Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Home Forums Search Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Viewing 15 results - 511 through 525 (of 730 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኪነ-ሕንፃ (አርክቴክቸር) ትምህርት ክፍል ዘንድሮ ተማሪዎች ሲያስመርቅ ሦስተኛው ሲሆን፥ 22 ወንዶች እና 7 ሴቶች በድምሩ 29 ተማሪዎች ለምረቃ በቅተዋል።

    ባህር ዳር (ሰሞነኛ)– ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የመሬት አስተዳደር ኢንስቲትዩት ስር የሚገኘው የኪነ-ሕንፃ (አርክቴክቸር) ትምህርት ክፍል ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ለሶስተኛ ጊዜ አስመረቀ።

    የዩኒቨርሲቲው መሬት አስተዳደር ዳይሬክተር ዶ/ር በላቸው ይርሳው ዓለሙ ለተመራቂ ተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት ተመራቂዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያገኙትን የቀለም እና የተግባር ትምህርት ወደ ተግባር የሚተረጉሙበት እና ከራሳችው አልፎ ህብረተሰባቸውን የሚያገለግሉበት ጥሩ አጋጣሚ በመሆኑ በከፍተኛ ኃላፊነት ስሜት እንዲሠሩ ይጠበቃል ብለዋል። የኪነ-ሕንፃ ትምህርት ትዕግስት እና ፈጠራ የሚጠይቅ በመሆኑ ተመራቂ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያሳደጉትን የፈጠራ ክህሎት የበለጠ አጎልብተው እራሳቸውን ጠቅመው ማኅበረሰቡን እንዲያገለግሉበት አሳስበዋል።

    ዶ/ር በላቸው አክለውም የኪነ-ሕንፃን ሙያ የሚጠይቅ ሥራ የሚሠሩ የፌዴራል፣ የክልል የግልም ሆነ የመንግስት መሥሪያ ቤቶች ከፍተኛ ሃብት እና ዕውቀት ፈሶባቸው የሰለጠኑ ተመራቂዎችን በአግባቡ ሊጠቀሙባቸው ይገባል ብለዋል።

    ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዶክተሮችን አስመረቀ

    የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ እንደተናገሩት፥ የሚገነቡት ከተሞች ብሎም አገራት የሚመስሉት የኪነ-ሕንፃ ባለሙያዎችን በመሆኑ ለከተሞች ውበት፣ የኑሮ ምቹነት፣ ቀጣይነት፣ ወጭ ቆጣቢነት የራሳቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ፕሬዝዳንቱ ቀጥለውም አሁን ትልቅ የኪነ-ሕንፃ ጥበብ የሚታይባቸው የአገራችን ቅርሶች የመፈራረስ አደጋ የተጋረጠባቸው ጊዜ ሲሆን መታደግ የሚቻለውም በዕውቀት እና በጥበብ በመሆኑ ተመራቂዎች ያላቸውን ዕውቀት እና ጥበብ በተቋርቋሪነት መንፈስ በመጠቀም ከመፍረስ እንዲታደጓቸው አሳስበዋል።

    ዶ/ር ፍሬው ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት፥ ተመራቂ ተማሪዎች የኢትዮጵያን ቅርሶች፣ መልክዓ-ምድሮች፣ እንስሳት፣ እጽዋት እና ሌሎች የተፈጥሮ ሃብቶች ሌሎች የሌሏቸው መለዮወቻችንን የንድፋቸው ማስጌጫ መጠበቢያ ቅመም በማድረግ እንዲጠቀሙባቸው አሳስበው ዓለም ከደረሰበት እድገት አንጻርም ዘመኑን የዋጀ ንድፍ መሥራት እንደሚገባቸው ተናግረው፤ ከሁሉም በፊት ግን ህሊናቸውን እና ፈጣሪያቸውን ዳኛ አድርገው የሙያ ሥነ-ምግባር በተላበሰ መልኩ እንዲሠሩ በአጽንኦት መክረዋል። በመጨረሻም ተመራቂዎች በሙያቸው ስኬታማ በመሆን የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲን ብሎም የውድ አገራቸውን ስም የበለጠ በበጎ እንዲታወቁ የበኪላቸውን ያደርጉ ዘንድ አደራ ብለዋል ።

    በምረቃ በርሃግብሩ የተገኙት አርክቴክት አበበ ይመኑ የረዥም ጊዜ የህይወት ተሞክሯቸውን እና የሥራ ልምዳቸውን ለተመራቂዎች ያቀረቡ ሲሆን፥ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በትምህርት ክፍል ደረጃ የሚሠሩት የተማሪዎች ፕሮጀክቶች ደረጃቸው ከፍ እንዲል መሠራት እንዳለበት ጠቁመው፥ በተጨማሪም በሙያው ትልቅ ስም ያላቸው አርክቴክቶች ያላቸውን የሥራ ልምድ፣ የፈጠራ ችሎታቸውንና ክህሎት ማካፈል የሚችሉበት መርሃግብር ቢዘጋጅ ጥሩ እንደሆነ ተናግረዋል። አቶ አበበ ይመኑ በመጨረሻም የኪነ-ሕንፃ ትምህርት በባህሪው የተለየ ክህሎት እና የተለየ ከባቢያዊ ሁኔታ የሚፈልግ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል።

    በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ከፍተኛ ውጤት ላመጡ እና ከ1ኛ-5ኛ ለወጡ ተማሪዎች ሽልማት ተስጥቷል። ከሴቶች ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበችው ተማሪ ቃልኪዳን ጥበቡ እንዲሁ ሽልማት የወሰደች ሲሆን ተማሪ በረከት ምትኩ 3.76 በማምጣት የከፍተኛ ማዕረግ የወርቅ ተሸላሚ ሆኗል።

    የዘንድሮው ምርቃት በትምህርት ክፍሉ ሦስተኛው ሲሆን 22 ወንዶች እና 7 ሴቶች በድምሩ 29 ተማሪዎች ለምረቃ በቅተዋል። በዕለቱ በተማሪዎቹ የተሠሩ የኪነ-ሕንፃ ንድፎች አውደ ርዕይ በመርሃ ግብሩ ለተገኙ ተሳታፊዎች እና ተመራቂ ቤተሰቦች ተጎብኝተዋል።

    ምንጭ፦ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኪነ-ሕንፃ ትምህርት ክፍል


    Semonegna
    Keymaster

    ግልጽ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ሕዝብ በአቶ ነአምን ዘለቀ ― አቶ ነአምን ዘለቀ ራሳቸውን ከአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ አገለሉ
    ———

    ለአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ አባላት፣ የሠራዊት አባላት፣ ደጋፊዎችና፣ በልዩ ልዩ መደረኮች ለምታውቁኝ ኢትዮጵያውያን በሙሉ፦

    በሀገራችን የመጣውን ለውጥ ተከትሎ የአርበኞች ግንቦት 7 የዴሞክራሲና የአንድነት ንቅናቄ (አግ7) አመራር አባላት እ.ኤ.አ. በሀምሌ (July) ወር 2018 በአሜሪካን ሀገር ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር በተደረገ ስብሰባ ላይ ከተደረሱት የስምምነት ነጥቦች መካከል አንዱ የአግ7 ንቅናቄ ሠራዊት ከኤርትራ በርሃና ከሀገር ውስጥም የነበሩት የአግ7 ታጣቂዎች ወደ ሀገር ወደ ሰላማዊ ኑሮ መመለስና ማቋቋምን የሚመለከት ነበር። በዚህም መሠረት በኤርትራ የነበሩ የንቅናቄው ሠራዊት አባላት እንዲሁም በየበረሃው የነበሩ የንቅናቄው ታጣቂዎች ወደ ልዩ ልዩ ካምፖች በየጊዜው እንዲገቡ መደረጉ ይታወቃል። በብዙ መቶ የሚቆጠሩ የንቅናቄው አባላትም ከልዩ ልዩ እስር ቤቶች ቀደም ሲል በተከታታይም እንደተለቀቁ ይታወቃል። በኃላፊነት ስመራ በቆየሁት በውጪው ዘርፍ ስር የማኅበራዊ ፈንድ ኮሚቴ እንዲቋቋም በማድረግ በውጭው ዓለም በሚገኙ በንቅናቄው አባላት፣ በደጋፊዎች፣ እንዲሁም አገር ወዳዶች ትብብር መጠነ ሰፊ ገንዘብ በማሰባሰብ በየእስር ቤቱ የነበሩት ተጋዮች ለሦስት ተከታታይ ወራት እንዲረዱ እንዲሁም ከኤርትራ በረሃ ለመጡትና በካምፕና ከካምፕ ውጭ ለሚገኙትም በልዩ ልዩ መንገዶች እርዳታዎች እንዲያገኙ ለማድረግ ተችሏል።

    ከኤርትራ በረሃ ወደ አገር ቤት እንዲገቡ የተደረጉትን የአርበኞች ግንቦት 7 የቀድሞ ታጣቂዎች እንዲሁም የሌሎች የፓለቲካ ድርጅቶች ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋሚያ ፕሮጄክት ጽ/ቤት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ስር ከ7 ወራት በፊት የተመሠረተ ሲሆን፥ የውጭ መንግስታትም በተለይም የጀርመን መንግስት ለዚሁ የሚውል ገንዘብ ለመስጠት ከበርካታ ወራት በፊት ተስማምተው ነበር። ሆኖም ከተቋቋመው ጽ/ቤት አቅም ማነስ እንዲሁም ጉዳዩ ተገቢውን ውሳኔዎች ሳያገኝ እየተጓተተ በመቆየቱ ሳቢያ የአርበኞች ግንቦት 7 ሠራዊት አባላት (በተለይም ከካምፕ ውጪ እንዲቆዩ ተደርገው መልሶ የማቋቋሚያ ድጋፍ እንዲጠብቁ የተነገራቸው ጭምር) ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸው ለህሊና እረፍት በሚነሳ ሁኔታ ውስጥ እራሴን አግኝቼ ነበር።

    የንቅናቄው ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እንዲሁም ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ችግሩ መፍትሄ እንዲያገኝ በየጊዜው ከጠቅላይ ሚንስትሩና ከሌሎች የመንግስት ኃላፊዎች ጋር የሚያደርጉት ግንኙነትና ክትትል እንደተጠበቀ ሆኖ፤ በችግር ላይ የነበሩ የሠራዊት አባላት ሁኔታ አየተደራረበ የጭንቀት ድምጾች እየተበራከቱ በመምጣታቸው፣ ይህ ጉዳይ የንቅናቄውን ሊቀመንበርና ዋና ጸሐፊውን ብቻ የሚመለከት ሳይሆን አባላትና ሠራዊቱ የመረጡን የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን በሙሉ በተናጠልም ሆነ በጋራ የሚያስጠይቅ፣ ለሠራዊቱም ሆነ ለአባላት ኃላፊነት አለብን በሚል መንፈስ ይህ ለውጡን ለሚመራው መንግስትም የጸጥታና የፓለቲካ ችግር የሚፈጥር ሁኔታ፣ ከሞራልም ሆነ ከፓለቲካ እኳያ የንቅናቄውንም ውስጣዊ ጤንነት እየተፈታተነ የነበረ ትልቅ ችግር እየሆነ በመምጣቱ፣ ለችግሩ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ እርዳታ ለመስጠት ቃል ከገቡና ለመርዳት ፈቃደኛ ከሁኑ መንግስታት በተለይም ከጀርመን አምባሳደር፣ ከስዊድን መንግስት ኃላፊዎችና የፓርላማ አባላት፣ ከልዩ ልዩ የመንግስት ኃላፊዎችና ከመንግስት መዋቅር ውጭ የሚገኙ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሚቀርቡ ግለሰቦች ጋር በመገናኘት ለማስረዳትና መፍትሄ እንዲያገኝ የበኩሌን አስተዋጽዖ ለማድረግ ጥረቶች ሳደርግ ቆይቻለሁ።

    ብዙ ዝርዝሮች ያሉትና ወራት ያስቆጠረ ሂደት ቢሆንም፣ በዚህ አጋጣሚ ለዚህ ችግር መፍትሄ በማፈላለግ ሊያዳምጡን በራቸውን ለከፈቱ የልዩ ልዩ የመንግስት ተቋማት ኃላፊዎች፣ በተለይም የብሄራዊ አደጋና መከላከል ኮሚሽነር ምትኩ ካሳ፣ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ፣ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት አማካሪ አምባሳደር ግርማ ብሩ፣ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ አቶ ብርሃኑ ጸጋዬ፣ እንዲሁም ከመንግስት መዋቅር ውጭ ያሉና ከለውጡ በኋላ ከጠቅላይ ሚንስትሩ ሊያገኙን እንደሚፈልጉ በላለቤቴ በኩል መልክት የላኩብኝ የጠቅላይ ሚኒስሩ የአርቅ ኮሚቴ አባል አቶ ብርሃን ተድላ፣ በበርካታ የሕዝብና የሀገር ጉዳዮች ያላሰለሰ አስተዋጽኦ የሚያደርጉትና የረጅም ጊዜ ወዳጄ ለሆኑት ዶ/ር አምባሳደር ካሳ ከበደ፣ በጉዳዩ ላይ ትኩረት ሰጥተው ለመርዳት ለተንቀሳቀሱት፣ በእርዳታና በመልሶ ማቋቋም ከፍተኛ ልምድና ዕውቀት ያላቸው ለሻለቃ ዳዊት ወልደ ጊዮርጊስ፣ እንዲሁም ለመለሶ ማቋቋም የተቋቋመው መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ኣፍሪድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቴዎድሮስ ይልማ፣ ሌሎችም ለችግሩ መፍሄ ለማግኘት ያገኘኋቸውን ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ሁሉ እስከአሁኑ ቀን ድረስ ለከፍተኛ ችግር ተዳርገው በሚገኙት የሠራዊት አባላት ስም ምስጋና ሳላቀርብ አላልፍም፡፡ በአንጻሩ ደግሞ ትላንት ከለውጡ በፊት እንኳን እነሱን ደጅ ልንጠና ቀርቶ አጠገባቸው ለመድረስ እንኳን የምንጸየፋቸው፣ የተቀመጡበት የኃላፊነትና የአማካሪነት ቦታ የሀገርና የህዝብ ችግሮች ለመፍታት መሆኑ እምብዛም የሚያስጨንቃቸው የማይመስሉ፣ ራሳቸውን የኮፈሱ አድርባዮች፣ ከንቱና ግብዝ የመንግስት ባለሟሎች በዚህ ሂደት ለመታዘብ ችያለሁ።

    የሆነ ሆነ ይህ ከፍተኛ ችግር መፍትሄ እንዲያገኝና በውጭ የሚገኙትም ሆኑ በካምፕ ውስጥ የሚገኙት የንቅናቄያችን ሠራዊት አባላት ቢያንስ አቅም ባለው፣ ሠራዊቱ የሚገኝበትን ችግር ለማቃለል ብቃትና ተቋማዊ ቁመና ለዓመታት ባካበተ የመንግስት ኮሚሽን በኩል እንዲሆን የሚያስችል እርምጃ እንዲወሰድ በቅርብ ቀን መወሰኑን አዲስ አበባ በነበሩኩባቸው አራት ሳምንታት ከሚመለከታቸው የመንግስት ኃላፊዎች ጋር በተደረገ ውይይት አረጋግጫለሁ። ይህም እርምጃ ለወራት የቆየን ከባድ የህሊና ሸክም ያቃለለ ቢሆንም፣ አሁንም ከካምፕ ውጭ የሚገኙ የሠራዊቱ አባላት የሚገኙበትን ዘርፈ ብዙ ማኅበራዊ ችግሮች አስመልክቶ በየዕለቱ በርካታ መረጃዎች እየደረሰን በመሆኑ ከካምፕ ውጭም ሆነ ከካምፕ ውስጥ የሠራዊቱ አባላት ቃል የተገባላቸው እርዳታ እንዲደርሳቸው፣ የመልሶ ማቋቋሙ ሂደት በቶሎ እንዲጀመር፣ የንቅናቄው የሥራ አፈጻሚ ኮሜቴ እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት ኃላፊዎች የሚያስፈልገው ያልተቋረጠ ትኩረትና ክትትል እንዲያደርጉ በድጋሚ ለማሳሰብ እወዳለሁ።

    ሀገራችን ኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ ተግዳሮቶችና ህልውናዋን የሚፈታተኑ ስጋቶች የተጋረጡባት ከመሆኗም በሻገር ከምንጊዜውም በባሰ መልኩ መስቀለኛ መንገድ ላይ የምትገኝ መሆኑን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ሁሉ የሚስማሙ ይመሰለኛል። ይህን አደጋ ለመቋቋም ደግሞ በርካታና ዘርፈ ብዙ ሕዝብ አቀፍ እንቅስቃሴዎች ያስፈልጋሉ። ስለዚህም ውስብስብ በሆኑና ስር በሰደዱ መጠነ ሰፊ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፓለቲካዊ ችግሮች አውድና ከባቢ ውስጥ ተዘፍቀው ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ፣ ፍትህና፣ የሕግ የበላይነትን ለማስፈን እየተደረገ በሚገኘው የለውጥ ጅማሮ እንዳይቀለበስ የለውጡን አራማጆች፣ ለውጡን ለማስቀጠል በተጨባጭ እርምጃዎች እስከተንቀሳቀሱ ድረስ ማገዝ አማራጭ የሌለው ነው ብዬ አምናለሁ።

    ሀገራችንን ቅርጫ ለማድረግ ሲሉ የ100 ሚሊዮን ህዝብ ዕጣ ፈንታ ላይ ቁማር የሚጫወቱ፣ የሕዝብን የተሻለ ህይወት፣ ለሁሉም የኢትዮጵያ ልጆች የታገሉለትን፣ የሚመኙትን ፍትህ፣ ነጻነትና የነገን ተስፋ እየረጋገጡ የሚገኙ እጅግ ራስ ወዳድ፣ ስግብግብ ህሊና ቢሶች፣ የኢትዮጵያን ልዩ ልዩ ማኅበረሶቦች አብሮነት አጥፍተው ለራሳቸው ጠባብ ብሄረተኝነት እጀንዳ ጥቅምና ስልጣን ለማምጣትም ሆነ ለማስቀጠል በየአካባቢው ትርምስ የሚፈጥሩ፣ ክቡር የሆነውን ሰብዓዊነት ረግጠው ወደ አራዊትነት በተጠጋ የለየለት ጽንፈኝነትና አክራሪነት የታወሩ ጥቂቶች፣ ከራሳቸው ግላዊ ፍላጎትና ጥቅም ውጭ ለሕዝብና የሀገር ደህንነት፣ ለሰላም፣ ለፍትህና፡ ለሕግ የበላይነት ምንም ቁብ የማይሰጡ የጥፋት ኃይሎች በአብዛኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች እንደአሸን በፈሉበት ሁኔታ ከኢትዮጵያዊነት ውጪ፣ ከፍትህ፡ ከእኩልነትና፣ ከሕዝብ አብሮነት የተለየ ሌላ አማራጭ እንደሌለ፣ ሌላ ሀገር፣ ሌላ ምድርም አለመኖሩን በሚገባ የተረዱ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ሁሉ በየአካባቢያቸው እያፈጠጠ፣ እያገጠጠ ከሚገኘውን የህልውና አደጋ ከእነዚህ አክራሪና ጽንፈኛ የጥፋት ኃይሎች ሊያመጡት ከሚችሉት የሀገራችንን የመኖር አለመኖር ህልውና የሚፈታተን የሲኦል ጎዳና ራሳቸውን፣ ቤተስባቸውንም ለመከላከል፣ ተከላካይ በሆነ መልኩ እርስ በእርስ መደራጀት፣ እንዲሁም ራስን በራስ ማደራጀትና፣ ብሎም ነቅቶ መጠበቅ ሌላው አስፈላጊና ወቅታዊ ተግባር ነው ብዬ አምናለሁ።

    ለአገራችን ሕልውና፣ ለሕዝባችን ሰላም፣ ፍትሕና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የሰፈነባት ኢትዮጵያ እንድትኖር የሚያስችል የፓለቲካ ስርዓት እንዲረጋገጥ የሚጨነቁ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እልህ አስጨራሽ ሁኔታ ውስጥ ብንገኝም ከዚህም ከዚያም የሀገሪቱን ህልውና አደጋ ላይ እየጣሉ የሚገኙ አክራሪና ጽንፈኛ ብሄረተኞችና የለውጥ ቅልበሳ ቡድኖች ወጥመድ ሰላባ ላለመሆን በስልት፣ በሰከነ ጥበብና በሃገራዊ ኃላፊነት መንቀሳቀስ የግድ ነው ብዬ አምናለሁ። ለኢትዮጵያዊነት፣ ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን ዜጎች እኩልነትና ሁለንተናዊ መብቶች የቆሙ የፓለቲካ ኃይሎች፣ የሲቪክ ተቋማት፣ እንዲሁም የፕሬስ ድርጅቶችን ማጠናከር እንዲሁ ሌላቅ የወቅቱ ዐቢይ ተግባራት ይመስሉኛል።

    በሀገራችን የተጀመረው ለውጥ ከመጣ ከጥቂት ወራት በኋላ ንቅናቄው የፓለቲካ ፓርቲ እንደሚሆን ስምምነት በተደረሰ ጊዜ የፓለቲካ ፓርቲ አመራርም ሆነ አባል ሆኜ ለመቀጠል ፍላጎት እንደሌለኝ በአመራሩ ላይ ለሚገኙ ሁሉ በተለያዩ ጊዜያት ገልጬ ነበር። እስካሁንም ድረስ የቆየሁት ከመሪዎች አንዱ ሆኜ እንዳገለግል ለመረጡኝ አባላትና የሠራዊት አባላት ባለኝ ኃላፊነትና ተጠያቂነት ቢያንስ ከኤርትራ በርሃና በኢትዮጵያም ውስጥ ሆነው በጨለማው ዘመን ለኢትዮጵያ አንድነትና ለሕዝብችን ነጻነት ህይወታቸውን ለመገበር ለቆረጡ እነዚህ ዛሬ በካምፕ ውስጥና ከካምፕ ውጭ የሚገኙ የሠራዊት አባላትና ታጋዮች ህይወት ተገቢውን መስመር እስኪይዝ ነበር።

    ቀደም ሲል መልቀቂያ አስገብቸ የነበረ ቢሆንም እንኳን የንቅናቄው ዋና ጸሀፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጨምሮ የተለያዩ የንቅናቄው አመራሮች በኃላፊነቴ እንድቆይ በነበራቸው ፍላጎት፣ እኔም ከነሱ ጋር ባደረኳቸው ውይይቶች በቦታው መቆየቴ ሠራዊቱን ይጠቅማል ብዬ ስላመንኩ እስካሁን ድረስ በተሰጠኝ የኃላፊነት ቦታ ላይ የምችለውን እያገዝኩ ቆይቻለሁ። ሆኖም ለቆሙለት ዓላማ፣ ለንቅናቄያቸውና ለሀገራቸው ክብር መተኪያ የሌላት ህይወታቸውን ለመክፈል የቆረጡ የትግል ጓዶቸ ላለፉት 7 ወራት በከፍተኛ ችግሮች ውስጥ ወድቀው ማየት ለኔ እንቅልፍ የሚነሳ ጉዳይ መሆኑ አልቀረም።

    ለኢትዮጵያ አንድነት፣ ለዴሞክራሲና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሁለንተናዊ መብቶች መረጋገጥ የበኩሌን አስተዋጽኦ ሳደርግ ቆይቻለሁ። ባለፉት ሁለት አስርት አመታት በላይ በውጭው ዓለም በተደረገው ትግል ልዩ ልዩ የትግል መድረኮችን በመሥራችነት፣ በአባልነት፣ በአስተባባሪነት፣ እንዲሁም በአመራር ኃላፊነቶች የዜግነት ግዴታዬን ከሚጠበቅብኝ በላይ አስተዋጽኦ በማድረግ ለ26 ዓመታት ያልተቋረጠ የትግል አስተዋጽኦ አድርጌያለሁ። የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥንን(ኢሳት) በማቋቋም፣ በመገንባት ሂደትና እስከ 2015 ድረስም በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ፣ እሰከአሁኑ ድረስም በቦርድ ሥራ አስፈጽሚ አባልነት የበኩሌን አስተዋጽኦ ተወጥቻለሁ።

    ባለፉት 8 ዓመታት የአርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና ልዩ ልዩ የሥራ ኃላፊነቶች ላይ በመሰማራት፣ እ.ኤ.አ ከመስከረም (September) ወር 2017 ከተደረገው የንቅናቄው ጉባኤ ላይ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ሆኜ ከተመረጥኩኝ በኋላም የንቅናቄው የውጪው ዘርፍ ኃላፊ በመሆን እስካሁን ድረስ በቅንነትና በምችለው እቅም ኃላፊነቴን ተወጥቻለሁ። በአሁኑ ወቅት ከአርበኞች ግንቦት 7 የሥራ አስፈጻሚ ኮሜቴ አባልነት፣ እንዲሁም ንቅናቄው የውጭ ዘርፍ ኃላፊነት በገዛ ራሴ ፈቃድ መልቀቄን ለአርበኞች ግንቦት 7 አባላት፣ ደጋፊዎች፣ በልዩ ልዩ የትግል መድረኮች ለምታውቁኝ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለማሳወቅ እወዳለሁ።

    የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ በቅርብ ጊዜ ጉባኤ በማድረግ ይከስማል። አዲስ ሀገራዊና በኢትዮጵያዊነት፣ በዜግነትና በማኅበራዊ ፍትህ ላይ የቆመ የፓለቲካ ፓርቲ የምሥረታ ሂደት ወደ ማገባደጃው በመድረሱ በአዲሱ ፓርቱ ለሚመረጡ አመራሮች እንዲሁም አባላትና ደጋፊዎች ሁሉ ያለኝን ጽኑና መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ። ለወደፊቱ ለኢትዮጵያ ሀገራችን እንዲሁም ለዓዝባችን ፋይዳና ጥቅም በሚያስገኙ ልዩ ልዩ ተግባራት ላይ በመሳተፍ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ድርሻዬን እንደምወጣ ለምታከብሩኝ፡ ለምትወዱኝና ለማከብራችሁና ለምወዳችሁ ወገኖቼ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለማረጋገጥ እወዳለሁ። እዚህ ላይ የንቅናቄው ወዳጆችም ሆናችሁ ሌሎች እንድታውቁት ላሰምርበትም የምፈልገው በንቅናቄው አጠቃላይ የፓለቲካ ራዕይና ተልእኮ፣ በሚመሠረተው የፓለቲካ ፓርቲ ዓላማና ተልዕኮ፣ እንዲሁም ከማንም የንቅናቄው አመራር አባላት ጋር በግል ሆነ በፓለቲካ ምንም ዓይነት ቅራኔ የሌለኝ መሆኑን ለማረጋገጥ እወዳለሁ። ዘለአለማዊ ክብርና ሞገስ ለኢትዮጵያ አንድነት፣ ለዓባችን ነጻነትና፣ ለፍትህ ሲሉ አይተኬ የህይወት መስዋዕትነት ለከፈሉ የኢትዮጵያ ልጆች ሁሉ! ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

    ነአምን ዘለቀ ቦጋለ
    ቨርጂኒያ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ
    ማርች 18 ቀን፣ 2019

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ነአምን ዘለቀ


    Semonegna
    Keymaster

    ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው አቤ ደንጎሮ ሆስፒታል የተመላላሽ፣ የአስተኝቶ ማከም፣ የወሊድ አገልግሎት፣ የቀዶ ሕክምና፣ የድንገተኛ ሕክምና፣ የራጅ፣ የላቦራቶሪና ሌሎች የአገልግሎት መስጫ ክፍሎች አሉት።

    ነቀምት (ኢዜአ) – ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤ ደንጎሮ ወረዳ ከ56 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው አቤ ደንጎሮ ሆስፒታል መጋቢት 8 ቀን 2011 ዓ.ም. ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ። ሆስፒታሉ ተገንብቶ ለአገልግሎት መብቃቱ እንዳስደሰታቸው አንዳንድ የወረዳው ነዋሪዎች ተናግረዋል።

    የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ደረጃ ዱጉማ በምርቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት፥ ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው አቤ ደንጎሮ ሆስፒታል የተመላላሽ፣ የአስተኝቶ ማከም፣ የወሊድ አገልግሎት፣ የቀዶ ሕክምና፣ የድንገተኛ ሕክምና፣ የራጅ፣ የላቦራቶሪና ሌሎች የአገልግሎት መስጫ ክፍሎች አሉት።

    ሆስፒታሉ በአቤ ደንጎሮ ወረዳና በአካባቢው በሚገኙ ተጎራባች ወረዳዎች ለሚገኙ ከ400 ሺህ ለሚበልጡ ነዋሪዎች አገልግሎት እንደሚሰጥ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ሆስፒታሉ የሕክምና መሳሪያዎችና የሰው ኃይል የተሟላለት መሆኑንም አመልክተዋል።

    የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንትና የማኅበራዊ ዘርፍ ክላስተር አስተባባሪ ወ/ሮ ጠይባ ሀሰን በበኩላቸው ሆስፒታሉ የህዝቡን የረጅም ጊዜ ጥያቄ የመለሰና የሕዝቡን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች የሚፈታ መሆኑን ገልጸዋል። ህብረተሰቡ ሆስፒታሉ የራሱ ሀብትና ንብረት መሆኑን ተረድቶ እንደ ዓይኑ ብሌን ሊጠብቀው እንደሚገባ አሳስበዋል።

    ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ነዋሪዎች በበኩላቸው ሆስፒታሉ ተገንብቶ ለአገልግሎት በመብቃቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል።

    ከወረዳው ነዋሪዎች መካከል የቱሉ ዋዩ ከተማ ነዋሪ ወ/ሮ እቴነሽ ደገፉ በሰጡት አስተያየት በአካባቢያቸው ለበርካታ ዓመታት የጤና ተቋማት ባለመኖሩ በተለይ በእናቶችና ህጻናት ህይወት ላይ አደጋ ይደርስ እንደነበር አስታውሰዋል። የወረዳው ህዝብ ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ሻምቡና ነቀምቴ ሆስፒታሎች በመጓዝ ለወጪና እንግሊት ሲጋለጥ መቆየቱንም ጠቁመዋል። በአካባቢያችን ደረጃውን የተጠበቀ ሆስፒታል መገንባቱ ወጪና እንግልትን ከማስቀረቱም በላይ የእናቶችና የህጻናትን ሞት ለመቀነስ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

    ሌላው የከተማው ነዋሪ አቶ ደቻሣ ገለታ ወረዳው ከነቀምቴና ሻምቡ ሆስፒታሎች በብዙ ኪሎሜትሮች ርቀት ላይ ስለሚገኝ በተለይ በወሊድ ጊዜ የበርካታ እናቶችና ህፃናት ህይወት ሲያልፍ መቆየቱን አመልክተዋል። የሆስፒታል መገንባት የአካባቢውን ሕዝብ የረጅም ጊዜ ጥያቄ የመለሰና የህብረተሰቡን የጤና ችግር የሚፈታ በመሆኑ ተገንብቶ ለአገልግሎት በመብቃቱ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    አቤ ደንጎሮ ሆስፒታል


    Anonymous
    Inactive

    «ጥቁሩ ሰንዱቅ» [BlackBox] ለምን ፈረንሳይ ተላከ?
    —–

    ከእሑዱ አሳዛኝ የአየር መንገድ አደጋ ጋር በተያያዘ ጥቁሩ የመረጃ ሰንዱቅ ከሁለት ቀናት በኋላ መገኘቱ ይታወሳል። ትናንት ደግሞ ለምርመራ ወደ ፈረንሳይ መላኩ ተዘግቧል። ለመሆኑ ለምን ፈረንሳይ ተመረጠች? ለምን የጥቁር ሰንዱቁን መረጃ ለሌላ አገር አሳልፈን እንሰጣለን? ቦይንግ ለምን የመረጃ ሰንዱቁን ለመመርመር ፍላጎት አሳየ? የአብራሪዎች ሚና በመጀመርያዎቹ ደቂቃዎች ምን ይመስላል? በነዚህ ቁልፍ ጥያቄዎችና ተያያዥ ጉዳዮች ዙርያ ለሁለት ዐሥርታት አብራሪዎችን የማስተማር ልምድ ያላቸውን ካፒቴን አማረ ገብረሃናን አነጋግረናቸዋል። ካፒቴን አማረ በአየር ኃይል ከ26 ዓመት በላይ ሠርተዋል። በሲቪል አቪየሽን የፍላይት ሴፍቲ ዲፓርትመንትን ደግሞ በዳይሬክተርነት ለ14 ዓመት መርተዋል። በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለ8ዓመት በበረራ ትምህርት ቤት አስተምረዋል። አሁን በአቢሲኒያ በረራ ምክትል ኃላፊ ናቸው።

    ጥቁሩን የመረጃ ሰንዱቅ በተመለከተ
    ጥቁሩ ሰንዱቅ ሁለት ቅንጣት አለው። አንዱ ፍላይት ዳታ ሪኮርደር ነው፤ ሁለተኛው ደግሞ ኮክፒት ቮይስ ሪኮደር ነው። እነዚህ ሁለቱ በአደጋ ጊዜም ሆነ በሌላ ተፈላጊ በሆነ ጊዜ ሁሉ ቁልፍ መረጃዎችን ይዘው የሚቆዩና አስፈላጊ ሆነው በሚገኙበት ጊዜ ደግሞ መረጃው ተገልብጦ ጥቅም ላይ ማዋል እንዲቻል ሆነው የተሠሩ ናቸው።

    ሙሉውን ቢቢሲ አማርኛ ላይ ያንብቡ

    Semonegna
    Keymaster

    በኢትዮጵያ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ተግባራዊ የሚሆን አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች በተገኙበት ዛሬ ይፋ ሆነ።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ አንዲት አገር በዓለም አቀፍ የጤና ህግጋት ላይ የተጠቀሱትን መሠረታዊ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችንና አደጋዎችን ለመከላከል፣ አስቀድሞ ለመለየትና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል አቅም ለማጠናከር የተቀመጡ ግቦችን እንድታሟላ የሚያስችል ዕቅድ ሲሆን በሃገሪቱ ሙሉ ባለቤትነት የሚቀረጽ የትግበራ ዕቅድ ነው።

    ማንኛውም የዓለም አቀፍ የጤና ሕግጋት ፈራሚ አገር ይህንን ዕቅድ እንደሚያዘጋጅ ሁሉ ኢትዮጵያም የዚህ ስምምነት ፈራሚ እንደመሆኗ በተደጋጋሚ የሚገጥሟትን የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎችን ለመቋቋም የሚያስፈልጓትን አቅም ለመገንባት ዕቅዱን ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኗል።

    የትግበራ ዕቅዱን በአዲስ አበባ በይፋ መጀመሩን ያበሰሩት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር  አቶመቀ መኮንን፥ ስለ አንድ አገር ሰላምና ደህንነት ስንናገር የሕዝቦቻችንን የጤና ደህንነት ጭምር አያይዘን እንደምንናገር መገንዘብ እንደሚገባ ጠቁመው፥ አገራዊ ዕቅዱ ወቅታዊና እንደአገር የሚያጋጥሙንን ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ቀድሞ ለመከላከልና ብዙ ጉዳት ሳያደርሱ ምላሽ ለመስጠት ያስችለናል ብለዋል።

    ◌ SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest

    የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን በበኩላቸው ሃገሪቱ እ.ኤ.አ በ2016 የዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ከአፍሪካ ቢሮ በመጡ ገምጋሚዎች የጤና ደህንነቷ ያለበትን ደረጃ ማስመዘኗን ገልጸው፥ ከግምገማው በተገኙ ግብረ መልሶች እና በሃገሪቱ ከተከሰቱ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ምላሽ አሰጣጣችን የተግባር ልምድ በመውሰድ አገራዊ የጤና ትግበራ ዕቅድ አዘጋጅታለች ብለዋል።

    የትግበራ ዕቅዱን ለመፈጸም በጀት ስለሚጠይቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ያለንን ሃብት አቀናጅተን በመጠቀም ለዕቅዱ መሳካት የበኩላችንን ድርሻ መወጣት ይገባናል ያሉት ደግሞ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ዶ/ር ፓሚላ ሙቱሪ ናቸው።

    የኢትዮጵይ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኤባ አባተ በበኩላቸው፥ እንደ ኩፍኝና ቢጫ ወባን የመሳሰሉ ወረርሽኞችን ለመከላከልና በዓለም ደረጃ ለሚከሰቱ እንደ ኢቦላ እና ዚካ ቫይረስ ያሉ ወረርሽኞችን ለመከላከል አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።

    ለዕቅዱ ትግበራ 368 ሚሊዮን 764 ሺህ 777 ዶላር የሚያስፈልግ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 77 በመቶ የሚሆነው የክትባት ሽፋንን ለማሳደግ የሚውል ይሆናል።

    አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅዱ ለአምስት ዓመት ማለትም ከ2011/12 እስከ 2016/17 ዓ.ም ድረስ የሚተገበር ይሆናል።

    ምንጭ፦ የጤና ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አገራዊ የጤና ደህንነት


    Semonegna
    Keymaster

    የዘንድሮው የዓለም ቲቢ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ “ጊዜው አሁን ነው…” (It’s Time…) በሚል መሪ ቃል፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ “በተጠናከረ አመራር ከቲቢ ነፃ የሆነች ሀገር” መሪ ቃል ይከበራል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር በየዓመቱ የሚከበረውን የዓለም ቲቢ ቀን በዓል ከዓመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባዔ ጋር በማቀናጀት የክልል ጤና ቢሮዎችን፣ ዩኒቨርሲቲዎችንና አጋር ድርጅቶችን በማስተባበር ያከብራል።

    በዚህም መሠረት ዘንድሮ በዓለም ደረጃ ለ37ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረው የዓለም ቲቢ ቀን በዓል እና ለ14ኛ ጊዜ የሚካሄደው ዓመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባዔ “በተጠናከረ አመራር ከቲቢ ነፃ የሆነች ሀገር” በሚል መሪ ቃል በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰመራ ከተማ መጋቢት 14-15 ቀን 2011 ዓ.ም. ይከበራል።

    በኢትዮጵያ የቲቢ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር አገልግሎት እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መጀመሪያ ከተጀመረ አንስቶ በሁሉም ክልሎች፣ በመንግሥታዊና በተፈቀደላቸው የግል ጤና ተቋማት በነጻ በመሰጠቱ በርካታ የቲቢ ሕሙማን ሕክምና እንዲያገኙ በማድረግ የብዙ ዜጎችን ሕይወት ታድጓል።

    እ.ኤ.አ. በ2018 የዓለም ጤና ድርጅት ባወጣው ሪፖርት መሠረት በኢትዮጵያ አጠቃላይ የቲቢ በሽታ ስርጭት ምጣኔ እ.ኤ.አ. በ1990 ከ100,000 ሰዎች ውስጥ 369 የቲቢ ተጠቂዎች የነበሩ ሲሆን፣ ይህ አሃዝ አሽቆልቁሎ እ.ኤ.አ. በ2017 ከ100,000 ሰዎች ውስጥ 164 የቲቢ ተጠቂዎች አንደሆኑ አሳውቋል። በቲቢ በሽታ ምክንያት የሚከሰት የሞት መጠንም እ.ኤ.አ. በ1990 ከ100,000 ሰዎች ውስጥ 89 ከነበረው ወደ 24 መቀነስ ተችሏል።

    አገልግሎቱን በተመለከተ ዛሬም ቢሆን ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች እንዳሉ በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ህይወት ሰለሞን ገልፀዋል። ወ/ሮ ህይወት በመግለጫቸው እንደተናገሩት በአገሪቱ የቲቢ በሽታ ይገኝባቸዋል ተብለው ከሚገመቱት ሰዎች 35 ከመቶ ያህሉ ወደ ሕክምና ተቋማት አለመሄድ እና የቲቢ በሽታ ታካሚዎች መድኃኒትን በሐኪም ትዕዛዝ መሠረት አለመጠቀም፣ ማቋረጥ፣ በባለሙያዎች የሚሰጥ ትዕዛዝና ክትትል ጉድለት ለመጀመሪያው ደረጃ ቲቢ በሽታ ሕክምና በጥቅም ላይ እየዋሉ ያሉ መድኃኒቶች የቲቢ በሽታ አምጪ ተሕዋስያንን የመግደል አቅማቸውን እያሳጣ መሆኑን አስታውቀዋል።

    • ቲቢ በዓለም ላይ ሰዎች ከሚሞቱባቸው መንስዔዎች ዘጠነኛው ሲሆን፥ በአንድ ተሕዋስ ብቻ ከሚተላለፉ በሽታዎ ከ ኤች አይ ቪ/ኤድስ (HIV/AIDS) ቀጥሎ ሁለተኛው ገዳይ በሽታ ነው፤
    • እ.ኤ.አ. በ2016 አፍሪካ ውስጥ ብቻ 2.5 ሚሊዮን ሰዎች በቲቢ በሽታ ተጠቅተዋል፤ ይህም በመላው ዓለም በበሽታው ከተጠቁ ሰዎች ሩቡን ያህል ነው፤
    • እ.ኤ.አ. በ2016 አፍሪካ ውስጥ ብቻ 417,000 ሰዎች፣ በመላው ዓለም ደግሞ 1.7 ሚሊዮን ሰዎች በቲቢ በሽታ ለሞት ተዳርገዋል፤
    • ሰባት አገራት፥ ማለትም ህንድ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ቻይና፣ ፊሊፒንስ፣ ፓኪስታን፣ ናይጄርያ እና ደቡብ አፍሪካ በዓለም ላይ ከሚከሰተው ቲቢ 64 በመቶው ያህሉ ይከሰትባቸዋል፤
    • በኤች አይ ቪ (HIV) ለተጠቁ ሰዎች ዋነኛ ገዳይ በሽታ ቲቢ ሲሆን፥ እ.ኤ.አ. በ2016 መሠረት 40 በመቶ የሚሆኑት በኤች አይ ቪ የተጠቁ ሰዎች የሞቱት በቲቢ በሽታ ነው፤
    • በየዓመቱ የቲቢ በሽታ በሁለት በመቶ እየቀነሰ ቢሆንም፥ እ.ኤ.አ. በ2020 ቲቢን ከዓለም ሙሉ ለሙሉ ለማጥፋት ይህ በሽታ ከአራት እሰከ አምስት በመቶ ያህል በየዓመቱ መቀነስ አለበት፤
    • እ.ኤ.አ. ከ2000 እስከ 2015 ድረስ በአጠቃላይ 53 ሚሊዮን ሰዎችን በሕክምና ከቲቢ በሽታ ማዳን ተችሏል፤ ከዚህ ውስጥም አፍርካ ውስጥ ብቻ እ.ኤ.አ. ከ2000 እስከ 2014 ድረስ 10 ሚሊዮን ሰዎችን በሕክምና ከቲቢ በሽታ ማዳን ተችሏል፤
    • እስከ 2030 ድረስ (እ.ኤ.አ.) ከዓለም ላይ የቲቢ በሽታን ማጥፋት ከዘላቂ የዕድገት አጀንዳዎች (Sustainable Development Goals) አንዱ ነው።

    ምንጮች፦ የጤና ሚኒስቴር፣ የዓለም ጤና ድርጅት / ሰምነኛ ኢትዮጵያ

    የዓለም ቲቢ ቀን


    Semonegna
    Keymaster

    እ.ኤ.አ ከ2019 እስከ 2023 ለሚተገበረው አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ 10 ቢሊዮን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን፥ ወጪው ከኢትዮጵያ መንግሥት፣ ከልማት አጋሮችና ባለድርሻ አካላት እንደሚሰባሰብ ለማወቅ ተችሏል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – በኢትዮጵያ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ተግባራዊ የሚሆን አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች በተገኙበት ዛሬ ይፋ ሆነ።

    በዚህ ወቅት እንደተገለጸው፥ አገሪቷ መከላከልን መሠረት ያደረገ ስልት ቀይሳ የምታደርገውን ጥረት በጉልህ ይደግፋል። በተለይም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ አካባቢዎች በተፈጠሩ አለመረጋጋት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ተላላፊ ለሆኑ በሽታዎች እንዳይጋለጡ አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችል ነው።

    እ.ኤ.አ ከ2019 እስከ 2023 ለሚተገበረው አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ 10 ቢሊዮን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን፥ ወጪው ከኢትዮጵያ መንግሥት፣ ከልማት አጋሮችና ባለድርሻ አካላት እንደሚሰባሰብ ለማወቅ ተችሏል።

    የጤና ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን እንደተናገሩት፥ በዕቅድ ዝግጅቱ የሚመለከታቸው መሥሪያ ቤቶች ተሳትፎ አድርገዋል።

    አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ ችገሮች ከመከሰታቸው በፊት አስቀድሞ በመለየት መከላከል፣ ችግሮች ሲከሰቱ ፈጣን ምላሽ መስጠት በኅብረተሰቡ ላይ በህመምና በሞት የከፋ ጉዳት ሳይደርስ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ስትራቴጂ ነው።

    ◌ SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest

    ባለፉት ሁለት ዓመታት የጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵይ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) ጋር በመሆን ዕቅዱን ዝግጅት ሲደረግ እንደነበረ ዶ/ር አሚር ገልጸው፥ አገሪቷ በዘርፉ ምን ክፍተት አለባት? የሚለውን በጥናት ላይ የተመሰረተ ሥራ መከናወኑን አስረድተዋል። እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፥ ዕቅዱ ከመዘጋጀቱ በፊት አገር አቀፍ የዳሰሳ ጥናት ተካሂዷል።

    ዶ/ር አሚር እንደሚሉት፥ በጥናቱ መሠረት ዝቅተኛ አፈጻጸም የታየበት አደጋ ሲከሰት ፈጣን ምላሽ መስጠት መሆኑ የተለየ ሲሆን ችግሩን ለመፍታት በሁለቱ ከተማ መስተዳደሮችና በዘጠኙ ክልሎች ማዕከላት ተቋቁሟል።

    ከኬሚካልና ጨረር ጋር በተያያዘ አደጋ ቢያጋጥም ምላሽ ለመስጠት በቂ ዝግጅት እንደሌለ በጥናት የተለየ ሌላው ችግር መሆኑን ጠቁመው በዚህም ላይ የማስተካከያ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አብራርተዋል።

    በዕቅዱ ላይ እንደ ክፍተት የተቀመጡ ችግሮችን ለመፍታት መንግሥት 25 ሚሊዮን ዶላር በመመደብ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጸዋል።

    የኢትዮጵይ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኤባ አባተ በበኩላቸው፥ አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅዱ በአገሪቷ ተላላፊ በሽታዎችና ወረርሽኝን አስቀድሞ ለመግታት ወሳኝ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።

    ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በዚሁ ወቅት እንደገለጹትዕ አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅዱ ወቅታዊና አስፈላጊ ነው። አደጋዎችን ቀድሞ የመከላከል፣ ብዙ ጉዳት ሳያደርሱ የመቆጣጠርና መልሶ የማገገምና እንዳይደገም የማድረግን አቅምን መገንባት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ


    Semonegna
    Keymaster

    የህንድ መንግስት በተያዘው የፈረንጆቹ ዓመት ለ3,500 ኢትዮጵያውያን ነጻ የትምህርት ዕድል ይሰጣል
    —–

    የህንድ መንግስት እንደ አውሮጳውያን አቆጣጠር በ2019 ብቻ ለ3ሺህ500 ያህል ኢትዮጵያውያን ነጻ የትምህርት ዕድል ለመስጠት መዘጋጀቱን አስታወቀ።

    ‘ስተዲ ኢን ኢንዲያ’ (Study in India) በተሰኘው ተቋም አማካኝነት የሚሰጠው የትምህርት ዕድል የአጭርና የረጅም ጊዜ ስልጠናን ያካተተ እንደሚሆን ታውቋል።

    የህንድ መንግስት በሚሰጠው ነጻ የትምህርት ዕድል ከመላው አፍሪካ ተጠቃሚ የሚሆኑ ዜጎች ቁጥር ከ20 ሺህ የሚልቅ እንደሆነ ‘ስተዲ ኢን ኢንዲያ’ አስታውቋል።

    ትምህርትና ስልጠና የሚሰጥባቸው መስኮች በርካታ ሲሆኑ የህክምና ዘርፍን የማያካትት መሆኑ ተገልጿል።

    በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኑራግ ስሪቫስታቫ እንደገለጹት፤ የህንድ መንግስት ለአፍሪካ አገሮች እየሰጠውን ያለው የአጭርና የረጅም ጊዜ ስልጠና አጠናክሮ የማስቀጠል ፍላጎት አለው።

    አክለውም ተቋሙ አጫጭር ስልጠናዎችን በማዘጋጀትና ነጻ የትምህርት እድል ሲሰጥ የቆየ መሆኑን ገልጸው አሁን ደግሞ በፊት ይሰጠው የነበረውን ቁጥር በማስፋትና ረጅም ስልጠናዎችንም ለመስጠት ማሰቡን ገልጸዋል።

    38 ሺ ኮሌጆችና 800 ዩኒቨርሲቲዎች ያሏት ህንድ በትምህርት ተቋማት ብዛትና የትምህርት እድሎችንም በማመቻቸት ረገድ ትታወቃለች።

    ምንጭ፦ ኢዜአ

    Semonegna
    Keymaster

    ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ዳያስፖራዎች ልዑካን ቡድን አባላት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውን በሙያቸው እንዲያግዙ ጥሪ ማቅረባቸውን ተክተሎ የመጡ ናቸው።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በኢትዮጵያ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሲካሄድ የቆየው መንግስት ቴክኖሎጂ ለመጠቀም ያለውን ዝግጁነት የሚለይና ለችግሮች የመፍትሄ አቅጣጫ የሚያስቀምጥ አውደ-ጥናት ተጠናቀቀ።

    በአውደ ጥናቱ የመንግስት አግልግሎት አሰጣጥ፣ ቴክኖሎጂ ለመጠቀም ያለው ዝግጁነት፣ የፋይናንስ አስተዳደር ስርዓት ክፍተት ተለይተውበታል – ሚኒስቴሩ እንደዘገበው።

    የጤና አስተዳደር፣ የታክስ አሰባሰብ ስርዓት፣ የመረጃ ግንኙነት (ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን) ቴክኖሎጂ ደኅንነት፣ በባንክ አገልግሎት፣ በኢንሹራንስ አገልግሎት፣ ትምህርት ሚኒስቴር፣ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ በኦዲት አገልግሎት፣ የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት፣ የውሃ አወጋገድ ላይ ክፍተቶች ተለይተዋል።

    አሜሪካ ውስጥ ቨርጂንያ ኢንተርናሽናል ዩኒቨርሲቲ (Virginia International University; Fairfax, VA) መምህር በሆኑት ዶ/ር ተፈራ በየነ የተመራው ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ልዑክ ክፍተቶቹን ከለዩ በኋላ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።

    ከ7ሺህ 800 በላይ አዳዲስ አነስተኛና መካከለኛ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች በመላው አገሪቱ ሊቋቋሙ ነው

    ባለሙያዎቹ በኢንሹራንስ፣ በህክምና ቴክኖሎጂ፣ በዲፕሎማሲ፣ በኢንፎርሜሽን ኮሙኑኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ በአሜሪካን ሀገር በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች ከፍተኛ ልምድ ያካበቱ ኢትዮጵያዊያን ናቸው።

    ሚኒስትሮች፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የፋይናንስ ዳይሬክተሮች እና ሌሎችም ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው አካላት ከቡድኑ ጋር ለ1 ሳምንት ክፍተቶችን እና ጉድለቶችን የመለየት ሥራ ሲሠሩ ቆይተዋል።

    የሚመለከታቸው አካላት በየዘርፉ የሚደረጉ ማስተካከያዎችን በኃላፊነት ወስደው ወደ ተግባር የመቀየር ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል። በማጠቃለያው ላይ፥ ልዑካኑ የኢትዮጵያ መንግስት ወይም የሚመለከተው መንግስታዊ ተቋም ዕድሉን ከሰጠን የሀገራችንን ችግር ለመፍታት በቂ አቅም አለን ብለዋል። ወደፊትም በማንኛውም መልኩ ሀገራቸውን ለማገዝ ቃል ገብተዋል።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታዎች ሹመቴ ግዛው (ዶ/ር) እና ጀማል በከር ልዑካኑ ሀገራቸውን ለመረዳት ያላቸውን ቁርጠኝነት በማድነቅ ምስጋና አቅርበዋል።

    የልዑካን ቡድኑ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውን በሙያቸው እንዲያግዙ ጥሪ ማቅረባቸውን ተክተሎ የመጡ ናቸው።

    ምንጭ፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ትውልደ ኢትዮጵያዊያን


    Anonymous
    Inactive

    የአውሮፕላን አደጋ መንስኤውን የሚመረምር ኮሚቴ ተዋቅሮ ስራ ጀመረ
    —–

    የትራንስፖርት ሚኒስቴር እሁድ መጋቢት 1/2011 ዓ.ም በኢትዮጵያ የመከስከስ አደጋ ያጋጠመውንና ለ157 ሰዎች ሕልፈት ምክንያት የሆነውን ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን የአደጋ መንስኤ የሚያጣራ ኮሚቴ በማዋቀር ወደ ስራ ገብቷል።

    በትራንስፖርት ሚኒስቴር ስር የሚገኘው የአውሮፕላን አደጋ ምርመራ ቢሮ በ ICAO Anex-13 መሰረት የአውሮፕላን አደጋ መንስኤውን የሚመረምር ኮሚቴ አዋቅሮ ስራ ጀምሯል።

    በዛሬው እለትም የአደጋውን መንስኤ በማጣራት ሂደቱ ከሚስሳተፉ አባላት ውስጥ የNational transport safety board of America የምርመራ ቡድን አባላት አዲስ አበባ ገብተዋል።

    ምንጭ፥ የትራንስፖርት ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    ለዩኒቨርሲቲ መምህራን ጥናትና ምርምር ማድረግ አስገዳጅ የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ በሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጀ። የአድዋ ከተማ አስተዳደር ለፓን አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ 114 ሄክታር መሬት ሰጠ።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – የዩኒቨርሲቲ መምህራን ጥናትና ምርምር እንዲያደርጉ አስገዳጅ የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ እያዘጋጀ መሆኑን የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

    በአሁኑ ወቅት በዩኒቨርሲቲዎች የሚሠሩት ጥናትና ምርምሮች ከሌሎች የአፍሪካ አገራት ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ መሆኑንም ሚኒስቴሩ ገልጿል። የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደተናገሩት፥ በአገሪቷ በሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚወጡት የጥናትና ምርምር ሥራዎች ከሚጠበቀው በታች ናቸው፤ ለዚህ ደግሞ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለጥናትና ምርምር የሚመደበው በጀት አነስተኛ መሆኑም እንደ ዋነኛ ምክንያት አስቀምጠውታል። እንዲያውም ለዘርፉ የሚመደበው አጠቃላይ ዓመታዊ በጀት ከሁለት በመቶ በታች መሆኑን በመጠቆም።

    በተጓዳኝም የምርምር መሠረተ-ልማቶች አለመኖር፣ ሦስተኛ ዲግሪ ያላቸው መምህራን ቁጥር አነስተኛ መሆንና መምህራን ለምርምር ትኩረት አለመስጠታቸውም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ለሚሠሩት ጥናታ ምርምሮች ቁጥር አነስተኛ መሆነ ተጨማሪ ምክንያቶች ናቸው። ይሁንና ዩኒቨርሲቲዎች አሁን ባሏቸው አቅም በአስገዳጅ መልኩ የጥናትና ምርምር ሥራ ላይ ለመሰማራት የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ እየተዘጋጀ መሆኑን ዶ/ር ሳሙኤል ገልጸዋል።

    ምንም እንኳን በትምህርት ተቋማቱ ዝቅተኛ ቢሆኑም በሥመ-ጥር ዓለም አቀፍ ጆርናሎች ላይ ምርምሮቻቸውን የሚያወጡ ጉምቱ ምሁራን መኖራቸውንም ዶ/ር ሳሙኤል አልሸሸጉም።

    ለጥናትና ምርምር የሚበጀተውን በጀት በተመለከተም ከአገሪቷ እድገትና ከመምህራኑ አቅም ጋር ባገናዘበ መልኩ እያደገ የሚመጣ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ዩኒቨርሲቲዎች ያሏቸውን ጆርናሎች ጥራታቸውን ከፍ ለማድረግ የሚያስችል መመሪያም በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ጥናት እየተደረገበት መሆኑንም አስረድተዋል። መመሪያውንም በቅርቡ ወደ ሕግ በመቀየር በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙ ጆርናሎች የሚመሩበት ወጥ ሥርዓት በመዘርጋት የእውቅና ደረጃም እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል።

    እንዲህ ዓይነቱን እርምጃ መውሰድ (ረቂቅ አዋጁን ማውጣትም ሆነ ለጆርናሎች መመሪያ መዘጋጀት) የሚካሄዱትን ምርምሮች ጥራታቸውን ለመጠበቅ እንደሚያግዝ ገልጸው፥ በቀጣይም ጥናትና ምርምር ላይ የግሉ ዘርፍ የድርሻውን ድጋፍ እንዲያደርግ እየተሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

    በአሁኑ ወቅት የግልና የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን ቁጥር 33 ሺህ ደርሷል፤ ከእነዚህ ውስጥ 5 ሺህ 500 የሚሆኑት ናቸው ሦስተኛ ዲግሪ ያላቸው – የኢትዮጵይ ዜና አገልግሎት እንደዘገበው።

    ከከፍተኛ ትምህርት ጋር በተያያዘ፥ ለፓን አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ 114 ሄክታር መሬት መስጠቱን በትግራይ ክልላዊ መንግስት፣ የአድዋ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል። የዩኒቨርስቲውን ግንባታ ለማስጀመር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።

    የአድዋ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ዘስላሴ ዘብራአብሩክ ለኢዜአ እንደገለጹት አስተዳደሩ ለዩኒቨርሲቲው ግንባታ እንዲውል መሬቱ ተሰጥቷል። በዚህም 131 የአካባቢው አርሶ አደሮች ከይዞታቸው ላይ ተነስተዋል። ከይዞታቸው ለተነሱ አርሶ አደሮችም ካሳ ክፍያ ለመፈፀም 15 ሚሊዮን ብር መመደቡን አስታውቀዋል።

    የዩኒቨርሲቲው ግንባታ ኮሚቴ አስተባባሪ አቶ ቢተው በላይ በበኩላቸው ግንባታውን ለማስጀመር ከፌዴራልና ከትግራይ ክልል መንግሥታት 450 ሚሊዮን ብር ተመድቧል። ከዚህም የትግራይ ክልል መንግሥት 250 ሚሊዮን ብር ለመለገስ ቃል መግባቱ ይታወሳል። የአዲስ አበባ አስተዳደርም በቅርቡ 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የዩኒቨርሲቲ መምህራን ጥናትና ምርምር እንዲያደርጉ


    Semonegna
    Keymaster

    እ.ኤ.አ በ2011 የተመሠረተው ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዶክተሮችን ሲያስመርቅ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ጊዜ እንደሆነ ተገልጿል። ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት ስድስት ኮሌጆች፣ አንድ ትምህርት ቤት እና አንድ ተቋም (ኢንስቲትዩት) አለው። 

    ዓዲግራት (ሰሞነኛ)– ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለመጀመርያ ግዜ ሰባት ሴቶች 25 ወንዶች በድምሩ 32 የሕክምና ዶክተሮችን (medical doctors) እንዲሁም በድኅረ መሠረታዊ መርሃግብር (post basic program) 30 ተማሪዎችን አስተምሮ መጋቢት 1 ቀን 2011 ዓ.ም. አስመርቋል። በዕለቱ የክብር እንግዳ የነበሩ የትግራይ ክልል ም/ር/መስተዳደር ክቡር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ባስተላለፉት መልዕክት፥ በሃገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ከፍተኛ የጤና ባለሙያዎች እጥረት እንዳለና ችግሮቻችን በማቃለል አንዳንዱን በመፍታት ልዩነት የሚያመጣ ድርሻ እንደሚኖራችሁ ባለ ሙሉ ተስፋ ነኝ ብለው መልእክታቸው አስተላልፍዋል።

    በዕለቱ የምርቃት ሥነ ስርዓት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ወ/ሮ ስሃረላ ኣብዲላሂ በበኩላቸው የጤና ባለሙያ ማለት የግል ምቾትን እንደ መስዋዕትነት በመክፈል እንብካቤ ለሚያስፈልጋቸው እንክብካቤ መስጠት መሆኑን በማወቅ በየተኛውም የሃገሪቱ ክፍል ሄዳችሁ ያስተማራችሁን ህብረተሰብ ለማገልገል ዝግጁ እንድትሆኑ በማለት ለዕለቱ ተመራቂዎች መልዕክታቸውን አስተላለፈዋል። ዩኒቨርሲቲው የነበሩበትን ፈተናዎች ኣልፈው ለመመረቅ መብቃታችው በጣም የሚያኮራ ታሪክ መሆኑ የዩኒቨርሲቲው ግዝያዊ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገ/መስቀል ገልፀዋል።

    ኬር ኢትዮጵያ በ7 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ወጭ ያስገነባውን የምርምርና የስልጠና ማዕከል ለሐረማያ ዩኒቨርሲቲ አስረከበ

    ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዶክተሮችን ሲያስመርቅ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሆነ ተገልጿል። ዩኒቨርሲቲው የተመሠረተው እ.ኤ.አ በ2011 ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት ስድስት ኮሌጆች፣ አንድ ትምህርት ቤት እና አንድ ተቋም (ኢንስቲትዩት) አለው። ከሁለት ዓመታት በፊት ዩኒቨርሲቲው ባወጣው የአሃዝ ዘገባ በአጠቃላይ ከ16,000 በላይ ተማሪዎች በመደበኛው፣ እንዲሁም ከ6,000 በላይ ተማሪዎች በተከታታይ (continuing education) መርሀ ግብር እያስተማረ ይገኛል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ


    Semonegna
    Keymaster

    “የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ማምጣት ቸርነት አይደለም። ነገር ግን ለአንድ ሀገር ህልውና በመሆኑ አንዱ ሰጭ ሌላው ተቀባይ በሆነ መልኩ ሳይሆን ሰብዓዊ ወይም ሰዋዊ መብትም ጭምር ነው።” ዶ/ር አልማዝ አፈራ

    ደብረ ብርሃን (ሰሞነኛ) – የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን “የላቀ ትኩረትና ቁርጠኝነት ለሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት” በሚል መሪ ቃል የዩኒቨርሲተው ከፍተኛ አመራሮች ተማሪዎች፣ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች፣ የዞን ሴቶች ህጻናትና ወጣቶች መምሪያ ኃላፊዎችና የሊግ ተወካዮች በተገኙበት መጋቢት 2 ቀን 2011 ዓ.ም. በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል።

    በበዓሉ ላይ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳሬክተር ወ/ሮ ኃይማኖት ቢችል እንደገለጹት የሴቶችን ቀን ስናከብር በሴቶች ላይ ይደርስ የነበረውን ጭቆና ለማስወገድ የተደረገውን የትግል እንቅስቃሴና ውጤታማነት ለመዘከር፣ ሴቶች ከነበረባቸው ጭቆና ተላቀው በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊ፣ በስነ-ልቦናዊ እና ፖለቲካዊ እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር የሚቻልበትን ሁነት ለመዘከር መሆኑን አንስተዋል። እንደ ዳይሬክተሯ ገለፃ፥ በዓሉ ሴቶች ውጤታማ የሆኑባቸውን ሥራዎች በመዘከር ለማበረታታት ያስችላል ብለዋል።

    የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር አልማዝ አፈራ በዓሉን በንግግር ሲከፍቱ፥ የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ማምጣት ቸርነት አይደለም። ነገር ግን ለአንድ ሀገር ህልውና በመሆኑ አንዱ ሰጭ ሌላው ተቀባይ በሆነ መልኩ ሳይሆን ሰብዓዊ ወይም ሰዋዊ መብትም ጭምር ነው ብለዋል። ፕሬዚዳንቷ አክለው እንደገለጹት፥ ሴት የቤተሰብና የሀገር መሠረት ስለሆነች እኛ የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰቦች ከዘር፣ ከጾታና ከሀይማኖት አድሎ በጸዳ መልኩ መሥራትና መታገል እንዲሁም በግልፅ ብቻ ሳይሆን በረቀቀ ዘዴ ጭምር የሚደረጉ ጾታዊ ትነኮሳዎችን ለመዋጋት መሥራት አለብን ብለዋል።

    የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የተቀናጀ የግብርና ምርምር ፕሮጀክት ተመረቀ

    በበዓሉ ላይ ሁለት ጥናታዊ ጽሁፎች የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት እና እናትነት /Motherism/ በሚሉ ርዕሶች በዶ/ር ሰርካለም ይገረሙ እና በመ/ር ጌትነት ጥበቡ ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል። በውይይቱም የቀረቡት ጽሁፎች አስተማሪ በመሆናቸው ለተግባራዊነታቸው ሁሉም አካል ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንዳለበት ተጠቁሟል።

    በመጨረሻም አርዓያ ለሆኑ ሴት መምህራንና በ2011 ዓ.ም የመጀመሪያው ወሰነ ትምህርት ከ1ኛ-3ኛ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ሴት ተማሪዎች የእወቅናና የማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷል። አቶ ደረጀ አጅቤ የአስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ም/ፕሬዚዳንት ተወካይ የማበረታቻ ሽልማቱን ከሰጡ በኋላ ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ሴቶች ቤተሰባቸውን ይመራሉ፣ ያስተዳድራሉ፤ ለዚህም መስዋዕትነት ይከፍላሉ። አመራር ለመሆን ሴቶች ራሳቸው መስዋዕትነት መክፈል ይኖርባቸዋል። ሴቶችን አመራር ስናደርጋቸው ምቹ የሥራ ቦታና ሁኔታ ልንፈጥርላቸው ይገባል ብለዋል።

    ምንጭ፦ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የሴቶች ቀን


    Semonegna
    Keymaster

    የድሬዳዋ ከንቲባ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ
    —–

    የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኢብራሂም ዑስማን ከኃላፊነታቸው ለመልቀቅ ለከተማ አስተዳደሩ ያቀረቡት ጥያቄ በምክር ቤቱ ተቀባይነት አገኘ።

    የኢትዮጵያ ሶማሌ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢሶሕዴፓ) አባል የሆኑት አቶ ኢብራሂም ለሦስት ዓመታት ከመንፈቅ በከንቲባነት ያገለገሉ ሲሆን፣ በተደጋጋሚ በሚደረጉ ሠልፎች ተቃውሞ ይቀርብባቸው ነበር።

    ምክር ቤቱ በምትካቸው አቶ መሐዲ ዲሬን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ በማድረግ ሹሟል።

    ምንጭ፦ ሪፖርተር ጋዜጣ

    Anonymous
    Inactive

    አየር መንገዱ በአደጋው ማዘኑንና ለተጎጂ ቤተሰቦች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ
    —–

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአውሮፕላን መከስከስ አደጋው ማዘኑንና ለተጎጂ ቤተሰቦች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ።

    አደጋውን አስመልክቶ የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳብራሩት አውሮፕላኑ ከጠዋት 2 ሰዓት ከ38 ደቂቃ ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ቢነሳም ከስድስት ደቂቃ በኋላ ከራዳር ውጪ ሆኗል።

    አውሮፕላኑ 149 ተሳፋሪዎችንና ስምንት የበረራ ሰራተኞችን ይዞ ሲጓዝ በነበረበት ወቅት በቢሾፍቱና ሞጆ መካከል በምትገኘው ኤጄሪ አካባቢ መከስከሱን ነው ያስረዱት።

    አየር መንገዱ ቦይንግ 737 የተሰኘውን ይህን አውሮፕላን ከአራት ወራት በፊት መረከቡን ገልፀው ከአውሮፕላኑ አዲስነት በተጨማሪ በበረራው የተሳተፉት አብራሪውና ረዳቱ ልምድ ያላቸው መሆናቸውን ተናግረዋል።

    አውሮፕላኑ ባለፈው ወር ምርመራ እንደተደረገለትና ከደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ከበረራ የተመለሰ መሆኑንም አስረድተዋል።

    ከጆሃንስበርግ መልስ ለሶስት ሰዓታት እረፍት ማድረጉንና በዚህም ወቅት የቴክኒክ ምርመራ ተደርጎለት እንደነበርም ዋና ስራ አስፈፃሚው ገልፀዋል።

    ይሁንና የአውሮፕላኑ አብራሪው ችግር ገጥሞት እንደነበር ለአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች አሳውቆ እንደነበር ነው አቶ ተወልደ የተናገሩት።

    የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን የተናገሩት አቶ ተወልደ በአደጋው 32 ኬኒያውያን፣ 18 ካናዳዊያን፣ 17 ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም የሌሎች አገራት ዜጎች ተሳፍረው እንደነበር ነው የገለፁት ።

    አየር መንገዱ ለሟች ቤተሰቦች የሚችለውን እንደሚያደርግ የተናገሩት አቶ ተወልደ ለመንገደኞችና ለሰራተኞቹ ቤተሰብና ወዳጅ ዘመዶች መፅናናትን ተመኝተዋል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ

Viewing 15 results - 511 through 525 (of 730 total)