ ስለ ሰላም እና በሰላም እጦት ምክንያት የሚከሰቱ አስከፊ ጉዳቶች ለታዳሚው አቅርበዋል። የሁሉም የመቋጫ ሀሳብ የአገራችን ህዝቦች አጥር ሳይገድባቸው በብሔር፣ በዘር፣ በጎሳ፣ በሀይማኖትና በመሳሰሉ ከፋፋይ ጉዳዮችን ትተው በአንድነትና በሰብዓዊነት ስሜት ተዋደውና ተቻችለው እንደቀድሞው አብረው ሊኖሩ እንደሚገባ ነው።

    በዚህ ታላቅ የሰላም ንቅናቄ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ጀማልና የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ወ/ሮ መሠረት አመርጋ ሰላም ለሁሉም ጉዳዮች መሠረት መሆኑ እና ሰላም በሌለበት ምንም ሊኖር እንዳማይችል ገልፀው የዞኑ ህዝብ በሙሉ ለሰላም ዘብ መቆም እንዳለባቸው አሳስበዋል።

    “ጥበብ ለሰላም” በሚል በተካሄድው በዚህ መርሀግብር ታዋቂ የአገራችን ደራሲያን፣ የጉራጌ ዞን የባህል ኪነት ቡድን፣ ከወልቂጤና ከቡታጅራ ከተማ አስተዳደሮች የኪነ ጥበብ ክበባት የተውጣጡ አማተር ኪያንያን ድንቅ የሙዚቃ፣ ድራማና የሥነ ግጥም ሥራዎቻቸውን አቅርበዋል። እንዲሁም በሱዑዱ አብደላ የተሳሉ ድንቅ የሥነ ስዕል ሥራዎቹን አቅርቧል። የ11ኛ ክፍል ተማሪ ይዘዲን የፈጠራ ሥራዎች በመድረኩ ከቀረቡ ሥራዎች ይገኝበታል።

    በመጨረሻም ለፕሮግራሙ መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የዞኑ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ያዘጋጃቸው ባህላዊ ስጦታዎች፣ የማበረታቻ ሽልማትና የምስጋና የምስክር ወረቀት አበርክቷል።

    ምንጭ፦ የጉራጌ ዞን አስተዳደር የሕዝብ ግንኙነት ቢሮ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ጥበብ ለሰላም መድረክ በጉራጌ ዞን


    Semonegna
    Keymaster

    ባለፉት ስድስት የሽልማት መርሀግብሮች አገራችን የምትኮራባቸውን የላቀ አርአያነት ያለው ተግባር ላከናወኑ ሰዎች እውቅና የተሰጠው ከሕዝብ በቀረበ ጥቆማ መሠረት ሲሆን፥ የዘንድሮው የበጎ ሰው ሽልማት ፕሮግራም ለአገራቸው እድገት አርአያነት ያለው አስተዋፅኦ ያበረከቱ ዲያስፖራዎች ዕውቅና የሚያገኙበት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)–ሰባተኛው የበጎ ሰው ሽልማት ፕሮግራም የዕጩዎች ጥቆማ ግንቦት 2 ቀን 2011 ዓ.ም. እንደጀመረ እና እስከ ሰኔ 3 ቀን 2011 ዓ.ም. ድረስ እንደሚከናወን የሽልማት አስተባባሪ ኮሚቴው አስታወቀ።

    ኮሚቴው በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለአገርና ለሕዝብ አርአያነት ያለው ታላቅ ተግባርን ያከናወኑ ሰዎችን ዕውቅና የሚሰጠው የበጎ ሰው ሽልማት ሰባተኛው መርሃ ግብር ነሀሴ 26 ቀን 2011 ዓ.ም. በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል ይካሄዳል።

    ሽልማቱም በመምህርነት፣ በሳይንስ፣ በኪነ-ጥበብ፣ በበጎ አድራጎት ሥራ፣ በቢዝነስ ሥራ ፈጠራ፣ በመንግስት የሥራ ተቋማት ኃላፊነት፣ በቅርስና ባህል፣ በማኅበራዊ ጥናት፣ በሚዲያና ጋዜጠኝነት ዘርፎች እና ለኢትዮጵያ እድገት አስተዋፅኦ ያበረከቱ ዲያስፖራዎችን የሚያካትት እንደሆነ ኮሚቴው ገልጿል።

    ለእያንዳንዱ የሽልማት ዘርፍ ሦስት ዳኞች ተመርጠው ምርጫው የሚከናወን ሲሆን ዳኞቹም የረጅም ጊዜ ልምድ ያላቸውና በታማኝነት ምርጫውን ያከናውናሉ ተብለው የታመነባው እንደሆኑ በመግለጫው ወቅት ተጠቅሷል።

    ኮሚቴው እንደገለፀው፥ ባለፉት ስድስት የሽልማት መርሀግብሮች አገራችን የምትኮራባቸውን የላቀ አርአያነት ያለው ተግባር ላከናወኑ ሰዎች እውቅና የተሰጠው ከሕዝብ በቀረበ ጥቆማ መሠረት መሆኑን ገልፆ፥ መርሀግብሩን ለዚህ ያበቃው በሂደቱ የሕዝብ ተሳትፎ በመኖሩ ስለሆነ ይህም አሁንም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀርቧል።

    የበጎ ሰው ሽልማት ዋና ዓላማ ለአገራችን መልካም የሠሩ፣ አገራዊ ተልዕኳውን በብቃት የተወጡ፣ የሕዝብን ኑሮ ለማሻሻል ለውጥ አምጪ ተግባራትን ያከናወኑ፣ የአገሪቱን ታሪክ፣ ቅርስ፣ ባህል እንዲጠበቅና የሀገራቸው ስልጣኔ ከፍ እንዲል የሠሩ ኢትዮጵያዊያንን በማበረታታት ዕውቅና በመስጠት ሌሎች በጎ ሥራዎችን ለሀገራቸው ማበርከት እንዲችሉ ማስቻል ነው።

    ይህንን የበጎ ሰው ሽልማት ዓላማ ከግምት ውስጥ በማስገባት ህብተረሰቡ ጥቆማውን ከግንቦት 2 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ በስልክ፣ በቫይበር (Viber)፣ በቴሌግራም (Telegram)፣ በኋትሳፕ (WhatsApp)፣ በኢሜይል (e-mail)፣ በፖስታና በአካል በመቅረብ መጠቆም እንደሚቻል ኮሚቴው ያሳወቀ ሲሆን፥ ለዚህም አገልግሎት በስልክ ቁጥር 0940140813begosewprize@gmail.com እና ፖስታ ሳጥን ቁጥር 150035 አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ መጠቀም ይቻላል ተብሏል።

    የዘንድሮው የሽልማት ፕሮግራም ለአገራቸው እድገት አርአያነት ያለው አስተዋፅኦ ያበረከቱ ዲያስፖራዎች ዕውቅና የሚያገኙበት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የበጎ ሰው ሽልማት


    Semonegna
    Keymaster

    ተከሳሽ ዓለም ታምራት ከተለያዩ ዓለም ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ የሚደረጉ ጥሪዎችን በማስተላለፍ ኢትዮ ቴሌኮም የዘረጋውን መሠረተ ልማት ወደ ጎን በመተው ዓለም አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት በመስጠት ጥፋተኛ ተብላለች።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– ዓለም ታምራት የተባለችው ተከሳሽ የቴሌኮም መሣሪያዎችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት፣ ለመጠቀም እና የቴሌኮም አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ሕጋዊ ፍቃድ ሳይኖራት ወደ ሕገወጥ ተግባሩ መግባቷ ተጠቁሟል። ወንጀሉ በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ልዩ ስሙ ገርጅ አካባቢ መፈጸሙ ታውቋል።

    የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል የወጣውን አዋጅ ቁጥር 761/2004 አንቀጽ1/ለ ስር የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሳሽ ከቀድሞው ኢፌዲሪ መገናኛ እና ኢንስፎርሜሽን ሚኒስቴር በተሰጠ ፍቃድ ብቻ ወደ ሀገር ውስጥ ለመጠቀም የሚቻሉትን የኮል ተርሚኔሽን (call termination)፣ ኮል ባክ (call back)፣ ጥሪ የመቀበል እና ጥሪ የመላክ አገልግሎት መስጠት እንደነበር ተነግሯል።

    ሆኖም ግለሰቧ ከሕግ አግባብ ውጪ ኢትዮ ቴሌኮም ሲም ካርዶችን በውስጣቸው በማስገባት በአንድ ጊዜ ብዛት ያላቸውን እቃዎች በቅናሽ በመግዛት እና ጥሪዎችን ማስተላለፍ የሚችሉ ብዛታቸው 4 የሆኑ ጌትዌይ (gateway) የቴሌኮም መሣሪያዎችን በድብቅ በማስገባት ወንጀል ፈጽመዋል።

    በድብቅ የገቡ መሣሪያዎችን ከበይነመረብ (internet) የግንኙነት አውታር ጋር በማገናኘት የሚያገኙትን ኔትወርክ (network) በማብዛት ወደ ዋየርለስ ኔትወርክ (wireless network) እንዲቀየር በማድረግ የራሳቸውን ኔትወርክ መፍጠር የሚችሉ 15 ቶፒ ሊንክ የተባሉ መሣሪያዎችን ከሌሎች አጋዥ መሣሪያዎች ጋር መጠቀማቸው በክሱ ቀርቧል።

    ግለሰቧ ከውጭ ሀገር ወደ ሀገር ውስጥ የሚደረጉ የስልክ ጥሪዎችን ኢትዮ ቴሌኮም በዘረጋው ኔትወርክ በኩል እንዲያልፉ በማድረግ ኢትዮ ቴሌኮምን 6,379,342.19 ብር ማሳጣቷ ተጠቅሷል።

    ተከሳሽ ዓለም ታምራት ከተለያዩ ዓለም ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ የሚደረጉ ጥሪዎችን በማስተላለፍ ኢትዮ ቴሌኮም የዘረጋውን መሠረተ ልማት ወደ ጎን በመተው ዓለም አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት በመስጠት ጥፋተኛ ተብላለች።

    ጉዳዩን ተመለከተው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 14 ወንጀል ችሎትም አቃቤ ሕግ ያቀረበውን የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎችን በመመልከት በሚያዝያ 14 ቀን 2011 ዓ.ም. በዋለው ችሎት በ12 ዓመት ጽኑ እስራት እና በ63 ሚሊዮን የገንዘብ መቀጮ አሳልፎባታል።

    ምንጭ፡- የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ / የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ኢትዮ ቴሎኮም


Viewing 15 results - 76 through 90 (of 124 total)