Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Home Forums Search Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Viewing 15 results - 571 through 585 (of 730 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን በማጎ እና ኦሞ ብሔራዊ ፓርኮች ላይ ያሉ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ለመፍታት በጥር 28 ቀን የተጀመረው ውይይት መድረክ ጥር 29 ቀን 2011 ዓ.ም. ከቀኑ 7:00 ሰዓት ላይ ተጠናቋል።

    በውይይቱ ወቅት ፓርኮቹ ከሚያዋስኗቸው ዞኖችና ወረዳዎች የተወከሉ የአካባቢው ሽማግሌዎች እና የጽህፈት ቤት ኃላፊዎች በስፋት ሐሳባቸውን አንሸራሽረዋል።

    ኦሞ ኩራዝ የስኳር ፋብሪካ፣ አርብቶ አደሩ እና የጥበቃ ቦታዎቹ በተቀናጀ መልኩ ችግሩን ለመፍታት መሥራት እንደሚኖርባቸው ተገልጧል። የመንገድ፣ መብራት፣ ትምህርት፣ ውሃ እና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን በቀጠናው በማስፋፋት የአካባቢውን ማኅበረሰብ ልማት ተጠቃሚነት በማስፋት በፓርኩ ላይ የሚደርስ ጫና መቀነስ እንደሚገባው የአካባቢው ኗሪዎች አሳወቀዋል።

    ቪዲዮ፦ የአሜሪካ መንግስት ለታሪካዊው የአባ ጅፋር ቤተ መንግስት እድሳት የሚሆን 335,000 ዶላር ልገሳ አደረገ

    የአገር ሽማግሌዎች እንደገለጡት፤ ላለፉት ሀምሳ ዓመታት ከፓርኮቹ ጋር በሰመረ መልኩ ኖረናል። ፓርኩ ዛሬ የመጣ ጉዳይ አይደለም የፓርኩ ህልውና የእኛ ህልውና እንደሆነ እንገነዘባለን። የስኳር ፕሮጀክቱም ቢሆን በተቀናጀ እና በተጠና መልኩ ከተተገበረ ጠቀሜታ እንዳለው እናምናለን ብለዋል። ሆኖም ግን የቅንጅት አሠራር ላይ በተለይም የፓርክ አስተዳደር እና ስኳር ፕሮጀክት በሚጠበቀው ልክ ባለመቀናጀታቸው ችግሮች መፈጠራቸውን እና ሁኔታውም በዚህ መልኩ የሚቀጥል ከሆነ አደጋው የከፋ እንደሚሆን አስረድተዋል።

    ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተዋረድ ኃላፊነቱን መወጣት ይኖርበታል። ከፌዴራል እስከ ቀበሌ ድረስ የሚጠበቅባቸውን መወጣት አለባቸው ሲሉ በአካባቢው ኗሪዎች በኩል የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ ቃል ገብተዋል። ተሳታፊዎቹ አጽንኦት ሰጥተው የገለጡት ጉዳይ፤ በየመድኩ የሚደረጉ ይህንን መሰል ውይይቶች የጋራ መግባባት ላይ ለመድረስ ፋይዳቸው የላቀ ቢሆንም በሚፈለገው ልክ ወደ ሥራ መውረድ ካልተቻለ በራሱ መድረክ ውጤታማ አያደርገንም የሚለው ዋናው ነው።

    በዚህ ጉዳይ ዙሪያ በርካታ ድረኮች መካሔዳቸውን በመጠቆም ከውሳኔው በኋላ ወደ መሬት ሊወርድ እንደሚገባ አሳስበዋል። ከዱር እንስሳት ቲንክ ታንክ ቡድን እና ከሌሎች ተቋማት የመጡ ባለሙያዎችም ከሁለቱ ፓርኮች ባሻገር የታማ ጥብቅ ስፍራ (Tama Wildlife Reserve) ከፍተኛ የብዝሃ ሕይወት ሀብት ያለው በመሆኑ ትኩረት ተሰጥቶት ጥበቃ ሊደረግለት እንደሚገባ ገልጠዋል።

    በማጎ ብሔራዊ ፓርክ ውስጥ በቅርብ ጊዜ የተከሰተውን የጥበቃና ቁጥጥር ሠራተኛ ግድያም አስመልክቶ የሚመለከታቸው አካላት ህገወጦችን ለፍርድ ማቅረብ እንደሚኖርባቸው ተመልከቷል።

    በተጨማሪም በውይይቱ የተደረሰበትን ውሳኔ ተከታትሎ በማስፈጸም ውጤታማ መሆን እንደሚኖርበት የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል። በቀጣይም በመስክ ሥራዎች የተገኙ ውጤቶች ላይ በተከታታይ ግምገማ ማካሄድ እንዳለበት ተገልጧል።

    በመጨረሻም ስኳር ኮርፖሬሽን ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እና ከክልሉ ጋር በስፋት ተወያይተው የጋራ መግባባት ላይ መድረስ እንደሚገባ ስምምነት ላይ ተደርሷል። መድረኩ የውይይቱን አጠቃላይ ሐሳብ የያዘ ባለስምንት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተቋጭቷል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን (EWCA) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን


    Anonymous
    Inactive

    ግብርን በመክፈል አገራዊ ለውጡን ማገዝ ይገባል — የደቡብ ክልል ገቢዎች ባለስልጣን
    —–

    የንግዱ ማህበረሰብ የሚጠበቅበትን ግብር በወቅቱ በመክፈል የተጀመረውን አገራዊ ለውጥ እንዲያግዝ የደቡብ ክልል ገቢዎች ባለስልጣን ጠየቀ።

    ክልል አቀፍ የታክስ ንቅናቄ በወልቂጤ ከተማ ተጀምሯል ።

    ባለስልጣኑ ዋና ዲያሬክተር አቶ ንጉሴ አስረስ በወቅቱ እንደገለጹት በግብር አሰባሰቡ ሂደት ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን በመፍታት የክልሉ ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ መሰብሰብ ትኩረት ተሰጥቷል።

    “የክልሉ ህብረተሰብ በተለይም ግብር ከፋዩ የታክስ ስወራና ማጭበርበርን በመከላከል የገቢ አሰባሰቡ ስኬታማ እንዲሆን ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል” ብለዋል ።

    ”የህዝቡ የልማት ጥያቄ ሊመለስ የሚችለው የንግዱ ማህበረሰብ ገቢውን በማሳወቅ የሚጠበቅበትን ግብር መክፈል ሲችል ነው” ያሉት ኃላፊው ግብር ከፋዩ ኃላፊነቱን በመወጣት ለውጡን እንዲያግዝ ጠይቀዋል ።

    “ተጠቃሚውም ደረሰኝ በመጠየቅ የድርሻውን ሊወጣ ይገባል” ብለዋል።

    በገቢዎች ሚኒስቴር የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ወልደመሰቀል በበኩላቸው “የታክስ ጉዳይ የግብር ሰብሳቢው ተቋም ብቻ ሳይሆን፤ የሁሉም ዜጎች በመሆኑ ህዝቡ ከሚመለከተው አካል ጋር በጋራ ሊሰራ ይገባል” ብለዋል ።

    “ስራ አጥ ወጣቶችን የስራ እድል ባለቤት ማድረግና የመሰረተ ልማት ተቋማትን ማስፋፋት የሚቻለው ተገቢውን ገቢ መሰብሰብበ ሲቻል ነው” ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ኮሚሽን የሐዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ታደሰ መርዕድ ናቸው ።

    ተገቢውን ግብር ለመሰብሰብ እንዳይቻል የሚያደርጉ በርካታ ጉዳዮች እንዳሉ የጠቆሙት አቶ ታደሰ ህገወጥ ንግድ፣ የኮንትሮባንድ ታክስ ማጭበርበር ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።

    በገቢና በወጪ ንግዱ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያስከተለ ያለውን የኮንትሮባንድ ንግድ ለመከላከል ህዝቡ ከመንግስት ጎን ሊቆም እንደሚገባ አሳስበዋል።

    የጉራጌ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪና የዞኑ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ታጁ ናስር በበኩላቸው በዞኑ ባለፉት ስድስት ወራት ለመሰብሰብ ከታቀደው 918 ሚሊዮን ብር ውስጥ 362 ሚሊዮን ብር ብቻ መሰብሰቡን ተናግረዋል ።

    ግብይትን ያለደረሰኝ ማካሄድ፣ የንግድ ፈቃድን በቤተሰብ ከፋፍሎ ማውጣት፣ የታክስ ስወራና ማጭበርበር ዕቅዱን እንዳይሳካ ያደረጉ ምክንያቶች መሆናቸውን ጠቁመዋል ።

    የወልቂጤ ከተማ የሰላም በር ትምህርት ቤት የታክስ ክበብ አባል ተማሪ አያልነሽ አይተንፍሱ “ግብር ያለ ማጭበርበርና በስርዓት መክፈል አገርን ከድህነት እንድታድግ ያስችላል” ብላለች ።

    ግብርን አለመክፈል አገራዊ እድገትን እንደሚጎዳም ገልጻለች ።

    ግዴታዬን እወጣለሁ መብቴን እጠይቃለሁ!” በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ክልል አቀፉ የታክስ ንቅናቄ እስከ የካቲት 30 ቀን 2011 ድረስ ይቆያል።

    የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት

    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት በቅርቡ ዋና ካምፓሱን በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፍቼ ከተማ በምድረግ ከተመሠረተው ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ጋር አብሮ ለመሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መለሰ ማርዮ እና የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገናናው ጎንፌ ጥር 8 ቀን 2011 ዓ.ም. በኢንስቲትዩቱ አዳራሽ እውቀትን ለማሸጋገር፣ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በጋራ ለማከናወን የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል።

    የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መለሰ ማርዮ በስምምነት ፊርማው ላይ ባደረጉት ንግግር እንዳስታወቁት የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና የምርምር ተቋማት ጋር አብሮ ሊያሠራው የሚችል ስምምነቶችን በመፈራረም የተለያዩ ተግባራትን ለማከናወን መቻሉን ገልጸዋል። ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በዱረም ስንዴ ላይ በተሠራው ሥራ ከፍተኛ ምርት የሚሰጥና ድርቅን መቋቋም የሚችል ውጤት መገኝቱን፤ ከጎንደር ዩኒቨረሲቲ ጋር በመተባበር በደን ልማት ላይ እየተሠራ መሆኑን እና ከዲላ ዩኒቨረሲቲ ጋርም በመተባበር ለምርምርና ለቱሪስት መስህብ የሚውል የቦታኒክ ጋርደን ግንባታ ሥራ ከተከናወኑ ተግባራት መካከል የሚጠቀሱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

    VIDEO: Ethiopia: After mandatory preparations, Selale University accepts incoming students

    የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገናናው ጎንፌ በበኩላቸው ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በቅርብ ጊዜ ሥራ የጀመረ፣ እየሰፋ የሚሂድና ለግብርና እና የአካባቢ ጥበቃ ልዩ ትኩረት የሚሰጥ ነው። የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ካለው መልካአ ምድራዊ አቀማመጡ ጋር በተያያዘም በእንስሳት ዝርያ አጠባበቅ በተለይም የተለያዩ ዝርያዎችን በማዳቀል ለአዲስ አበባ ከተማ 50 በመቶ የሆነውን የወተት ምርት የሚያቀርበው የሰላሌ አርሶ አደርን ተጠቃሚ ለማድረግ ከኢንስቲትዩቱ ጋር አብረው ለመሥራት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

    ዶ/ር ገናናው አክለውም ስምምነቱ የወረቀት ላይ ስምምነት ብቻ እንዳይሆን ለማድረግና የብዝሀ ሕይወት ጥበቃ ሥራዎችን ለሕብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ከመማር ማስተማር ሥራው ጎን ለጎን የአካባቢውን ማሕበረሰብ ተጠቃሚ የማድረግ ሥራ ለማከናወን ዩኒቨርሲቲው መዘጋጀቱን ገለጸዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦  

    የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት


    Anonymous
    Inactive

    ኢትዮጵያ የኤሌክትሮኒክስ ግብይትን ለመዘርጋት የጀመረችውን ስራ ዴንማርክ እንድታግዝ ጠየቀች፡፡
    —–

    በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ካሪን ፖውልሰን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎች ጋር በግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያና በኤሌክትሮኖክስ ግብይት ዙሪያ ምክክር አድርገዋል፡፡

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ኢትዮጵያ የጀመረችውን የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ዴንማርክ እንድታግዝና ቴክሎጂን በሚጠቀም የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ዘረፍ እንድትሳተፍ ጠይቃዋል፡፡

    1ቢሊየን ዶላር ገደማ የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኘውን ቡና እሴት ጨምሮ በኤሌክትሮኖክስ ግብይት ወደ ገበያ ማቅረብ ቢጀመር ገቢውን በ4 እና 5 እጥፍ ማሳደግ እንደሚቻል ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

    የኤሌክትሮኒክስ ግብይትን በኢትዮጵያ ለመጀመር የአለም አቀፉ ፖስታል ድርጅት ቴክኒካል ኮሚቴ ጥናት መጀመሩ ይታወሳል፡፡

    የኢትዮጵያ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ያዘጋጁት የዘንድሮው ውድድር ለ2ኛ ጊዜ የተካሄደ ሲሆን፥ በባለፈው ዓመት የተመረጠችው ወ/ሪት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በአማራ ክልል በተካሄደው የቁንጅና ውድድር ላይ ተሳትፋ 3ኛ ደረጃ መውጣቷም ተገልጿል።

    ደብረ ብርሃን (ሰሞነኛ)– በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ‹‹ቱሪዝም ለአካባቢ እንክብካቤና ለማኅበረሰብ አቅም መጎልበት›› በሚል መሪ ቃል ሲከበር የቆየው የቱሪዝም ሳምንት ጥር 24/2011 ዓ/ም የቁንጅና ውድድር በማካሄድ ተጠናቀቀ።

    በውድድሩም ወ/ሪት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ያብፀጋ አይነኩሉ ከሁለተኛ ዓመት የሎጅስቲክና ሰፕላይ ቼን ማኔጅመንት (Logistics and Supply Chain Management) ትምህርት ክፍል ተመርጣለች። በሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ኤልሳቤጥ ደስታ የ3ኛ ዓመት የባዮቴክኖሎጂ (Biotechnology) እና በሦስተኛነት ደረጃ ተማሪ ትንሳኤ ፀጋዬ አንደኛ ዓመት የሳይኮሎጂ (Psychology) ትምህርት ክፍል እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።

    VIDEO: The Yellow Movement AAU: Speaking up for women and girls – empowering women (Ethiopia)

    የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዘዳንት ተወካይ ዶ/ር ጌትነት አሸናፊ በፕሮግራሙ መዝጊያ ላይ ተገኝተው እንደገለጹት የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ከሳምንት በፊት ጀምሮ በዩኒቨርስቲው ግቢና ውጪ ያለውን አካባቢ በማጽዳት ለሌሎች ምሳሌ የሚሆኑ ተግባራት በማከናወን የቆዩ መሆናቸውን በመግለፅ ላደረጉት በጎ ተግባር ምስጋና አቅርበዋል።

    የቱሪዝም ማኔጅመንት የትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ አብርሃም ኪዳኔ እንደገለፁት የዘንድሮው ውድድር ለ2ኛ ጊዜ የተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው፥ በባለፈው ዓመት የተመረጠችው ወ/ሪት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በአማራ ክልል በተካሄደው የቁንጅና ውድድር ላይ ተሳትፋ 3ኛ ደረጃ በመውጣቷ በርካታ ሽልማቶችን ያገኘች መሆኗን ተናግረዋል።

    በመጨረሻም ለጓሳ ማኅበረሰብ ጥብቅ ስፍራ መታሰቢያነት ‹‹ቱሪዝም ለአካባቢ እንክብካቤና ለማህበረሰብ አቅም መጎልበት›› በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የቱሪዝም ሳምንት 8 /ስምንት/ ተወዳዳሪዎችን ያሳተፈው የቁንጅና ውድድር ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ የወጡትን አሸናፊዎችን በመምረጥና እውቅና በመስጠት በዓሉ ተጠናቋል።

    ምንጭ፦ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የሰጣቸው ምሁራን በመማር ማስተማሩ፣ በጥናትና ምርምር፣ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አገልግሎት እንዲሁም በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት በዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሊጅስሌሽን መሰረት የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ ስለተወጡ ነው።

    አዲስ አበባ (አ.አ.ዩ)– በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሚመለከታቸው የትምህርት ክፍሎች ተመርመሮ፣ በየኮሌጆች አካዳሚክ ጉባዔዎች ተፈትሾ፣ አጥጋቢ በሆነ መልኩ ተገመግሞ በዩኒቨርሲቲው ሴኔት ታይቶ እና ይሁንታ አግኝቶ የቀረበለትን መረጃ የተመለከተው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ጥር 26 ቀን 2011 ዓ.ም. የዶ/ር ሂሩት ወልደማርያምን፣ የዶ/ር ተፈሪ ገድፍን፣ የዶ/ር ምሩፅ ግደይን፣ የዶ/ር ሃጎስ አሸናፊን፣ የዶ/ር መረራ ጉዲናን እና የዶ/ር ጌታቸው አሰፋን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አፅድቋል። ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው 6 መምህራን አጭር መግለጫ እንደሚከተለው ነው።

    1. ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም የመጀመርያ፣ ሁለተኛ እና የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በቋንቋ ጥናት (Linguistics) ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል።

    ፕሮፌሰር ሂሩት በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ6 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 42 ነጥብ አስመዝገበዋል። በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሂዩማኒቲስ፣ የቋንቋዎች ጥናት፣ የጆርናሊዝምና የኮሚዩኒኬሽን ኮሌጅ የቋንቋ ጥናት ትምህርት ክፍል ባልደረባ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

    2. ፕሮፌሰር ተፈሪ ገድፍ የመጀመርያና ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ዲግሪያቸውን በፋርማሲ (Pharmacy) ትምህርት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በፋርማሲ ትምህርት በጀርመን ከማርቲን ሉተር ሐለ-ቪተንበርግ ዩኒቨርሲቲ (Martin Luther University Halle-Wittenberg) አግኝተዋል።

    ፕሮፌሰር ተፈሪ በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ20 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 104.56 ነጥብ አስመዝገበዋል። በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ፕሮፌሰር ተፈሪ ገድፍ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሳይንስ ኮሌጅ የፋርማሲ ትምህርት ክፍል መምህር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

    ቪዲዮ፦ ኢትዮጵያ ውስጥ ትምህርት ቤቶች አካባቢ የሚከፈቱ የጫት እና የሁካ ቤቶች ተማሪዎች ለሱሰኝነት እየዳረጓቸው ነው

    3. ፕሮፌሰር ምሩፅ ግደይ የመጀመርያ ዲግሪያቸውን በባዮሎጂ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በባዮዳይቨርሲቲ (Biodiversity) ከ ከስዊድን የእርሻ ዩኒቨርሲቲ (Swedish University of Agricultural Sciences)፣ እንዲሁም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ቦታኒካል ሳይንስ (Botanical Science) ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል።

    ፕሮፌሰር ምሩፅ በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ18 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 56 ነጥብ አስመዝገበዋል። በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ፕሮፌሰር ምሩፅ ግደይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአክሊሉ ለማ የፓቶባዮሎጂ ኢንስቲትዩት (Aklilu Lemma Institute of Pathobiology) በእንዶድና ሌሎች የመድሃኒት ዕጽዋት የምርምር ማዕከል (Endod and Other Medicinal Plants Research Unit) ባልደረባ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

    የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ

    4. ፕሮፌሰር ሃጎስ አሸናፊ የእንስሳት ህክምና ዲግሪያቸውንና የሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በቤልጄም ከሉቨን የካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ (Catholic University of Leuven) አግኝተዋል።

    ፕሮፌሰር ሃጎስ በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ24 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 94.06 ነጥብ አስመዝገበዋል። በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ፕሮፌሰር ሃጎስ አሸናፊ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በእንስሳት ህክምና እና ግብርና ኮሌጅ የፓቶሎጂና ፓራሲቶሎጂ (Pathology and Parasitology) ትምህርት ክፍል መምህር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

    5. ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና የመጀመርያ ዲግሪያቸውን በፖለቲካ ሳይንስ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከአሜሪካን ዩኒቨርሲቲ ኢን ካይሮ (The American University in Cairo)፣ እንዲሁም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በፖለቲካ ሳይንስ ከኤራስመስ ዩኒቨርሲቲ ሮተርዳም ኢንስቲትዩት ኦፍ ሶሻል ስተዲስ (Erasmus University Rotterdam – Institute of Social Studies) አግኝተዋል።

    ፕሮፌሰር መረራ በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ12 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 37.25 ነጥብ አስመዝገበዋል። በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሶሻል ሳይንስ ኮሌጅ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለማአቀፍ ግንኙነት (Political Science and International Relations) ትምህርት ክፍል መምህር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

    6. ፕሮፌሰር ጌታቸው አሰፋ የህክምና ዲግሪያቸውን (Doctor of Medicine) ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የስፔሻሊቲ ዲግሪያቸውን በራዲዮሎጂ (Radiology) ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ እንዲሁም የሰብ-ስፔሻሊቲ ዲግሪያቸውን በኒሮራዲዮሎጂ (Neuroradiology) በኦስትሪያ ከሜዲካል ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቭየና (Medical University of Vienna) አግኝተዋል።

    ፕሮፌሰር ጌታቸው በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ17 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 75.25 ነጥብ አስመዝገበዋል። በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ፕሮፌሰር ጌታቸው አሰፋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሳይንስ ኮሌጅ የዲያጎነስቲክ ራዲዮሎጂ (Diagnostic Radiology) ትምህርት ክፍል መምህር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

    አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የሚሰጣቸው ምሁራን በመማር ማስተማሩ፣ በጥናትና ምርምር፣ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አገልግሎት እንዲሁም በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት በዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሊጅስሌሽን መሰረት የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ ለተወጡ እና ለዓለም የዕውቀት ስርጸት መዳበር ስኬታማ አበርክቶ ላደረጉ ነው።

    ምንጭ፦ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ


    Anonymous
    Inactive

    የኤሌክትሮኒክስ ግብይት በኢትዮጵያ ለመጀመር የአለም አቀፉ የፖስታ ድርጅት ቲክኒካል ኮሚቴ ጥናት ጀመረ፡፡
    —–

    አፍሪካን በተለያዩ ቀጠናዎች ከፍሎ የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ለመጀመር እየሰራ የሚገኘው ዓለማቀፍ የፖስታ ኅብረት (Universal Postal Union) አጥኚ ቡድኑን ወደ ኢትዮጵያ የላከው ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በተፈራረመው ስምምነት መሰረት ነው፡፡

    ቡድኑ የኢትዮጵያ ዝግጁነት ከፖሊሲ፣ ከመሰረተ ልማትና ከኢ-ታክስ አኳያ፤ ኢትዮጵያ ስርዓቱን ለመዘርጋት ምን ማድረግ አለባት፣ ትግበራውን በምን መልኩ መከናወን ይኖርበታል የሚሉትንና የመሳሰሉትን ጉዳዮች ያጠናል፡፡

    የግብይት ስርዓትን ለማዘመን፣ ገዢና ሻጭን በቀጥታ ለማገናኘት፣ ቀጠናዊ ትስስር ለመፍጠር፣ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ሃብት ለማሳደግ ትልቅ ጠቀሜታ ይኖረዋል ተብሎ የሚታሰበው የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ስርዓት በኢትዮጵያ በቅርቡ ተግባራዊ ለማድረግ ርብርብ እንደሚደረግ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ተናግረዋል፡፡

    የአለም አቀፉ የፖስታል ድርጅት የምስራቅ አፍሪካ ማዕከሉን ኢትዮጵያ ውስጥ ለመገንባት ማቀዱ ይታወሳል፡፡

    በ2017 በአፍሪካ በኤሌክትሮኒክስ ግብይት ከ85 ቢሊየን እስከ 100 ቢሊየን ዶላር የገበያ ድርሻ ይይዛል ተብሎ ይገመታል፡፡

    የኢትዮጵያ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

    Anonymous
    Inactive

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ግጭት ላለባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አርአያ ነው — አፈ ጉባዔ ኬሪያ ኢብራሂም
    —–

    በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ያለው ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ሌሎች ግጭት ላለባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አርአያ እንደሆነ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ገለፁ።

    በዞኑ ያለው ሰላምና መረጋጋት በተምሳሌትነት የሚጠቀስ መሆኑን አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም ተናግረዋል።

    በደቡብ ብሔር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ውስጥ የሚገኙ 16 ብሄረሰቦች የተሳተፉበት የባህል ፌስቲቫል ጥር 27 ቀን 2011 ዓ.ም. በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ተካሄዷል።

    ፌስቲቫሉ በዞኑ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀ ሲሆን “ባህላዊ እሴቶች ለአብሮነትና ለልማት” በሚል መሪ ቃል ነው የተካሄደው።

    አፈ ጉባዔዋ ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም በፌስቲቫሉ መክፈቻ ላይ እንደገለጹት፤ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ያለው ሰላምና መረጋጋት ለመማር ማስተማር ስራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተ በመሆኑ ለሌሎች ግጭት ላለባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አርአያ ነው።

    በርካታ ብሄረሰቦች የሚኖሩበት ዞኑ በአካባቢው ያለው ሰላምና መረጋጋት በአገር አቀፍ ደረጃ በተምሳሌትነት የሚጠቀስ ነውም ብለዋል።

    በዩኒቨርሲቲው የተካሄደው ፌስቲቫል በዞኑ ያለውን ቋንቋ፣ ባህልና ታሪክ ለማስተዋወቅ የሚረዳ መልካም ተግባር እንደሆነም ተናግረዋል።

    እንዲሁም የዞኑን ባህልና እሴቶች ለሌሎች አካላት ለማሳወቅ የጀመራቸው የጥናትና ምርምር ስራዎች ወሳኝ መሆናቸውን አንስተዋል።

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ እንዳሉት፤ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ አካባቢያዊ ጥናትና ምርምሮች ወሳኝ ሚና ያላቸው በመሆኑ አገር በቀል እውቀትን ለተማሪዎችና ለኀብረተሰቡ ለማሳወቅ ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የጀመረው ጥናትና ምርምር ያለው ፋይዳ የጎላ ነው።

    ዩኒቨርስቲው በሳይንስና ቴክኖሎጂ በመደገፍ በተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ለሚማሩ ተማሪዎች በኮምፒዩተር አማካይነት የሚሰጠውን መጽሕፍ አቅርቦት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አሳስበዋል።

    ዩኒቨርሲቲው በዞኑ ባህልና እሴቶች ላይ ለሚካሄዱ ጥናትና ምርምሮች የልህቀት ማዕከል በመሆን ማገልገል እንዳለበት ፕሮፌሰር አፈወርቅ ጠቁመዋል።

    የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ገብሬ ይምቲሶ በበኩላቸው ከዚህ በፊት በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ ብሄረሰቦች የሚያስተዋውቅ ፌስቲቫል ባለመካሄዱ የብሔረሰቦቹን ባህልና እሴት በማስተዋወቅ ረገድ የሚፈለገው ያህል አልተሰራም ብለዋል።

    በዚህም ምክንያት ዩኒቨርሲቲው የሚጠበቅበትን ማህረሰባዊ አገልግሎት ለኀብረተሰቡ አለመስጠቱን ተናግረዋል።

    ዘንድሮ የባህል ፌስቲቫሉ ለመጀመሪያ ጊዜ መዘጋጀቱ 16ቱ ብሔረሰቦች እርስ በርስ እንዲተዋወቁና የባህል ልውውጥ እንዲያደርጉ ምቹ አጋጣሚ የፈጠረ በመሆኑ ወደፊት ቀጣይነት ባለው መልኩ እንደሚካሄድም አመልክተዋል።

    የፌስቲቫሉ ዓላማ በዞኑ የሚገኙ ብሔረሰቦችን ከማቀራረብ ባሻገር ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የመጡ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የ16ቱን ብሔረሰቦች ቋንቋ፣ ባህልና እሴት እንዲያውቁ ማድረግ እንደሆነም ገልጸዋል።

    እንዲሁም በዞኑ ግጭቶች ሳይከሰቱ የአገር አንድነትና ሰላም ለማስጠበቅ ወሳኝ ሚና እንዳለውም ፕሮፌሰር ገብሬ አስረድተዋል።

    በፌስቲቫሉ የዞኑ ብሔረሰቦች የምግብ፣ የሙዚቃና የዕደ-ጥበብ ስራዎች ለእይታ የቀረቡ ሲሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ተገኝተዋል።

    የደቡብ ኦሞ ዞን በባህል ብዝሃነት የሚታወቅና በበርካታ የውጭ አገር ዜጎች የሚጎበኝ አካባቢ ነው።

    የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት

    Anonymous
    Inactive

    የጊዳቦ ግድብና መስኖ ልማት ፕሮጀክት ተመረቀ
    —–
    ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የጊዳቦ ግድብና መስኖ ልማት ፕሮጀክትን መርቀው ከፈቱ።

    በ2002 ዓ.ም ግንባታው የተጀመረው የጊዳቦ ግድብና መስኖ ልማት ፕሮጀክት በሁለት ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል ቢባልም ከተባለለት ስድስት ዓመት ዘግይቶ ዛሬ ተመርቋል።

    ከአዲስ አበባ በ365 ኪሎ ሜትር ርቀት፣ ከዲላ ከተማ አቅራቢያ ጊዳቦ በተሰኘ የደቡብና የኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ ቦታ ላይ ነው ግድቡ የተገነባው።

    በሁለት ዓመታት ውስጥ ግንባታው እንደሚጠናቀቅ ታቅዶና በ258 ሚሊዮን ብር በጀት የተጀመረው የጊዳቦ ግድብና መስኖ ልማት ፕሮጀክት በ1 ነጥብ 26 ቢሊዮን ብር ተጠናቋል።

    ግድቡ ከ63 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር በላይ ውኃ የመያዝ አቅም ሲኖረው 13 ነጥብ 5 ሺህ ሄክታር መሬት በመስኖ ለማልማት ያስችላልም ተብሏል።

    በግድቡ ግራና ቀኝ ዋና ዋና የውኃ ቦዮች መገንባታቸውና በአሁኑ ወቅትም ከ1 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ያካለለ ውኃ በግድቡ መጠራቀሙም ታውቋል።

    በምርቃቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድና የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጅነር ስለሺ በቀለን ጨምሮ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳ፣ የደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ፣ የሁለቱ አጎራባች ክልሎች ነዋሪዎች፣ አባ ገዳዎችና ሌሎችም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

    የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ዋልታ)– ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ ድርጅቶች የሚመረቱ የታሸጉ ውሃዎች ላይ ሁነኛ የሆነ የጥራት ችግር እንዳለ ተገለፀ።

    በአገሪቱ ለመጠጥ ውሃ የሚውሉት የታሸጉ ውሃዎች ላይ በሚታየው የጥራት መጓደል ምክንያትም በኅብረተሰቡ ላይ አሉታዊ የጤና ችግር መንስዔ ከመሆናቸው ባሻገር አገሪቱ ማግኘት ያለባትን ገቢ አለማግኘቷም ተገልጿል።

    የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ በውሃ ምርቶች ላይ የሚስተዋሉትን ችግሮችና የጥራት ማስጠበቅ ሥራዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ጥር 23 ቀን 2011 ዓ.ም. አካሄዷል።

    ቪዲዮ፦ የታሸጉ ውሃዎች በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ የመጣው ፍላጎት እና የውሃዎቹ ያልተመጣጠነ ዋጋ

    በመጠጥ ውሃ የፕላስቲክ ማሻጊያዎቹ ክዳን ላይ የሚለጠፉትና ከፍተኛ የውጭ ምናዛሬን የሚጠይቁ ግብዓቶች ተመሳስለው በሀገር ውስጥ የሚሠሩ በመሆኑ የማሸጊያዎችም የምርት ጥራት ላይ ችግር እየተስተዋለ በመሆኑ ይህን ለማስቀረት እየተሠራ ይገኛል።

    በሀገሪቱ እየተስፋፉ ያሉ የውሃ ማምረቻ ተቋማት ንፁ ውሃን በማቅረብ እና ኢኮኖሚውን ከመደገፍ አንጻር አበረታታች ሥራ ቢሠሩም አሁንም ግን ዘርፉ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚንስትር ዴኤታ አቶ እሸቱ አስፋው ተናግረዋል።

    በርካታ በሀገሪቱ የሚኖሩ ኤምባሲዎችና የውጭ ኮሚኒቲ አካላት የታሸጉ ውሃዎችን ወደ አገር ውስጥ እያስገቡ በመሆኑ፤ በዘርፉ ያለውን የጥራት ችግር ያሳያል።

    የምርቶቹን የጥራት ደረጃ በማሻሻል ለውጭ ገበያ እንዲቀርቡ በማድረግ ሀገሪቱን ከዘርፉ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ለማሳደግ መሥራት እንደሚገባ ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል።

    የምርቶችን የአመራረት፣ የአስተሻሸግ፣፤ የማጓጓዝ እና የአቀማመጥ ሆነ ለገበያ በሚቀርቡበት ጊዜ ያለው አያያዝ ችግር ምርቶቹን በከፍተኛ ሁኔታ የጥራት ችግር እንዲጋለጡ ማድረጉን ሚኒስትር ዲኤታው አክለው ገልጸዋል።

    አሁን በሥራ ላይ የሚገኙ ከ 65 በላይ የታሸጉ ውሃ አምራቾች አለም አቀፉን የጥራት ደረጃ በጠበቀ መልኩ እንዲያመርቱ እየተሠራ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ ዳይሬክተር አቶ ይልማ መንግስቱ ተናግረዋል።

    ምንጭ፦ ዋልታ ሚዲያ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የታሸጉ ውሃዎች


    Semonegna
    Keymaster

    ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ የሚያከናውናቸው ምርምሮች በመጠጥ ውሃ፣ በግብርናና በትምህርት መስኮች ላይ እንደሚያተኩሩና የሕዝቡን መሠረታዊ ችግሮች ይፈታሉ ተብለው እንደሚጠበቁ፤ በሥራ ፈጠራ፣ በማጠናከሪያ ትምህርት በግብርናው መስኮች በመሥራት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።

    ሐዋሳ (ኢዜአ)– ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ አገልግሎቱን በማጠናከር ኅብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሠራ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንቱ ገለጹ። ዩኒቨርሲቲው ዘንድሮ በሚያከናውናቸው ምርምሮችና በማኅበራዊ አገልግሎት ዙሪያ ከኅብረተሰቡ ተወካዮች ጋር ተወያይቷል።

    የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሀብታሙ አበበ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው አገልግሎቱን በማጎልበት ኅብረተሰቡን በጥናትና ምርምር ሥራዎቹ ተጠቃሚ እንዲሆን ይሠራል።

    ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ የሚያከናውናቸው ምርምሮች በመጠጥ ውሃ፣ በግብርናና በትምህርት መስኮች ላይ እንደሚያተኩሩና የሕዝቡን መሠረታዊ ችግሮች ይፈታሉ ተብለው እንደሚጠበቁም ገልጸዋል። በሥራ ፈጠራ፣ በማጠናከሪያ ትምህርት በግብርናው መስኮች በመሥራት ላይ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።

    VIDEO: After mandatory preparations, Selale University accepts incoming students

    ይሁን እንጂ ይህን የሚያከናውነው የማኅበረሰብ አገልግሎት እምብዛም ስለማይታወቅ ከኅብረተሰቡ ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር መድረኩ መዘጋጀቱን ዶ/ር ሀብታሙ አመልክተዋል።

    የሐዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አያሌው ዝና በዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰብ አገልግሎት ላይ በቂ ግንዛቤ ባለመፈጠሩ ከማኅበረሰቡና ከዞኑ አስተዳደር ክፍተት መፍጠሩን በዚህም አገልግሎቱን ለማገዝ ሳይቻል መቆየቱን ይናገራሉ። ዩኒቨርሲቲው የሆሳዕና ከተማ በማስተር ፕላን እንድትመራ ለሚያከናውነው ሥራ በሚቀጥለው በጀት ዓመት 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

    የአምብቾ ጎዴ ቀበሌ አባገዳ በቀለ ጅራ እንዳሉት በዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ አገልግሎት ከዚህ በፊት ተወያይተውም ሆነ ተሳትፈው እንደማያውቁ ገልጸው፣ ዘንድሮ የተጀመረው ውይይት ችግሮቻቸውን ለማሳወቅና ለመመካከር አስችሎናል ብለዋል።

    መንግሥታዊ ካልሆነ ድርጅት የመጡት አቶ ዳኛቸው ዓለሙ በበኩላቸው ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ከተመሠረተበት ከ2004 ዓ.ም. ጀምሮ የሚያከናውናቸው የማኅበረሰብ አገልግሎት ሥራዎች አመርቂ መሆናቸውን ገልጸዋል።

    በዩኒቨርሲቲው የሲቪል ምህንድስና ትምህርት ክፍል መምህር አቶ ታምራት ፍቅሬ የሆሳዕና ከተማ ዕድገት ማስተር ፕላኗን በጠበቀ መልኩ ለማከናወን ፕሮጀክት መቀረጹን ተናግረዋል። ፕሮጀክቱ በከተማዋ የሚካሄደው ሕገ ወጥ ግንባታን ለመቆጣጠር እንደሚያስችልም እምነታቸውን ገልጸዋል።

    የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ስርጸት ጉዳዮች ተጠባባቂ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጸደቀ ላምቦሬ ዩኒቨርሲቲው ለሐዲያ ዞን አርሶ አደሮች የተሻሻለና ከፍተኛ ምርት የሚሰጥ የስንዴ ዘር፣ ለደጋማ አካባቢዎች ደግሞ የአፕል ችግኞች እንዲሁም ቡና በማቅረብ ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑ ተናግረዋል።

    አርሶ አደር መልሰው ሐሲቦ ከስድስት ዓመታት በፊት በዩኒቨርሲቲው የቀረበላቸውን አፕል በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን ይናገራሉ። በዓመት ሁለት ጊዜ ምርቱን በመሰብሰብ እስከ አራት ሺህ ብር እንደሚያገኙ ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 

    ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ


    Anonymous
    Inactive

    የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በማይናጋ መሰረት ላይ ለመጣል ግብር ከፋዩ ግዴታውን ሊወጣ ይገባል — ወይዘሮ አዳነች አበቤ
    —–

    የኢትዮጵያን ኢኮኖሚዋ በማይናጋ መሰረት ላይ ለመገንባት ግብር ከፋዩ ህብረተሰብ የውዴታ ግዴታውን ሊወጣ ይገባል ሲሉ የገቢዎች ሚኒስቴር ወይዘሮ አዳነች አበቤ ገለጹ።

    የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የ2011 በጀት ዓመት የግብር ህግ ተገዥነትን ለማሳደግ የሚያስችል የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በባህር ዳር ከተማ አስጀምሯል።

    “ግዴታዬን እወጣለሁ፣ መብቴን እጠይቃለሁ” በሚል መሪ ቃል በተጀመረው የንቅናቄ መድረክ ላይ የተገኙት የገቢዎች ሚኒስትር ወይዘሮ አዳነች አበቤ እንደገለጹት በኩሩ ህዝቦቿ ተጋድሎ ማንነቷ ተከብሮ የኖረችው ኢትዮጵያ በኢኮኖሚው ዘርፍ ድሃ ከሚባሉት አገራት ተርታ ትገኛለች።

    “ይህን ስሟን ለማስቀየርና ኢኮኖሚዋ በማይናጋ መስረት ላይ እንዲገነባ ለማድረግ ግብር ከፋዩ ሕብረተሰብ በፍላጎትና በአገራዊ ፍቅር ስሜት ከሚያገኘው ገቢ ላይ ለመንግስት ግብርን መክፈል አለበት” ብለዋል።

    በአገሪቱ የተከሰተውን ለውጥ ምክንያት በማድረግ ለውጡ ጥቅማቸውን የነካባቸው አካላት ሰላም እንዲደፈርስና የተለያዩ ምክንያቶችን በመፍጠር ግብረ በአግባቡ እንዳይከፈል እያደረጉ መሆኑንም ሚኒስትሯ ተናግዋል።

    ” ግብር ከፋዩ ህብረተሰብ ግብር መክፈል ለራሱና ለሚወዳት አገሩ መሆኑን ተገንዝቦ ኃላፊነቱን ከመወጣት ባለፈ እንደ ጥንት አባቶች አንድነቱን አጠናክሮ መንቀሳቀስ ይኖርበታል ” ብለዋል።

    የአማራ ክልልም ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚያደርገው እንቅስቃሴ የፌዴራል መንግስት ተገቢውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አመልክተዋል።

    ሙሉ ታሪኩን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ገጽ ላይ ያንብቡ

    Anonymous
    Inactive

    የትምህርት ተቋማት የእውቀትና የምርምር መሰረት እንጂ የግጭት ማእከላት መሆን የለባቸውም – አቶ ኦባንግ ሜቶ
    —–

    ትምህርት ቤቶች የእውቀትና የምርምር ተቋም እንጂ የግጭት ማእከላት መሆን የለባቸውም ሲሉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች አቶ ኦባንግ ሜቶ አመለከቱ።

    የትምህርት ተቋማት የግጭት ማእከላት እንዳይሆኑ ለማድረግ ተማሪዎችንና የትምህርት ማህበረሰቡን በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ተዘዋውረው ሊያወያዩ መሆኑንም ገልጸዋል።

    የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ መስራችና ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ከልኡካን ቡድናቸው ጋር በመሆን ላለፉት አምስት ወራት ግጭት በተከሰተባቸው የአገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ላይ ያለውን ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

    ”ለመተማመን እንነጋገር” በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ ለኢዜአ መግለጫ የሰጡት አቶ ኦባንግ፤ ትምህርት ቤቶች የእውቀትና የምርምር ተቋም እንጂ የግጭት ማእከላት መሆን እንደሌለባቸው አስገንዝበዋል።

    ልኡካን ቡድኑ በሰብአዊ መብትና ጥሰት ላይ በስፋት ከህዝብና ከመንግስት ጎን በመሆን ለአምስት ወራት እየሰራ መቆየቱን ጠቁመው ተማሪዎች ለፖለቲካ ግብአትና ብሔርን መሰረት አድርገው ለሚቀሰቅሱ አካላት መጠቀሚያ መሆናቸውን እንደታዘቡ ገልጸዋል።

    በጉብኝታቸው ወቅት የተማሪዎች የመማሪያ ግብአት አለመሟላትና ምቹ የመማር ማስተማር ሁኔታ አለመኖር ሌላኛው የግጭት መንስኤ እንደነበርም አብራርተዋል።

    ትምህርት ቤቶች የግጭት ማእከል እንዳይሆኑ ለመከላከል በትምህርት ቤቶች በመዘዋወር ከቀጣዩ የትምህርት መንፈቅ አመት ጀምሮ የማወያየት ስራ እንደሚጀምሩ ገልጸዋል።

    የየአካባቢው ማህበረሰብ፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ተማሪዎችና መምህራን በሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ላይ ምክክር እንዲያካሂዱ የሚደረግ መሆኑን ጠቁመዋል።

    ከየትምህርት ቤቶቹ አስተዳደር ጋር ውይይቶችን ተከታታይነት ባለው መልኩ የማካሄድ ስራ እንደሚከናወን ገልጸዋል።

    በውጭ አገር ላሉ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና የፖለቲካ ፓርቲዎች መንግስት ወደ አገራቸው እንዲገቡ ባደረገው ጥሪ መሰረት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ መስራችና ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶና ልኡካን ቡድናቸው ወደ አገራቸው መመለሳቸው የሚታወሰ ነው።

    የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ኦባንግ ሜቶና የስራ ባልደረቦቻቸው የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳይፈጸም በተለያየ መድረክ ላይ በመገኘት ግንዛቤ የማስጨበጥ ተግባር እያከናወኑ እንደሚገኙ ይታወቃል።

    የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት

    Semonegna
    Keymaster

    አዳማ (ኢዜአ)–የኢትዮጵያ የምግብ፣ የመድኃኒት እና ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን 22 ነጥብ 78 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው ህገ-ወጥ መድኃኒቶች እንዲወገዱ ማድረጉን አስታወቀ።

    ባለፉት ስድስት ወራት በጤና አገልግሎት ግብአቶች ላይ ቁጥጥርና ፍተሻ ተደርጎ ከ4 ቢሊዮን ብር በላይ መድኃኒትና የህክምና መገልገያ መሣርያዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ መደረጉም ተመልክቷል።

    በባለስልጡኑ የፕሮጀክትና ፕላን ማስተባበሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ዓለም እሸቴ እንዳሉት መስፈርቱን ያላሟሉና ህገ ወጥ የሆኑ መድኃኒቶች ጥቅም ላይ እንዳይውሉና በአግባቡ እንዲወገዱ የተደረገው ባለፉት ስድስት ወራት ነው። መደኃኒቶቹ የተያዙት በመውጫና መግቢያ ኬላዎች ላይ በተደረገ የቤተ-ሙከራ ፍተሻ እንዲሁም በኦዲቲንግ ኢንስፔክሽን ወቅት መሆኑንም ጠቁመዋል።

    ከውጭ ሀገር የሚገቡ መድኃኒቶችን ጥራት፣ ደኅንነትና ፈዋሽነታቸውን ለማረጋገጥ ባለስልጣኑ ከዓለም አቀፍ የፖሊስ ድርጅትና ሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካለት ጋር በመተባበር የቁጥጥር ሥራ ማከናወኑንም ገልጸዋል። በቶጎ ውጫሌ፣ ሞያሌ፣ ቃሊቲ፣ መተማና ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ባለስልጣኑ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

    ወ/ሮ ዓለም አንዳሉት በግማሽ በጀት ዓመቱ የምግብ ጥራትና ደህንነት ቁጥጥር ውጤታማነትን ለማሻሻል በተደረገው እንቅስቃሴም 2ሺህ 389 ሜትሪክ ቶን ዱቄት፣ ሩዝ፣ አኩሪ አተርና የምግብ ጥሬ እቃ ተይዟል።

    “በተደረገ ፍተሻም ምግብና ጥሬ እቃው የመጠቀሚያ ጊዜው በመቃረቡ፣ አምራች ካምፓኒው ባለመታወቁ፣ በጉዞ ወቅት በደረሰ ጉዳትና በነቀዝ በመባላቱ ምክንያት ወደመጣበት አገር እንዲመለስ ተደርጓል” ብለዋል።

    በተጨማሪም ከ200 ሺህ ብር በላይ ግምት ያላቸው ፓስታ፣ ዱቄት፣ ዘይት፣ ብስኩት፣ ጁስ፣ ሩዝ፣ ወተት፣ ፍራፍሬና የምግብ ጥሬ እቃዎች በተለያየ ምክንያት በመበላሸታቸውና አስፈላጊውን መስፈርት ያላሟሉ ሆነው በመገኘታቸው ከንግድ ተቋማት ውስጥ ተሰብስበው እንዲወገዱ መደረጉን ነው ያስረዱት።

    ዘይት፣ ጨው፣ የዱቄት ወተት፣ ጁስና ሌሎች 15 አይነት የምግብ ናሙናዎች ላይ በተካሄደ የቤተሙከራ ምርመራ ሰባቱ መስፈርቱን ሳያማሉ በመቅረታቸው ምርቱ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መደረጉን አስረድተዋል።

    “በመንፈቅ ዓመቱ በጤና አገልግሎት ግብአቶች ላይ ቁጥጥርና ፍተሻ ተደርጎም 4 ነጥብ 23 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው መድኃኒትና የህክምና መገልገያ መሣሪያዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ተደርጋል” ብለዋል። ዋጋቸው ከ457 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ የውበትና የንጽህና መጠበቅያ ምርቶችም ቁጥጥርና ፍተሻ ተደርጎላቸው ሀገር ውስጥ እንዲገቡ መደረጉን አስረድተዋል።

    የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሪት ሄራን ገርባ በበኩላቸው ህገ-ወጥ የጤና አገልግሎትና ግብአቶችን ለመቆጣጠር ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ በስሩ ስድስት ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶችንና 17 የመውጫና መግቢያ ኬላዎችን በማደራጀት እየሠራ ይገኛል።

    በየደረጃው በሚደረጉ የቁጥጥር ሥራዎች ህዝቡን ተሳታፊ ለማድረግ በተለያዩ የህዝብ ንቅናቄ መድረኮች ላይ ህዝብን የማስገንዘብ ሥራ መሠራቱን ወ/ሪት ሄራን ገልጸዋል። በእዚህም ህገ ወጥ የምግብና የመድኃኒት ንግድን እንዴት መከላከል እንደሚቻልና በዘርፉ ቁጥጥር አለማድረግም በሀገር ላይ የሚያስከትለውን ተፅዕኖ ህብረተሰቡ እንዲገነዘበው የማድረግ ሥራ እየተሠራ መሆኑን አመለክተዋል።

    ዳይሬክተሯ እንዳሉት በቁጥጥር ሥራው ካጋጠሙ ችግሮች መካከል የምግብ ቤተሙከራ አለመጠናከር፣ የባለሙያዎች አቅም ውስንነት፣ የባለድርሻ አካላትና የህዝብ ክንፉ ተሳትፎ የተደራጀና የተቀናጀ አለመሆን ይጠቀሳሉ። ይህንን ችግር ለማቃለል የባለስልጣኑን አዋጅ የመከለስ ሥራ እየተጠናቀቀ ሲሆን ከምግብና መድኃኒት ጋር የተጣጣመ የአደረጃጀት ትግበራ፣ የሰው ኃይል ድልድልና የህግ ማዕቀፎች ዝግጀት መደረጉንም አመልክተዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 

    ህገ-ወጥ መድኃኒቶች


    Anonymous
    Inactive

    የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች ፋብሪካ በኢትዮጵያ ሊነባ ነው (አዲስ አድማስ ጋዜጣ)

    ተቀማጭነቱን በቻይና አድርጐ፣ በህክምና መገልገያ መሳሪያዎች ምርትና ሽያጭ፣ በህክምና ዘርፍ ምርምሮች አለም አቀፍ እውቅና ያለው ዋንፎ ካምፓኒ፤ የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች ማምረቻ ፋብሪካውን በኢትዮጵያ ሊያቋቁም ነው፡፡ ፋብሪካው በቂሊንጦ ፋርማሲ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ውስጥ የሚሰራ ሲሆን እ.ኤ.አ አቆጣጠር በ2020 ግንባታው ተጠናቆ ወደ ምርት እንደሚገባ ተገልጿል፡፡

    ቻይናዊው ዋንፎ ካምፓኒ ዴልታ ኢንስትሩመንት ቴክኖሎጂ፣ EZM እና RE4 ኢምፖርት ኤክስፖርት ከተባሉ አገር በቀል አጋሮቹ ጋር በትብብር ለሚያቋቋመው ለዚሁ ፋብሪካ ከ10 ሚሊዮን ዶላር በላይ በጀት መመደቡንና የፋብሪካው ስራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ስራ በሚጀምርበት ወቅት ምርቶቹን ወደተለያዩ የአፍሪካ አገራት በብዛት ለማዳረስ እንደሚያስችል ተገልጿል፡፡

    ኢትዮጵያን የህክምና መሳሪያዎች ማኑፋክቸሪንግ እምብርት ለማድረግ በዝግጅት ላይ እንደሆነ የገለፀው ዋንፎ ካምፓኒ፤ ይህም ለአገሪቱ የስራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሏል፡፡

    ትናንት በሸራተን አዲስ ሆቴል በተካሄደው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተነገረው፤ ዋንፎ ካምፓኒ ከሶስቱ አገር በቀል አጋሮቹ ጋር በመሆን በአፍሪካ እጅግ ተፈላጊ የሆነውን የወባ፣ የኤችአይቪ ኤድስ እና የእርግዝና ምርመራ ማድረጊያ የህክምና መሳሪያዎችን ሌሎች መገልገያ ቁሳቁሶችን ለማምረት የሚያስችለውን ፋብሪካ በአገራችን ያቋቁማል፡፡ ፋብሪካው በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ እንደሚባና ለፋብሪካ ማቋቋሚያው ከተያዘው በጀት 3 ሚሊየን ዶላር የሚሆነው ለፋብሪካ ግንባታው እንደሚውል ተገልጿል፡፡

    አዲስ አድማስ ጋዜጣ

Viewing 15 results - 571 through 585 (of 730 total)