Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Home Forums Search Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Viewing 15 results - 496 through 510 (of 730 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    እንደ አንድ ዜጋ እጠይቃለሁ ― ታማኝ በየነ

    ይድረስ ለኢትዮጵያ መንግስት፤

    እኔ በደረሰኝ መረጃ ከትናንት ጀምሮ በወሎ ከሚሴና በሽዋ አጣዬ በደረሰ ግጭት ንጹሃን ዜጎች እየሞቱ ነው፡፡

    ለመሆኑ ሰላም የነበር አካባቢ በአንዴ ወደ ጦርነት ቀጠና እንዴት ሊለወጥ ቻለ?

    የአማራ ክልል መንግስት በእካባቢው የታጠቁ ሃይሎች ሲገቡና ሲወጡ አላየም ነበር?

    የኦሮሚያ ክልል መንግስትስ ከራሱ ኃይል ውጭ የታጠቀ ኃይል ሲያይ ‘ማን ነህ?’ ብሎ አይጠይቅም ወይ?

    ኦዴፓ (የኦሮሞ ዲሚክራሲያዊ ፓርቲ) እና አዴፓ (የአማራ ዲሚክራሲያዊ ፓርቲ) በእርግጥ እየተነጋገራችሁ ነው የምትሠሩት? ከሆነስ የአንድ ንጹህ ዜጋ ህይወት ከማለፉ በፊት ለምን ግጭቱን ተነጋግራችሁ አትፈቱትም ነበር?

    የፌደራል መንግስት እንደ እኛ ውጭ እንዳለነው እኩል ነው ግጭቱን የሰማው?

    በአጠቃላይ ለተፈጠረው ቀውስ ከፌደራል መንግስቱና ከሁለቱ የክልል መንግስታት ውጭ በዚህ ጉዳይ ተጠያቂ የለም።

    በአጠቃላይ በየቦታው የሚታዩት ግጭቶች ነገን አስፈሪ እያደረጉት ነው፡፡ መንግስት ሁሉንም በእኩል ዓይን አይቶ በጥፋተኛው ላይ የማያዳግም እርምጃ ካልወሰደ ወደ ፈራነው እልቂት እንደምንገባ ለመናገር ትንቢት ተናጋሪ መሆን አያስፈልግም፡፡

    ገና በጠዋት ‘የአብዮታዊ ዲሞክራሲ የዘር ፖለቲካ መሠረት ሲጣል አይበጀንም!’ ብዬ አደባባይ የወጣሁት የዘረ ፖለቲካ መጨረሻው ዛሬ የምናየው በእጅጉ በከፋ ሁኔታ ነገ የምንጋፈጠው መሆኑን በመረዳት ነበር።

    ዛሬ የዘር ፖለቲካ በድርስ ዘዋሪ አፍላ ጎረምሳዎችም፣ እድሜ በተጫናቸው በችግሩ አምጪ አዛውንቶችም በአስፈሪ ሁኔታ እየተራገበ እሳቱ ደግሞ በየቀኑ አገር የቆመችበትን ምሶሶ እየለበለበ የዜጎችን ነፍስ እየቀጠፈ ነው።

    አስገራሚው ነገር በተመሳሳይ ወቅት ያልተማርንበት የሩዋንዳ የዘር ፍጅት መታሰቢያ ለ25ኛ ጊዜ በዓለም መድረክ እየታወሰ ነው። እኛ እንደሌሎቹ ካለፈው መማሩ ቢሳነን ዛሬ እየሆነ ባለው በራሳችን ውድቀት ለመማር እንኳን ዝግጁ የሆንን አንመስልም።

    እርግጥ ነው መንግስት በቅርቡ የአገራችን መሠረታዊ ችግር የምንከተለው የብሔር ፖለቲካ ነው ሲል የደረሰበትን ድምዳሜ በግልፅ ማሳወቁ የተስፋ ምልክት ሆኖ ሊታይ ይችላል።

    ይህ በራሱ ግን ከዛሬው እልቂት የሚታደገን አይደለምና የፌደራል መንግስቱም ሆነ የሁለቱ ክልል መንግስታት በአፋጣኝ ይህን ሁኔታ ቀልብሰው ከዚህ በላይ ሌላ ጉዳት እንዳይደርስ እንዲከላከሉ ይህንን ሰይጣናዊ ተግባር የሚፈፅሙ አካላትንም በሕግ ተጠያቂ እንዲያደርግ እንደ አንድ ዜጋ ለመጠየቅ እወዳለሁ።

    ኢትዮጵያዊው ታማኝ በየነ (አሜሪካ)

    ምንጭ፦ ECADF Ethiopian News / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተያያዥ ዜና፦ አጣየ፣ ካራቆሬ፣ ማጀቴ እና አካባው በሚኖሩ ዜጎች ላይ የታጠቁ ኃይሎች እያደረሱት ያለው ኢ-ሰብአዊ በደል

    ታማኝ በየነ


     

    Semonegna
    Keymaster

    አጣዬ፣ ማጀቴ እና ካራቆሬ በሚባሉ አካባቢዎች የሚኖሩ ሰዎች እንደተናገሩት፥ ጥቃቱን እያደረሱ ያሉት ኃይሎች በሚገባ ዝግጅት ያደረጉ፣ በቁጥር ብዙ ከመሆናቸው የተነሳ ከ አካባቢዎች የሕግ አስከባሪ ፖሊሶች ቁጥር ጋር ሲነጻጸሩ እጅጉን የበዙ እንደሆኑ ተናግረዋል።

    ደብረ ብርሃን (ሰሞነኛ)– በወገኖቻችን ላይ በታጠቁ ኃይሎች እየደረሰ ያለውን ጥፋት የፌዴራል እና የክልሉ መንግስት በአስቸኳይ ሊያስቆሙ ይገባል፤ ሲሉ የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች በሰላማዊ ሰልፍ ጠየቁ።

    በአሁኑ ሰዓት በአማራ ክልል መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች በአጣዬ፣ በካራቆሪ፣ በማጀቴና አካባቢው በሚኖሩ ሰላማዊ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ግድያና ሰቆቃ መንግስት በአፋጣኝ ሊያስቆም ይገባዋል በማለት ድምፃቸውን በሰላማዊ ሰልፍ በመግለፅ ላይ ናቸው።

    አጣዬ፣ ማጀቴ እና ካራቆሬ በሚባሉ አካባቢዎች የሚኖሩ ሰዎች እንደተናገሩት፥ ጥቃቱን እያደረሱ ያሉት ኃይሎች በሚገባ ዝግጅት ያደረጉ፣ በቁጥር ብዙ ከመሆናቸው የተነሳ ከ አካባቢዎች የሕግ አስከባሪ ፖሊሶች ቁጥር ጋር ሲነጻጸሩ እጅጉን የበዙ እንደሆኑ ተናግረዋል።

    በታጠቁ ኃይሎች የመቁስል አደጋ የደረሰባቸው መገኖቻችን ተገቢውን ህክምና እንዲያገኙ የተዘጉ መንገዶችን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጣልቃ ገብቶ እንዲያስከፍትም ጠይቀዋል።

    ሰልፉ እስካሁን በሰላማዊ አግባብ ተካሄዶ የተጠናቀቀ ሲሆን በአጣዬ ከተማ በህብረተሰቡ ላይ ጥቃት እያደረሰ የሚገኘው ኦነግ መሆኑን የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደርና ፀጥታ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ካሳሁን እምቢያለ ገልጸው ችግሩ ከዞኑ አቅም በላይ በመሆኑ መከላከያ ሠራዊት ገብቶ አካባቢውን እንዲያረጋጋ ድጋፍ የተጠየቀ ቢሆንም በወቅቱና በፍጥነት ባለመግባቱና ከገባም በኋላ እርምጃ እንድወስድ አልታዘዝኩም በማለቱ ችግሩ እየተባባሰ መሄዱን ተናግረዋል።

    በአጣዬ ከተማ የኦነግ (የኦሮሞ ነጻ አዉጪ ግንባር) የታጠቀ ኃይል ባደረሰው ጥቃት በሰው ህይወት እና ንብረት እንድሁም በሀይማኖት ተቋማት ላይ ውድመት መድረሱን ኃላፊው ገልጸዋል።

    ጥቃቱን እየፈጸመ ያለው ኃይል በተለየ መንገድ ስልጠና የወሰደ በመሆኑ ይህን አካል መደምስ ካልታቻለ የሕዝቡን ሰላምና ደህንነት ለማስከበር አስቸጋሪ በመሆኑ የክልሉና የፌዴራል መንግስትን የተቀናጀ መፍትሄ መስጠት አለባቸው ብለዋል።

    ከኦሮሚያ ክልል መንግስት ጋር በሚያዋስኑ ወረዳዎች እና ቀበሌዎች ሰላማዊ ግኑኙነት መኖሩን ጠቁመው፥ በከሚሴ ልዩ ዞን ዙሪያ የተፈጠረውን ክስተት ለመፍታት በየደረጃው የሚገኘው የመንግስት አካል የተለየ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሆነም ተናግረዋል።

    የአማራ መገናኛ ብዙሃን ድርጅት (አብመድ) ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ እንደዘገበው፥ ወደ አጣየ፣ካራቆሬ እና ማጀቴ መከላከያ ገብቷል፤ ሁኔታውም ከሌሎች ቀናት ይልቅ በአንጻራዊ መሉ እሁድ (መጋቢት 29 ቀን፥ 2011 ዓ.ም.) እየተረጋጋ መምጣቱን፤ ተጨማሪ ፀጥታ አስከባሪ ኃይልም እየገባ መሆኑን የአማራ ክልል የሰላምና ደኅንነት ግንባታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኮሎኔል አለበል አማረ አስረድተዋል።

    የፀጥታ ችግሩ ሙሉ በሙሉ ባይቀረፍም ከቅዳሜ እና ከእሁድ ረፋዱ (መጋቢት 28–29 ቀን፥ 2011 ዓ.ም.) የተሻለ መሆኑን የተናገሩት ኮሎኔል አለበል፥ ተደራጅቶ ሕዝብን ሰላም እያሳጣ ያለውን ቡድን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር የተቀናጀ ሥራ እንደሚከናወንም አረጋግጠዋል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አጣዬ፣ ማጀቴ እና ካራቆሬ


    Semonegna
    Keymaster

    የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ከስዊድኑ ጎተንበርግ ዩኒቨርሲቲ (The University of Gothenburg) ጋር በትብብር የቅርስ ጥበቃና እንክብካቤን የሚመለከት ትምህርት ለመስጠት የሚያስችላቸው የመግባቢያ ሰነድ ይፈርማሉ።

    በቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ መስክ በሀገራችን ያለውን የባለሙያ እጥረት የሚቀርፍ መነሻ ሀሳብ ከስዊድን ጎተንበርግ ዩኒቨርሲቲ የመጡ መምህራን ለክቡራን ሚንስትሮች ገለፃ አድርገዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ሀገራችን ኢትዮጵያ ከስዊድን መንግስት ጋር ያላት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑ በተለይ በኪነ-ሕንፃ ትህምርት ዘርፍ ያላቸው ልምዶች ታሪካዊና ጠናካራ ግንኙነት የተፈጠረበት መሆኑ ብዙ ይወሳል።

    በመሆኑም የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ስዊድን ውስጥ በትልቅነቱ ሁለተኛ ከሆነው ጎተንበርግ ዩኒቨርሲቲ (The University of Gothenburg) ጋር በትብብር ለመክፈት ያሰበው የቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ እውን እንዲሆንና የቅርስ ጥገና ተግባራዊ ትምህርት በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ እንዲሰጥ ታስቦ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በኩል ቅድመ ዝግጅት መጀመሩን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አርኪዮሎጂ (archeology) ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት ዶ/ር መንግስቱ ጎበዜ፥ የታሰበው የትምህርት መርሀግብር ለክቡራን ሚኒስትሮች (ለፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ፥ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ እና ለወ/ሮ ብዙነሽ መሠረት፥ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የባህል ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ) የሥልጠናውን ዓላማና ግብ የሚያግባባ ገለፃና ትውውቅ አድርገውላቸዋል።

    በመቀጠልም በልዑካኑ በስዊድን ጎተንበርግ ዩኒቨርሲቲ በኩል የመጡት መምህራን ያላቸውን ዝግጁነትና ተቋማዊ አደረጃጀት እንዲሁም የገጠሩ ሕዝብ ባህላዊ ሀብቱን እየተወ ወደ ከተማ ከሚኮበልል እዛው በቅርሱ ተጠቃሚ የሚሆንበት መሠረት የጣለ ልምድ መኖሩን የሚያብራራ ገለጻ በ‘Bosse Lagerqvist’ እና ‘Lars Runnquist’ የልዑኩን ቡድ ኑን በመወከል ገለፃ አደርገዋል። ተመራማሪ ፕሮፌሰሮች በነሱ በኩል ተግባራዊ ትምህርቱ ከቁሰቁስ አቅርቦት እንደሚደገፍ ጭምር በትብብር የሚሠራበት ሁኔታ ለመፍጠር በቻርትና ስዕላዊ መግለጫዎች ማብራሪያ አድርገዋል።

    ሰባት ዩኒቨርሲቲዎች፣ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እና STEMpower ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ

    ለመርሀግሩ ማጠቃለያ ክቡራን ሚኒስትሮችም በበኩላቸው በሁለቱም ሀገራት መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ታሪካዊ ግንኙነት መልካም በሚባል ደረጃ የደረሰ መሆኑን በማመስገን፥ ያቀረባችሁት ሀሳብ የሚጠቅመንና እንደኢትዮጵያ በቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ መስክ የሚሰጡ ትምህርቶች በንድፈ-ሀሳብ ብቻ በመሆኑ በትብብር ስለምንሠራው ብዙ ባለሙያዎችን የምናፈራበት ዕድል ይፈጥራል ብለዋል።

    የትምህርት ማስተማሪያ መርሀግብሩ የሁለተኛ ዲግሪ ለመስጠት የሚያበቃ ሲሆን፥ ለዚህ የመግባቢያ ሰነድ በቅርብ ጊዜ እንደሚፈረም እንዲሁም ተግባራዊ ትምህርቱ የሚሰጥበት ቦታ አንድ ካምፓስ በላሊበላ ቅርጫፍ የሚዘጋጅበት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።

    ምንጭ፦ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የወልድያ ዩኒቨርሲቲ


    Anonymous
    Inactive

    የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ አንድ ቋት ዋሽ አካውንት ፕሮግራምን ተቀላቀለ
    —–

    የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (KOICA) የዋን ዋሽ ብሔራዊ ፕሮግራም አካል የሆነውን አንድ ቋት ዋሽ አካውንት (Consolidated WASH Account) ፕሮግራም ተቀላቀለ።

    የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (KOICA) ላለፉት በርካታ ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን፤ በመስኖ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ህብረተሰብን ተጠቃሚ በሚያደርጉ የልማት ፕሮጀክቶች ላይ በመሳተፍ ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል።
    ኤጀንሲው በመደበኛ ፕሮግራሙ ከሚያከናውናቸው ተግባራት በተጨማሪ ከ2012 በጀት ዓመት ጀምሮ በሚከናወነው የሁለተኛው ዙር አንድ ቋት ዋሽ አካውንት (Consolidated WASH Account) ፕሮግራም በመቀላቀል ፕሮግራሙን ለመደገፍ 10 (አሥር) ሚሊን ዶላር የድጋፍ ስምምነትን የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ዳይሬክተር የሆኑ ሚስተር ዶንግ ሆ ኪም እና የውሃ ፤ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ነጋሽ ዋጌሾ መጋቢት 18/2011 ዓ.ም ተፈራርመዋል።

    የሁለቱ ሀገራት የረጅም ዘመናት ትብብር ይበልጥ እየተጠናከረ መምጣቱን ሚኒስቴር ዴኤታው በማስታወስ ከዚህ ከተመደበው በጀት ውስጥ 7 ሚለዮን ዶላር ለመጠጥ ውሃ አቅርቦት እና ቀሪው 3 ሚሊዮን ዶላር ኮይካ ከዚህ በፊት የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን በሚያከናውንባቸው አከባቢዎች የገጠር ሳኒቴሽንን ሽፋን ለማሳደግ የሚውል በጀት መሆኑን አስረድተዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

    Anonymous
    Inactive

    “ገና በጠዋቱ ሀገሪቱ መሪ እያላት ስርዓት አልበኝነት ነገሰ፣ ሕግ ረከሰ፣ የንፁሃን ደም በከንቱ ፈሰሰ የሚል ጩኸት ብዙዎች ቢያሰሙም የሽግግር ባኅሪው ነው በሚል ሚዛናዊ ምላሽ መስጠት አልተቻለም።”
    ———–

    ሚዛናዊነት ከራስ ቢጀምር ― ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)

    አለማየሁ ገበየሁ

    ፍርድ ቤት የቆመችው የፍትህ ምስል /Lady Justice/ ተጠሪነቷና ምሳሌነቷ ለፍርድ ቤት ሥራ ብቻ አይመስለኝም። አይኗን ሸፍና ያላጋደለ ሚዛን የያዘችው አስተዳዳሪዎች በሞራል ሕግ ተመርተው ለዜጎች ሁሉ ሚዛናዊ አገልግሎትና ውሳኔ እንዲያስተላልፉ ነው።

    ዶ/ር አብይ አህመድ ደጋግመው ስለሚዛናዊነት ይሰብካሉ። ጋዜጠኞች የተመጣጠነ ዜና እንዲያቀርቡ፣ አክቲቪስቶች ከዋልታ-ረገጥ ሀሳብ ወደ መሃል እንዲመጡ፣ ፖለቲከኞች እኔ ብቻ ነኝ አዳኝህ ወይም የማውቅልህ ከሚለው አባዜ ተላቀው ለሌላውም ሥራ እውቅና እንዲሰጡ ወዘተ…

    የሚዛን መንሻፈፍ ግለሰብን፣ ማኅበረሰብንና ሀገርን እየቆየ እንደሚጎዳና ለማይጠገን ቀውስ እንደሚዳርግ የሚገነዘብ ሁሉ በዚህ ሀሳብ ይስማማል። ችግሩ ዶ/ር አብይ እንዳሉት ሁሉም ቀድሞ ጣቱን የሚቀስረው ሌሎች ላይ የመሆኑ አባዜ ነው። ይህ የጣት ቅሰራ ራሳቸው ዶ/ር አብይንም ይመለከታል። አንዱን ትልቅ ጥፋት ሸፋፍነህ ሌላው ላይ ጣትህን ስትቀስር ሚዛናዊነት ይንጋደዳል። አንዱን ትልቅ ጥፋት አላየሁም ብለህ አይንህን ከሸፈንክ ሌላኛው ጥፋት ላይ የአይንህን መጋረጃ ቀደህ ለመጣል ሞራል ታጣለህ።

    ከብዙ ምሳሌዎች የተወሰኑትን ብቻ እናንሳ። ገና በጠዋቱ ሀገሪቱ መሪ እያላት ስርዓት አልበኝነት ነገሰ፣ ሕግ ረከሰ፣ የንፁሃን ደም በከንቱ ፈሰሰ የሚል ጩኸት ብዙዎች ቢያሰሙም የሽግግር ባኅሪው ነው በሚል ሚዛናዊ ምላሽ መስጠት አልተቻለም። ከዚህ ይልቅ በቅድሚያ ለውጡ ያመጣቸውን ትሩፋቶች ሳትደባብቁ አሞግሱ ማለት መጣ። ትክክል ነው ሚዛናዊ ለመሆን የበርካታ ባኅሪያት/ ጥሩ ተናጋሪ፣ ትዕግስተኛ፣ ይቅር ባይ፣ ትሁትና የሰላም አጋር/ መሆናቸውን መመስከር ይቻላል። በዚህ ጥሩ ባኅሪ በመታገዝም መንግስታቸው አስደሳች ፖለቲካዊ ድሎች አስመዝግቧል። ይህ ማለት ግን ለውጡ መሳ ለመሳ እየተጓዘ ያለው ከነውጥ ጋር ነው ነው ማለት ስህተት አይደለም። ሕገ-ወጥነት ሀገሪቷን የወረረው ይቅርባይነት ስለበዛ ነው የሚል የቄለ ግምገማ የለኝም – በዚህ ረገድ መንግስታቸው ስትራተጂካዊ ብቃት የለውም የሚለው ሀሳብ የበለጠ ቅርብ ነው። አሁን በቅርቡ እንኳን የሀገራችን ስርዓት አልበኝነት ተግባር ከ8 እስከ 10 ወራት ይቀጥላል በማለት እንደ ዓመታዊ ዕቅድ ነግረውናል። ሕገ-ወጥነትን አምርሮ ከመታገል ይልቅ ከሕገ-ወጥነት ጋር ተቻቻሎ ለመኖር ማሰብ ገራሚ አቋም ነው። በተሸፋፈነች ፍትሃዊ አይን ሚዛናዊነትን እንይ ከተባለ ከዚህም በላይ ነው።

    መንግስት ባለበት ሀገር አሥራ ምናምን ባንኮች በጠራራ ፀሐይ ሲዘረፉ የሽግግር ሂደት ባኅሪው ነው የምትል ከሆነ ሌላውን ሌባ ወይም ሙሰኛ ለመገሰጥም ሆነ ፍርድቤት ለማቆም ይከብዳል። ምክንያቱም ፍ/ቤት የቆመችው የፍትህ ምስል ስለምትታዘብ። ለተቃውሞ ዱላና ገጀራ አደባባይ ይዞ የወጣ ማኅበረሰብ በቸልታ አልፈህ ያለዱላ ስብሰባ የከተመውን ወጣት በማያሳምን ምክንያት አስረህ የምታሸማቅቅ ከሆነ የሚዛናዊነት መሠረትህ ተናደ ማለት ነው። ይከበር እየተባለ የሚለፈፈው ሕግ ባለመከበሩ ዱላና ገጀራው አድጎ እነሆ ዛሬ የጦር መሣሪያ ይዞ አደባባይ መውጣት ተጀምሯል። በገዛ ፍቃድህ ሚዛናዊ ካልሆንክ ብሎም ቸልተኝነት እንደ ኩይሳ ካሳደግክ ሌሎች አደባባይ የተገተረውን የፍትህ ሚዛን በሌላ ጡንቻ ይሰብሩብሃል። ትርፉና ውጤቱም ይሄው ነው።

    የቸገረው የከተማ ህዝብ ከሰውነት ተራ ወጥቶ በሠራው ኮንዶሚኒየም አትገባም ተብሎ ገጀራ ሲወደርበት “የባለገጀራዎች ሀሳብ ይለምልም” ብሎ መግለጫ ማውጣት እንዴት ሚዛናዊ ሊሆን ይችላል? በቡራዩና ለገጣፎ ሰላማዊ ዜጎች ላይ የደረሰው መፈናቀል፣ እንግልትና አግላይ ርምጃዋች ከልብ ሳታወግዝ ሌላ ታፔላ ለጥፎ አደባብሶ ማለፍ የሚዛናዊነትን ጥያቄ ያስነሳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገር የሚበትኑ ሀሳቦች ይወገዙ ይላሉ። በሀገሪቱ ያለው ሁለት መንግስት የአብይና የቄሮ ይባላል የሚል ትንታኔ የሚሰጠው ጃዋር የበርካታ በታኝ ሀሳቦች ባለቤት ቢሆንም ውግዘት አይመለከተውም። ኦሮሞ ከቋንቋው ውጭ ሌሎችን ማነጋገር የለበትም፤ ከሌሎች ጋር መጋባትም ማቆም አለበት የሚለው የ“ምሁሩ” በቀለ ገርባ አፓርታይዳዊ አስተያየት ለመመርመርም ሆነ ለመተቸት አልተፈለገም። በተቃራኒው የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ጥቅም ለማስጠበቅ በሚንቀሳቀሰው እስክንድር ነጋ ላይ ግልጽ ጦርነት እናውጃለን ተብሏል። ሲጠቃለል ዶ/ር አብይ በበቀለ፣ በኦነግ፣ በጃዋር፣ በሕገወጥ ፖለቲከኞችም ሆነ በእስክንድር ሀሳብ ላይ ሚዛናዊ መሆን አልቻሉም።

    ለዚህም ነው ማንኛውም ሚዛናዊ ለመሆን የሚጥር ሰው ለምን የሚል ቀጥተኛ ጥያቄና እንዴት የሚል የጀርባ ምፀት ለማንሳት የሚገደደው። ግዜ የሰጠው ቅል ድንጋይ እንዲሰብር ብሂሉ ስለሚያስገድድ? ምንም ቢሆን ዘር ከልጓም ስለሚስብ?… ኢትዮጵያዊነትን መርህ አድርጌያለሁ የሚል መሪ ለጃዋርም ሆነ ለእስክንድር ሀሳቦች እኩል የድጋፍም ሆነ የተግሳጽ መስፈርት ማበጀት ካልቻለ መርሁ ሁሉ ፈጥኖም ሆነ ዘግይቶ ለራሱ ችግር ይፈጥሩበታል (backfire ያደርግበታል)። ዶ/ር አብይ ከጊዜ ወደጊዜ እየገረጣ የመጣባቸውን ሕዝባዊ እምነት ስር ሳይሰድ ለማከም ከፈለጉ ሚዛናዊነት ከራሳቸው መጀመር ያለባቸው ይመስለኛል። ጥሩ መሪ ደግሞ እንደዛ ነው። መንገዱን የሚያውቅ፣ በመንገዱ የሚሄድ እና መንገዱን የሚያሳይ ስለሚሆን። ባለጊዜ ነን በሚሉ ቡድኖች የሚጊሩ አስከፊና አቀያያሚ ጉዳዮችን አደብ ማስገዛት፣ አቅም ቢያጥር እንኳን በግልጽ ‘አካፋን አካፋ’ በማለት ማውገዝ መጀመር አለባቸው። ከዚህ ከጀመሩ ሌላኛውን ብልሹ ሀሳብና ተግባር ለማረቅ ምቹ መደላድል ይፈጥራል። ይህ አካሄድ ልበ ሙሉነትን በቀላሉ ማትረፍ የሚያስችል ሲሆን፥ ከሁሉም አቅጣጫ በቂ ድጋፍ ያስገኛል። አክባቢዎን በሚያውቋቸው ሰዎች መሙላት ብቻ ሳይሆን ገለልተኛና ሚዛናዊ ሀሳብ የሚሰጡትንም አማካሪዋች ቢያበዙ ጭልጥ ብሎ ከመሳሳትም ያድናል።

    አለማየሁ ገበየሁ

    ሚዛናዊ


    Semonegna
    Keymaster

    በቪክቶሪያ እና አልበርት ሙዚየም የሚገኙ የመቅደላ ስብስብ ቅርሶች በአጭር ጊዜ ሊመለሱ ይችላሉ
    —–

    ለንደን የሚገኙ ቅርሶች የሚያዙበት ሁኔታና የሚተዳደሩበት ሕግ በጣም ጠንካራ ነው። በየትኛውም አጋጣሚ እጃቸው ላይ የገባ ቅርስ በሕጉ መሠረት ይተዳደራል። ስለሆነም የእኛም ቅርሶች የዚሁ አካል ናቸው ማለት ነው። ይሁን እንጂ እነዚህ ቅርሶች ለኢትዮጵያውያን የማንነትና የእድገት መሠረቶች ናቸውና ሊመለሱልን እንደሚገባ በተደጋጋሚ ሲጠየቁ ቆይተዋል።

    እ.ኤ.አ በ2018 ከወደ ቪክቶሪያ እና አልበርት ሙዚየም ብቅ ያለው መረጃ በረጅም ጊዜ ውሰት ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ማድረግ እንደሚቻል ገለጸ። የማንን ቅርስ ማን አበዳሪ? ማንስ ተበዳሪ? እንዴት አይነት ድፍረት ነው?ወዘተ… ብለን ተቆጨን። እነሆ የይመለሱልን የሕዝብ ጥያቄው በክብርት ዶ/ር ሂሩት ካሳው (የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር)፣ በልዑካን ቡድኑና በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል ቅርሶቹ ተጎበኙ፤ ጥያቄውም ቀረበ ሰፊ ውይይትም ተደረገ። ዳይሬክተሩ ዶ/ር ትሪስትራም ኸንት /Tristram Hunt/ ጥያቄው ተገቢ መሆኑን ‘ውሰት’ የሚለው ቃልም ለኢትዮጵያውያን ከባድ መሆኑን እንደተረዱት በመግለጽ የተቸገሩት የሕግ ጉዳይ በመሆኑና ምላሽ ለመስጠት ያለን አማራጭ ይህ ብቻ ስለሆነ ነው አሉ። አክለውም ያለን አማራጭ ይህን ቀዳዳ በመጠቀም ሊስተካከሉ የሚችሉ አባባሎችን ተጠቅመን የሚመለሱበትን ሁኔታ መፍጠር ይህን ካላደረግን ግን በሕጉ ላይ ጸንተን ወደፊት የሚሆነውን ነገር መመልከት ይኖርብናል ብለዋል። በመቀጠልም ከክብርት ሚንስትሯም የተለያዩ ማሳመኛ ምክንያቶች ከቀረቡ በኋላ በሙዚየሙ፣ በኤምባሲውና በሚንስቴር መሥሪያ ቤቱ በኩል ጊዜ ሳይሰጠው በአስቸኳይ መግባቢያ ሰነዱን ካለው ሕግ ጋር በማይጋጭና የኢትዮጵያን ጥያቄ ሊመልስ በሚችልበት ሁኔታ ሠርተን በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት እልባት እንደሚያገኝ ዳይሬክተሩ ገልጸው ስምምነት ላይ ተደርሷል።

    በፈጣንና ታታሪ አመራሮችና ባለሙያዎች የተደራጀው ኤምባሲም ባለው ሙሉ አቅምና ጊዜ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በመወጣት ቅርሶቹ ወደ አገራቸው እንዲገቡ እንደሚያደርጉ ሃላፊነቱን መቀበላቸውን ክቡር አምባሳደሩ ፍሰሃ ሻወል ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – የአጼ ቴዎድሮስ ልጅ የልዑል አለማየሁ አፅም ከሀገረ እንግሊዝ ወደ እናት ሀገሩ እንዲመለስ ኢትዮጵያ ተጠየቀ። በተጨማሪም ለንደን ከተማ ውስጥ በቪክቶሪያ እና አልበርት ሙዚየም (Victoria and Albert Museum) የሚገኙ የኢትዮጵያ ቅርሶች ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ጥያቄ ቀርቧል።

    በኢፌዴሪ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶ/ር ሂሩት ካሳው የተመራው የልዑካን ቡድን መጋቢት 13 ቀን 2011 ዓ.ም. በለንደን ጉብኝት አድርገዋል።

    በዚሁ ወቅትም በለንደን የዊንዶዘር ቤተመንግስት (Windsor Castle) የልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስን መካነ መቃብር እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አፄ ሃይለስላሴ ይጸልዩበት የነበረውን ወንበር ጎብኝተዋል።

    ዶ/ር ሂሩት ካሳው በአጼ ቴዎድሮስ ልጅ ልዑል አለማየሁ መቃብር ላይ የአበባ ጉንጉን ማስቀመጣቸውን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴርን እንደመረጃ ምንጭነት በመጥቀስ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዘግቧል።

    በጉብኝቱ ወቅትም “የአጼ ቴዎድሮስን ፀጉር ማግኘታችን ደስ ብሎናል፤ ይሁን እንጂ ከትውልድ ቦታው ተለይቶ ህይወቱ ያለፈው ልዑል አለማየሁ አፅም በትውልድ ሀገሩ እንዲያርፍ የኢትዮጵያዊያን ጥያቄ ስለሆነ በክብር ወደ አገሩ እንዲመለስ” ሲሉ ዶክተር ሂሩት ጠይቀዋል።

    አፅሙ ወደኢትዮጵያ ተመልሶ ከአባቱ አጼ ቴዎድሮስና ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር መቀላቀል እንደሚገባውና የዊንዶዘር ቤተመንግስት ለሚመለከተው አካል ጥያቄውን አቅርቦ በአፈጣኝ ምላሽ እንዲሰጥም ጥሪ አቅርበዋል።

    በዕለቱ ልዑካን ቡድኑን በመቀበል ከቡድኑ ጋር የተወያዩት የዊንዶዘር ቤተ-መንግስት ሃላፊ ዶ/ር ማርክ ፓወል በበኩላቸው በጉዳዩ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንነጋገርበታለን ብለዋል። ሂደቱን በተመለከተ በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በመከታተል እልባት እንዲያገኝ አስፈላጊውን ጥረት እንደሚያደርግም ሚኒስቴሩ ተገልጿል።

    በሌላ በኩል የልዑካን ቡድኑ መጋቢት 12 ቀን 2011 ዓ.ም. ለንደን የሚገኘውን የቪክቶሪያ እና አልበርት ሙዚየም ጎብኝቷል። በዶ/ር ሂሩት ካሳው የተመራው የልዑካን ቡድኑና በለንደን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከሙዚየሙ ዳይሬክተር ዶ/ር ትሪስታራም ኸንት (Tristram Hunt, PhD) ጋር ተወያይቷል። በውይይቱ ወቅት በቪክቶሪያ እና አልበርት ሙዚየም የሚገኙ የመቅደላ ስብስብ ቅርሶች ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ጥያቄ ቀርቧል።

    እ.አ.አ በ2018 የቪክቶሪያ እና አልበርት ሙዚየም የሚገኙ የመቅደላ ስብስብ ቅርሶች ለኢትዮጵያ መመለስ እንደማይችል፤ ነገር ግን በረጅም ጊዜ ውሰት ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ማድረግ እንደሚቻል መገለጹ ይታወቃል። የሙዚየሙ ዳይሬክተር ዶ/ር ትሪስታራም ኸንት ጥያቄው ተገቢ መሆኑን ጠቅሰው ውሰት የሚለው ቃልም ለኢትዮጵያውያን ከባድ መሆኑን እንደተረዱት ተናግረዋል። በመሆኑም “የተቸገሩት ጉዳዩ የሕግ ጉዳይ በመሆኑና ምላሽ ለመስጠት ያለን አማራጭ ይህ ብቻ ስለሆነ ነው ” ብለዋል።

    “ያለን አማራጭ ይህን ቀዳዳ በመጠቀም ሊስተካከሉ የሚችሉ አባባሎችን ተጠቅመን የሚመለሱበትን ሁኔታ መፍጠር፤ ይህን ካላደረግን ግን በሕጉ ላይ ጸንተን ወደፊት የሚሆነውን ነገር መመልከት ይኖርብናል” ሲሉም ዶ/ር ኸንት አክለዋል።

    የባህል ሚኒስትሯ ዶ/ር ሂሩት ቅርሶቹ የኢትዮጵያ በመሆናቸው በረጅም ጊዜ ውሰት ሳይሆን በቋሚነት ቅርሶቹ ለኢትዮጵያ መመለስ የሚችሉበት አማራጭ መፍትሄ ሙዚየሙ ሊያበጅ እንደሚገባ አመልክተዋል።

    በኤምባሲውና በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በኩል በአስቸኳይ መግባቢያ ሰነድ በመፈራረም፣ ካለው ሕግ ጋር በማይጋጭና የኢትዮጵያን ጥያቄ ሊመልስ በሚችልበት ሁኔታ በመንቀሳቀስ ጉዳዩ በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት እልባት እንደሚያገኝ ዳይሬክተሩ ገልጸፀዋል።

    በለንደን ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲም ባለው ሙሉ አቅምና ጊዜ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በመወጣት ቅርሶቹ ወደ አገራቸው እንዲገቡ እንደሚያደርጉ በብሪታኒያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍስሃ ሻወል ገብሬ ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ልዑል አለማየሁ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– ከ12 ቀናት በፊት የተከሰከሰው ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነው የቦይንግ 737 ማክስ 8 (Boeing 737 MAX 8) አውሮፕን አብራሪ ተገቢዉን የምሰለ በረራ (simulator) ስልጠና አልወሰደም በሚል መጋቢት 11 ቀን 2011 ዓ.ም. ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ (The New York Times) ሰላም ገብረኪዳን በተባለች ትውልደ ኢትዮጵያዊት ጋዜጠኛ ፀሐፊነት ያወጣው ዘገባ ከእውነት የራቀ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ።

    “ምንም እንኳን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ማክስ ምስለ በረራ ቢኖረውም የተከሰከሰውን አውሮፕላን ያበር የነበረው ፓይለት የዚህ ምስለ በረራ ስልጠና አልተሰጠውም” (Ethiopian Airlines had a Max 8 simulator, but pilot on doomed flight didn’t receive training on it) በሚል ርዕስ ኒው ዮርክ ታይምስ ያወጣው ዘገባው ከእውነት የራቀና ኃላፊነት የጎደለው መሆኑንም አየር መንገዱ አመለክቷል።

    የአደጋው መንስዔ እየተጣራ ባለበት በአሁኑ ሰዓት ሁሉም አካላት እንዲህ መሰል አሳሳች መረጃ ከማሰራጨት እንዲታቀቡም አየር በሚገባ መንገዱ በአጽንዖት አሳስቧል።

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መረጃ፥ የተከሰከሰው አውሮፕላን አብራሪ ሁሉንም አግባብነት ያላቸው የበረራ ስልጠናዎችን መውሰዱን አስታውቋል።

    ● SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest

    አውሮፕላን አብራሪው በቦይንግ የአውሮፕን አምራች ኩባንያ (The Boeing Company) እና በአሜሪካ አቪዬሽን አስተዳደር (US Federal Aviation Administration) የተቀመጡ ሁሉንም የበረራ ስልጠናዎችን መውሰዱንም ነው በመግለጫው የገለጸው።

    ዋና አብራሪው ከወራት በፊት በኢንዶኔዥያው ላየን ኤየር (Lion Air) በደረሰው ተመሳሳይ የአውሮፕላን አደጋ ጋር በተያያዘ አስፈላጊዉን የአደጋ ጊዜ የበረራ መመሪያ በቂ ግንዛቤ እንደተሰጠዉም ተገልጿል።

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ አብራሪዎቹን ለማሰልጠን የሚያስችሉ የተሟሉ 7 ምስለ በረራዎች ወይም የበረራ ማሰልጠኛዎች እንዳሉት አስታውቋል። በአሁን ወቅት ብቁና የተሟሉ ኪው 400፣ ቢ737 ኤን ጂ፣ ቢ 737 ማክስ፣ ቢ 767 ፣ ቢ 787 ፣ ቢ 777 እና ኤ 350 የተሰኙ ሰባት ምስለ በረራዎች እንዳሉት ይፋ አድርጓል።

    በአፍሪካም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከተሟላ የስልጠና መሣሪያ ጋር በቂ ስልጠና ከሚሰጡት ጥቂት ተቋማት መካከል አንዱ መሆኑንም ነው ያስታወቀው – የኢትዮጵያ አየር መንገድ። ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ ባልተለመደ ሁኔታ ከስልጠና ጋር ተያይዞ ለመሠረተ ልማት ግንባታ ከግማሽ ቢሊየን ዶላር በላይ ወጭ እንዳደረገ ተነግሯል።

    የዓለም አቀፍ ሕግን በመከተል የአደጋው መንስዔ ተጣርቶ ይፋ እስከሚደረግ ድረስ በትዕግስት መጠበቅ ተገቢ መሆኑንም አየር መንገዱ አስታውቋል።

    ምንጭ፡- የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የዓለም የውሃ ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ በአዲስ አበባ ከተማ መጋቢት 13 ቀን 2011 ዓ.ም. “ማንንም ባለመተው” (“Leaving no one behind”) በሚል መሪ ቃል ተከብሯል። የዓለም የውሃ ቀን በዓለም አቀፍ ለ27ኛ ጊዜ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ26ኛ ጊዜ የተከበረ ሲሆን፥ በሥነ ስርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ የጤና ሚኒስቴር፣ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርና ሌሎች ተቋማት ተዎካዮችና የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

    በበዓሉ መርሀግብር ላይ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት የሚተገበር የሁለተኛው ዋን ዋሽ ብሔራዊ መርሃ ግብር (One WASH National Program) ይፋ መደረጉን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታውቋል።

    የሁለተኛው ዋን ዋሽ ብሔራዊ መርሃ የገጠር፣ የከተማና የተቋማት ንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት፣ ንጽሕና እና የጤና ንጽሕና አጠባበቅ (water, sanitation and hygiene) የሚያካትትና በሀገር አቀፍ (ብሔራዊ) ደረጃ የሚተገበር፣ የመጠጥ ውሃ፣ሳኒቴሽንና ሃይጅንን በገጠር፣ በከተማ፣ በት/ቤቶችና በጤና ጣቢያዎች ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን የሚረዳ እንደሆነ ተገልጿል።

    ● SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest

    ይህ መርሀግብር (ፕሮግራም) በውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ በትምህርት ሚኒስቴር፣ በጤና ሚኒስቴር፣ በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር፣ በልማት አጋር አካላትና በህብረተሰቡ ቅንጅት የሚተገበር ነው።

    የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ነጋሽ ዋጌሾ ዋን ዋሽ መርሀግብር (One WASH Program) በዓለም አቀፍ ደረጃ ለየት ያለ ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ እየተተገበረ ያለ ፕሮግራም መሆኑን ጠቁመው፥ መንግሥት፣ የልማት አጋሮችና ሕብረተሰቡ አንድ ላይ ሀብት በማሰባሰብና ወደ አንድ ቋት በማስገባት፣ አንድ ላይ በማቀድ፣ አንድ ላይ አፈጻጸሙን በመከታተልና በመገምገም፣ አንድ ላይ ሪፖርትም በማድረግ የሚፈጸም ፕሮግራም መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው ተናግረዋል።

    የመጀመሪያው የዋን ዋሽ ፕሮግራም ባለፉት አራት ዓመታት ከስድስት ወራት ሲተገበር መቆየቱን የተናገሩት ሚኒስትር ዴኤታው፥ ሁለተኛው የዋን ዋሽ ፕሮግራም ከ2012 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ ትግበራ እንደሚገባና የአምስት ዓመታት ፕሮግራም መሆኑን ተናግረዋል። በመጀመሪያው ፕሮግራም 3ነጥብ6 ሚሊየን ሰዎችን ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን፥ 90 በመቶ ያህል ተግባራዊ መደረጉ ነው የተገለጸው። በሚቀጥሉት ወራትም እቅዱን በመቶ በመቶ ለማካናዎን እንደሚሰራ ተጠቁሟል።

    ሁተለኛው ዋሽ በመጀመሪያው የዋን ዋሽ ፕሮግራም ይተገበር ከነበረው በገጠርና በከተማ፣ በጤና ተቋማትና በት/ቤቶች የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽንን ለህብረተሰቡ ከማቅረብ በተጨማሪ ለድርቅ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚተገበረውን ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የመጠጥ ውሃ ፕሮግራም (Climate Resilient WASH) የተካተተበት እንደሆነ ዶ/ር ነጋሽ ዋጌሾ ተናግረዋል።

    በሁለተኛው የዋን ዋሽ ፕሮግራም ከመንግሥት፣ ከልማት አጋሮች፣ ከህብረተሰቡ ቀጥተኛ ተሳትፎ፣ በአነስተኛ ወለድና በረጅም ጊዜ ክፍያ የሚከፈል ብድር ከአበዳሪ ተቋማት በጠቅላላው 6.5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሀብት ተሰባስቦ ለፕሮግራሙ ማስተግበሪያ ይውላል ብለዋል ሚኒስትር ዴኤታው በመግለጫቸው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የዓለም የውሃ ቀን


    Semonegna
    Keymaster

    ዓመታዊው የትምህርት ጉባዔ የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ-ካርታ ዝግጅት ተጠናቆ ለመንግስት ውሳኔ በሚቀርብበት፣ 5ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት መርሃ ግብር የሦስት ዓመት አፈጻጸም የሚዳሰስበት፣ ለቀጣይ ሥራ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ተለይተው አቅጣጫ የሚቀመጥበት ነበር።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ትምህርት ሚኒስቴር የሚያዘጋጀው 28ኛው ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የትምህርት ጉባዔ በትግራይ ብሔራዊ ክልል መቐለ ከተማ ተካሔደ። በየዓመቱ ሚካሄደው እና ከመጋቢት 12 እስከ 13 ቀን 2011 ዓ.ም. በቆየው 28ኛው ሀገር አቀፍ የትምህርት ጉባዔ በተለያዩ የትምህርት ዘርፍ ጉዳዮች ላይ በመምከር ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

    በመድረኩ ከሁለት መቶ በላይ የሚሆኑ ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ፣ ከሁሉም ክልሎችና ከተለያዩ ከተማዎች አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች የተውጣጡ የትምህርት ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለ ድርሻ አካላት እንዲሁም የትምህርት ልማት አጋር አካላት በሀገር አቀፉ የትምህርት ጉባዔ ተሳታፊ ሆነዋል።

    ● SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest

    ዓመታዊ ጉባዔው የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ-ካርታ ዝግጅት ተጠናቆ ለመንግስት ውሳኔ በሚቀርብበት፣ 5ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት መርሃ ግብር የሦስት ዓመት አፈጻጸም የሚዳሰስበት፣ ለቀጣይ ሥራ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ተለይተው አቅጣጫ የሚቀመጥበት ሁነኛ ጉባዔ እንደነበር የትምህርት ሚኒስቴር ዘግቧል።

    በተጨማሪም በአፈፃጸም ሂደት የተገኙ ስኬቶችና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ለአብነት የትምህርት ጥራትና የትምህርት ቤቶች ደረጃ ምደባ ቀርበው በተሳታፊዎች ውይይት እንደተደረገባቸው ታውቋል።

    የዘንድሮውን ትምህርት ጉባዔን ለየት የሚያደርገው ሀገር አቀፍ የተማሪዎች ስፓርት ጨዋታ ጋር አቀናጅቶ እንዲካሄድ መደረጉ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዘግቧል።

    ምንጭ፦ የትምህርት ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የትምህርት ጉባዔ


    Anonymous
    Inactive

    ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ሀገር በቀል እውቀቶችን ከማስቀጠል ረገድ፡
    —–

    የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ሀገር በቀል እውቀቶችን ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ በምርምር የታገዘ ስራ እየሰራ መሆኑን ገለጸ።

    በዩኒቨርሲቲው የገዳና ባህል ጥናት ተቋም /Institute of Culture and Gada Study/ በ30/06/2011ዓ.ም ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከተጋበዙ ምሁራን ፣ አባገዳዎች፣የዩኒቨርሲቲው አመራር እንዲሁም ከአካባቢው ማህበረሰብ የተውጣጡ አካላት በተገኙበት ማዕከሉ በይፋ ተመርቋል::

    በፕሮግራሙ ላይ ጥናታዊ ጸሑፍ ቀርቧል፣ የባህል ስዕል፣ የምግብና የፎቶ አውደ ርኢይ ጉብኝት ተካሄዷል።

    ምንጭ፦ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    Semonegna
    Keymaster

    ከአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ

    የተከበራችሁ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች !!

    አገራችን ኢትዮጵያ 76 ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች የሚኖሩባት ታላቅ አገር ነች። የሕዝባችን አብሮ የመኖር እሴት የሰው ልጆች መደበኛ ማኅበራዊ ግንኙነት ተሻግሮ በደም ዝምድና ተጋምዶ በባህል ተሳስሮ ላይለያይ ተቆራኝቷል። ይህ ህብረት የብሄር ማንነት እና የእምነት ልዩነት ሳይለያየው ለሺህ ዓመታት፣ ሺህ ችግሮችን ተጋፍጦ ይሄው ዛሬም ድረስ በጋራ ዘልቋል።

    የዚህ አኩሪ ታሪክ ጉዞ አልጋ ባልጋ ያልነበረ ከመሆኑ ባሻገር፣ ሕዝባችን የሚያነሳቸው የፍትህ፣ የዴሞክራሲና የልማት ጥያቄዎች በተለያዩ ጊዜያት የነበሩትን መንግሥታት በመታገል ለመብቱ የተከራከረበት ወቅትም በርካታ እንደነበር የሚታወቅ ነው። በተለይም ባለፉት ሦስት ዓመታት በአገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች የተነሱት የፍትህ፣ የዴሞክራሲ፣ የመልካም አስተዳደር፣ የሰብዓዊ መብትና ሌሎች መሠረታዊ ጥያቄዎች ምክንያት በአገሪቱ ለውጥ አንዲመጣ አድርጓል።

    ከለውጡ ማግስት ጀምሮ ኢትዮጵያዊንን እና ሌላውን ዓለም ያስደመሙ በርካታ የለውጥ እርምጃዎች ተወስደዋል። ከተማችንም ዘመን ተሻጋሪና ተጨባጭ ውጤቶች እየተከናወኑና ቀደም ሲል ሕዝባችን ያነሳቸው የነበሩ የፍትህ፣ የዴሞክራሲ፣ የእኩልነት፣ የልማትና መሰል አጀንዳዎች ቅድሚያ ተሰጥቷቸው እንዲመለሱ እየተደረገ ይገኛል።

    በመሪ ድርጅታችን ኢህአዴግ የሚመራው የከተማችን አስተዳደር ሰላም፣ ልማትና ዴሞክራሲ መርሆዎችን ተከትሎ የአዲስ አበባ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ ችግሮችን ለመፍታት ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማካሄድ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸው የከተማው ነዋሪ የሚመሰክረው ሃቅ ነው።

    በሌላ በኩል የከተማችን ነዋሪዎች ሕገ-መንግሥቱ በሰጣቸው ሥልጣን መሠረት በከተማው ሕዝብ ተሳትፎ ወኪሎችን በመምረጥ ሕዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ሥራዎች ተከናውነዋል፤ እየተከናወኑም ይገኛሉ። ይህ ሲባል ሕዝቡ ከአስፈፃሚው አካል ጐን ሆኖ ባያግዝና ባይሳተፍ ኖሮ አሁን የተገኘውን ውጤት ማስመዝገብ አይቻልም ነበር።

    ስለሆነም የከተማችን ነዋሪዎች በሁሉም የሥራ መስኮች ያልተቋረጠ ድጋፍ ያደረገና እያደረገ ያለ ሲሆን በተለይም የአዲስ አበባ ሰላም ተጠብቆ እንዲቀጥል በማድረግ ለሁሉም የአገራችን አካባቢዎች ትልቅ ትልቅ ተምሳሌት ሆኖ ይገኛል። በመሆኑም ሕዝቡ ላበረከተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ምስጋናና ዕውቅና ሊቸረው ይገባል።

    ይሁንና አሁንም በከተማችን የሚስተዋሉና በልዩ ትኩረት ሊፈቱ የሚገባቸው ችግሮች እንዳሉ በመገንዘብ ችግሮችን ለመፍታት የከተማው አስተዳደር ያላሰለሰ ጥረት እያደረገ እንደሆነ እና ምከር ቤቶችም የክትትል ድጋፍና ቁጥጥር ሥራችን አጠናክረን የተጠያቂነት አሠራር በጥብቅ ዲስፒሊን እየተመራ ተግባራዊ አየተደረገ ይገኛል።

    ከምክርቤቱ የምርጫ ዘመንጋር ተያይዞ ለሚነሱ ጥያቄዎች የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መካሄድ የነበረበትን የአዲስ አበባ ከተማ ምርጫ እንዲራዘም በወሰነው መሠረት እና እንዲሁም ሰኔ 30 ቀን 2010 ዓ.ም. የከተማውን አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር 361/1995ን ለማሻሻል ባወጣው አዋጅ ቁጥር 1094/2010 አንቀጽ 2 ንዑስ አንቀጽ 2 መሠረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ጊዜ እንዲራዘም የወሰነ እና “ምርጫ ተደርጐ በምርጫው መሠረት አዲስ አስተዳደር እስኪደራጅ ድረስ በሥራ ላይ ያለው ምክር ቤቱ እና አጠቃላይ የከተማው የአስተዳደሩ በነበረበት ሁኔታ ይቀጥላል” በሚል በደነገገውና በወሰነው ውሳኔ መሠረት ህጋዋ ዕውቅና አግኝቶ የቀጠለ አስተዳደር እንደሆነ ሊታወቅ የሚገባው ሲሆን በዚሁ አዋጅ ቁጥር 1094/2010 አንቀጽ 3 ስር “ምክትል ከንቲባው ከምክር ቤት አባላት ውስጥ ወይም ከምክር ቤት አባላት ውጭ የሚሾም ሆኖ የሥራ ዘመኑ የምክር ቤቱ የሥራ ዘመን ይሆናል”ተብሎ በግልጽ በተደነገገው መሠረት የከተማው ምክር ቤት ሐምሌ 10 ቀን 2010 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ የከተማውን ምክትል ከንቲባ ሹመት በወቅቱ በተገኙት ምክር ቤቱ አባላት በሙሉ ድምፅ አጽድቋል።

    ስለሆነም “የከተማውን ምክትል ከንቲባ ሹመት የነዋሪው ውክልና የለውም” ህጋዊ አይደለም በሚል የሚነሱ የተሳሳቱ አስተሰሰቦች ምንም ዓይነት ህጋዊ መሠረት የሌላቸው እና በስሜት ብቻ የሚንጸባረቁ እንዲሁም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1094/2010 የሚፃረር እና ህገወጥ እንደሆነ ሁሉም የከተማችን ነዋሪ ሊረዳው ይገባል።

    ይሁንና አስተዳደሩ በከተማችን ነዋሪ ተሳትፎ ጭምር በአገር ደረጃ የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ ለማስቀጠል ሌት ተቀን ደፋ ቀና በሚልበትና በዕቅድ ተይዘው እየተተገበሩ ያሉ በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማሳካት እየተረባረበ እና ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበ ባለበት በዚህ ወቅት አንዳንድ ወገኖች በሕግ የተቋቋመውን የአስተዳደሩን ተግባራት በማደናቀፍ የሕዝብ ያልሆኑ ጥያቄዎችን የሕዝብ በማስመሰል ሲንቀሳቀሱ ይስተዋላል።

    ስለሆነም በአገራችን ብሎም በከተማችን የመጣውን ለውጥ ለማደናቀፍ በቅርቡ በከተማችን ሰላምን ለማደፍረስ እየታዩ ያሉ ኢ-ሕገመንግሥታዊ እንቅስቃሴዎችን በትኩረት በመከታተልና ሕገወጥ እንቅስቃሴ አድራጊዎችን በሰላማዊ መንገድ በመታገል የከተማችን ነዋሪዎች እንደወትሮው ሁሉ የከተማችንን ሰላም በማስከበር የተጀመረውን ልማት በማስቀጠል የበኩሉን አስተዋጽኦ በማድረግ ከከተማው አስተዳደር ጐን እንደሚቆም ያለንን ጽኑ እምነት እየገለጽን፡-

    1ኛ. ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጋጩ፣ ከአንድነት ይልቅ ልዩነትን የሚያራግቡ፣ በህጋዊ መንገድ በተመረጠው አስተዳደር ላይ አመጽ የሚያነሳሱ ማናቸውም ድርጊቶች ለማንም የማይጠቅም ህገወጥ ድርጊት እና ፀረ-ህገመንግሥትም ስለሆነ ባስቸኳይ እንዲቆም፤

    2ኛ. አሁን ያለው የከተማው አስተዳደር ህጋዊ መሠረት ያለው እና በም/ቤቱ ፀድቆ የተሾሙ በመሆኑ መላው የከተማው ነዋሪዎች ከከተማው አስተዳደር ጐን በመቆም በከተማችን ነዋሪዎች ድምፅ ውክልና የተሰጠውን ም/ቤት ሥልጣን ወደጐን በመተው እየተነሱ ያሉ የማደናገሪያ አስተሳሰቦችን አምርሮ እንዲታገል፤

    3ኛ. በከተማችን ውስጥ የላቀ ልማት ለማስመዝገብ፣ ዘላቂ ሰላምና ዋስትና ያለው ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ለማድረግ የሁሉም ወገኖች የጋራ ጥረትን የሚጠይቅ በመሆኑ ለውጡን ባስተማማኝ ሁኔታ ለማስቀጠል የከተማችን ነዋሪዎች ሁሉን አቀፍ ትብብር እንዲያደርጉ እና ከከተማው አስተዳደር ጐን እንዲቆሙ ጥሪ እያቀረብን፣ የብሄርብሄረሰቦችና ሕዝቦች የቃልኪዳን ሠነድ እና የህጐች ሁሉ የበላይ የሆነውን ሕገመንግሥት የማክበር፣ የማስከበርና የመጠበቅ ኃላፊነታችሁን በመወጣት ሕዝቡን በማደናገር የከተማችንን ሰላም ለማደፍረስ ሌት ተቀን የሚጥሩ ኃይሎችን በመታገል ከከተማ አስተዳደሩና ከምክርቤቱ ጐን በመሆን የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታደርጉ፤

    4ኛ. የአዲስ አበባ ጉዳይን በተመለከተ ከተማችን የሁሉም ብሄር ብሄረሰቦችና ሕዝቦች በፍቅር፣ በመተሳሰብና በመቻቻል በአብሮነት ለሰላም ልማትና ዴሞክራሲ ዘብ የቆመ ሕዝብ የሚኖርባት የሁላችንም ከተማ የአፍሪካ መዲና፣ የዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶች መኖሪያ መሆንዋ ታውቆ ከከተማው ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጥያቄዎች የሕጐች ሁሉ የበላይ በሆነው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሕገ-መንግሥት ምላሽ የሚያገኝ ስለሆነ ፍጸም የግጭት መንስኤ መሆን አይገባውም፤

    5ኛ. የከተማው አስተዳደር እንደሌላው ጊዜ ሁሉ የከተማውን ሰላምና ፀጥታ ከማስከበር ባሻገር እያከናወነ ያላቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ፕሮግራሞችን አጠናክሮ እንዲቀጥል እያሳሰብን፣ እንደወትሮው ሁሉ የከተማችን ነዋሪዎችም ህግና ሥርዓት እንዲከበርከ አስተዳደሩ፣ ከሕግ እና የፀጥታ አስከባሪ አካላት ጐን በመሆን ለሰላም ዘብ በመቆም የተለመደው ትብብሩን እንዲቀጥል እንጠይቃለን።

    እናመሰግናለን!

    ወ/ሮ አበበች ነጋሽ
    የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ
    አዲስ አበባ
    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት


    Semonegna
    Keymaster

    አዎ አገር እንደ እንደ ካልጠነከረች በመርፌ ስለት በቻ ሳይሆን በዶለዶመ ብረትም ትበሳለች። የመርፌ አቅሙ ጨርቅ ወይም እንደ ጨርቅ በሳሳ ነገር ላይ ነው። ኢትዮጵያ አገራችን ደግሞ ከመቼውም በከፋ ሁኔታ ሳስታለች።

    ያሬድ ኃይለማርያም

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በትላንትናው እለት የማኅበራዊ ሚዲያዎችን አጠቃቀም በተመለከተ ምክር አዘል ተግሳጽ የያዘ ደብዳቤ ከጽሕፈት ቤታቸው ለሕዝብ ይፋ አድርገዋል። እርግጥ ነው ጠቅላዩ እንዳሉት ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚተላለፉ ጽንፍ የያዙ እሰጣገባዎች፣ በማንነት ላይ ያነጣጠሩ ጸያፍ ንግግሮች፣ ሕዝብን ለግጭት የሚቀሰቅሱ ጥሪዎች፣ የሃሰት መረጃዎች እና ውንጀላዎች ከመቼው ጊዜ በስፋት እየተስተዋሉ መጥቷል። ይህ ዓይነቱ ችግር በጊዜ ካልታረመ የእርስ በርስ ንቁሪያው ከማኅበራዊ ሚዲያ ወደ መሬት ወርዶ በግልም ሆነ በአገር ደረጃ ዋጋ እንደሚያስከፍለን ደብዳቤያቸው በግልጽ አስቀምጦታል።

    ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ሚዲያዎች ጽንፍ ይዘው እና የተሳሳቱ መረጃዎችን እያሰራጩ ሕዝብን የሚያደናግሩ እና ለግጭት የሚያነሳሱ ሰዎችን በመርፌ መስለው አስቀምጠዋል። እንዲህም ይላሉ “መርፌ ዓይናማ ናት ባለ ስለት፤ ችግሩ የፊቷን እንጂ የሚከተላትን አታይም። እናም ጨርቅ ላይ እሷ አለፍኩ ብላ የክር እና የገመድ መአት ታስገባበታለች። የእኛ አገር አንዳንድ የማኅበራዊ ድረ-ገጽ ጦማሪዎች ልክ እንደ መርፌ ናቸው። እነሱ አገር በሚወጋ መርፌያቸው እየወጉን ሲጓዙ እንደ ክር አያሌዎች መድረሻቸውን ሳይጠይቁ ይከተሏቸዋል…” አገላለጻቸው ግሩም ነው። ወድጄዋለሁም፤ ነገር ግን እውነቶች ይጎድሉታል።

    ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሁኔታውን አንድ ገጽታ ብቻ ነው እንደ ዋነኛ ምክንያት ወስደው እና አትኩሮት ሰጥተው ስጋታቸውንና ማሳሰቢያቸውን የሰጡት። እኔ ያላዩት ወይም ችላ ብለው ያለፉት ገጽታ አለ እላለሁ። መርፌ ጨርቅ እንጂ አለት አትሰፋም ወይም አይበሳም።

    አዎ አገር እንደ እንደ ካልጠነከረች በመርፌ ስለት በቻ ሳይሆን በዶለዶመ ብረትም ትበሳለች። የመርፌ አቅሙ ጨርቅ ወይም እንደ ጨርቅ በሳሳ ነገር ላይ ነው። አገራችን ደግሞ ከመቼውም በከፋ ሁኔታ ሳስታለች።

    አገር እንደ አለት የሚጸናው በጥሩ ሕግ፣ የሕግ የበላይነትን በሚያረጋግጡ ጠንካራ ተቋማት፣ ሕግን በሚያከብሩ እና በሚያስከብሩ የመንግስት ተቋማት እና ሕግ አክባሪ በሆነ ማኅበረሰብ ነው።

    በሁሉም አለም ማኅበራዊ ሚዲያዎች ጥሩም፣ መጥፎም ገጽታ አላቸው። የሕግ የበላይነት በሳሳበት እና መንግስት ሕግ የማስከበር ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት ባልቻለበት ስፍራ አሉታዊ ጎኑ ይበረታና አገር እሰከ ማተራመስ አልፎም እስከ ማፍረስ ይደርሳል። በሕግ የጸና ጠንካራ አገር እና ሕግ አክባሪ ማብሀረሰብ ባለበት አገር ደግሞ የማኅበራዊ ሚዲያዎች ጩኸት ሰሚ አልባ ነው። እዛው አየር ላይ ተንሳፎ ይቀራል።

    ክቡርነትዎ፥ የእኛ አገር የማኅበራዊ ድረ-ገጾች መረን የለቀቀ የእርስ በርስ ንቁሪያ እኮ መሬት ላይ ያለው እውነታ ነጸብራቅ ነው። እርሶ በተቀመጡባት መዲና አዲስ አበባ ሳይቀር ሰዎች ሜጫ፣ ድንጋይ፣ ሚስማር የተመታበት ዱላ ይዘው አደባባይ ለፍልሚያ በየቀኑ በሚወጡበት እና ዜጎች በሰላም ወጥቶ በሰላም መግባት የማይችሉበት አደጋ መሬት ላይ እየታየ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ያለው ጦርነት እንብዛም ትኩረት ሊስብ አይገባውም።

    አገሪቱን እንደ ጨርቅ ያሳሳት እንደ እኔ እምነት የመርፌው ጥንካሬ ሳይሆን መንግስት የሕግ የበላይነትን በመላ አገሪቱ ማስፈን አለመቻል ነው። እባክዎ ቅድሚያ አየር ላይ ካለው የቃላት ጦርነት በፊት መሬት ላይ ሕግ ያስከብሩ። የእርሶ ጽሕፈት ቤትም አይደል እንዴ በአደባባይ እና በማኅበራዊ ሚዲያ በሕዝብ ላይ የእልቂት እና የግጭት አዋጅ አውጆ ለቄሮ የክተት ጥሪ ያደረገውን ጃዋር መሃመድን በሕግ ተጠያቂ ከማድረግ ይልቅ በቅርቡ በኢሲኤ (ECA) አዳራሽ ባዘጋጁት የውይይት መድረክ ላይ በአገሪቱ የመገናኛ ብዙሃን አጠቃቀምን አስመልክቶ ትምህርት እንዲሰጥ ዋና ተናጋሪ አድርጎ ያቀረበው።

    ማኅበራዊ ሚዲያው ላይ ያሉት ችግሮች እና ስጋትዎን እኔም ሙሉ በሙሉ እጋራዎታለው። ጽንፈኝነት ነግሷል። የሃሰት መረጃዎች ሕዝብን እያደናገሩ ነው። እኔም ሆንኩ ሌሎች ሚዲያውን የሚጠቀሙ አካላት እርሶንም ጨምሮ ለችግሩ አስተዋጽኦ ይኖረን ይሆናል። ይህ ችግር አገር ሳያሳጣን በፊት በአግባቡ እና በአፋጣኝ ሊፈታ ይገባል። ኢትዮጵያን እንደ አለት የጸናች አገር ማደረግ ከቻልን ግን የማኅበራዊ ሚዲያው ጩኸትም ሆነ ትርምስ ንፋስ ይወስደዋል ወይም እየነጠረ ይመለሳል እንጂ አገር አያፈርስም።

    አዎ እርሶ እንዳሉት ኢትዮጵያ ጽኑ መሠረት ያላት አገር ስለሆነች በማኅበራዊ ሚዲያ ወሬ አትፈርስም። መሬት ላይ ያለው ሕግ አልባነት፣ የመንጋ እንቅስቃሴ እና በሕግ ያልተገራና ልቅ የሆነ የግለሰቦች እና የፓርቲዎች እንቅስቃሴ ግን የሞት አፋፍ ሊያደርሳት ይችላል።

    የሕግ የበላይነት ትኩረት ይሰጠው!

    ያሬድ ኃይለማርያም / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 

    መርፌ ጨርቅ እንጂ አለት አይበሳም


    Semonegna
    Keymaster

    “የሠራዊቱ ሁኔታ ከፍተኛ የህሊና መረበሽ ውስጥ ከቶኛል” አቶ ነአምን ዘለቀ
    —–

    ላለፉት 26 ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ ሲያደርጉ የቆዩት የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ከፍተኛ አመራርና ሥራ አስፈጻሚ አባል አቶ ነአምን ዘለቀ ከፓርቲ መልቀቃቸውን ተከትሎ ከቢቢሲ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

    ቢቢሲ፡ የአርበኞች ግንቦት 7 የሠራዊ አባላት አሁን ያሉበት ሁኔታ ትንሽ ያስጨነቀዎት ይመስላል። ግን ደግሞ ለመልቀቅ ከወሰኑ ቆይተዋል፤ እርስዎም በጽሑፍዎ እንደጠቀሱት። እና ዝም ብሎ ከመውጣት፣ መልቀቅዎን ከአንድ ጉዳይ ጋ ሆን ብለው ለማያያዝ የሞከሩ ይመስላል።

    አቶ ነአምን፡ (ዘለግ ካለ ሳቅ በኋላ) ምን እላለሁ እንግዲህ። አንተ የመሰልህን (ማሰብ ትችላለህ). . .። መጀመሪያ (ከጽሑፌ) አንተ ይሄን ብቻ ነጥለህ ለምን እንዳወጣኽው አላወቅኩም። እዚያ ላይ ሠራዊቱን በሚመለከት የተደረገው ጥረት በዝርዝር ተቀምጧል። እስካሁን ድረስ እነኚህ የሠራዊት አባላት በከፍተኛ ችግር ላይ ነው ያሉት፤ ላለፉት ሰባት ወራት።

    መንግሥት የእነርሱን ጉዳይ በተደረገው ስምምነት መሠረት (ማለትም) ቶሎ በሁለትና በሦስት ወር ውስጥ መልሰው ይቋቋማሉ፣ ድጎማ ይሰጣቸዋል አለ፤ የጀርመን መንግሥት ገንዘብ ለመስጠት ቃል ገባ፤ ነገር ግን በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት የተቋቋመው ቢሮ ምንም አቅም ስላልነበረው እስካሁን ድረስ ሲጓተት ቆይቶ አሁን ገና ወደ ኮሚሽን ጉዳዩ ተመርቶ ያው ኮሚሽኑ ኃላፊነት ተሰጥቶት በብሔራዊ አደጋ መከላከል ኮሚሽን በኩል የእነርሱ ጉዳይ እንዲካሄድ ነው እየተደረገ ያለው።

    ቢቢሲ፡ ለመሆኑ የሠራዊቱን አባላት በአካል አግኝተዋቸዋል?

    ሙሉውን ቢቢሲ አማርኛ ላይ ያንብቡ

    Semonegna
    Keymaster

    የሕክምና መሣሪያዎችን በሀገር ውስጥ ለማምረት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ
    —–

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የሕክምና መሣሪያዎችን በሀገር ውስጥ ለማምረት የሚያስችል ስምምነት መጋቢት 10 ቀን 2011 ዓ.ም. ተፈረመ።
    ስምምነቱ በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ሚኒስቴር፣ በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ፥ በጤና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን መካከል ነው የተፈረመው።
    ስምምነቱ በሀገሪቱ ያለውን የሕክምና መሳሪዎችን ፍላጎት ለማሟላትና ለግዢ የሚወጣውን የውጪ ምንዛሪ ለመቀነስ ያስችላል።

    ምንጭ፦ የጤና ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

Viewing 15 results - 496 through 510 (of 730 total)