Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Home Forums Search Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Viewing 15 results - 631 through 645 (of 730 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በንሳ ዳዬ ካምፓስ ካለው ርቀትና የመሬት አቀማማጥ አኳያ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ራሱን ወደቻለ ዩኒቨርሲቲ ሊያድግ የሚችል በመሆኑ ግንባታዎቹ ይህንኑን ታሳቢ አድርጎ የተካሄዱ እንደሆነ ታውቋል።

    ሀዋሳ (ሰሞነኛ)– ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ያቋቋመውና ላለፉት 4 ዓመታት በግንባታ ሂዳት ላይ የነበረው የበንሳ ዳዬ ካምፓስ ጥቅምት 30 ቀን 2011ዓ.ም. ወደ ካምፓሱ ለተመደቡ 340 አዲስ ገቢ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል በማድረግ በይፋ ሥራውን ጀምሯል።

    በበንሳ ወረዳ ዳዬ ከተማ ውስጥ ወደተገነባው ካምፓስ ተማሪዎቹ በመጡበት ጊዜ በአከባቢው ማኀበረሰብ ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አቶ አያኖ በራሶ በቦታው በመገኘትለተማሪዎቹ የዩኒቨርሲቲው አባልነታቸውን አረጋግጠውላቸዋል።

    አቶ አያኖ ለተማሪዎች፣ ለአካባቢው ህብረተሰብ እና ለእንግዶች ባስተላለፉት መልዕክት መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በያዘው የትኩረት አቅጣጫ ካምፓሱ የተገነባ ሲሆን ሙሉ በሙሉ ባይጠናቀቅም የሰው ሃይልና አስፈላጊ ቁሳቁሶች በመሟላታቸው ወደ ሥራ መገባቱን አስረድተዋል።

    በንሳ ዳዬ ካምፓስ ካለው ርቀትና የመሬት አቀማማጥ አኳያ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ራሱን ወደቻለ ዩኒቨርሲቲ ሊያድግ የሚችል በመሆኑ ግንባታዎቹ ይህንኑን ታሳቢ አድርጎ የተካሄዱ እንደሆነ ያስታወቁት ፕሬዝዳንቱ፥ ተማሪዎች፣ ሠራተኞችና የአከባቢው ማኀበረሰብ እንደግል ንብረታቸው መንከባከብና ለመጭው ትውልድ የማስተላፍ ግዴታ እንዲወጡ አሳስበዋል።

    አዲስ የተመደቡ ተማሪዎችም ከቤተሰብ ተለይተው የመጡበትን ዓላማ በማንገብ ጊዜያዊ ተግዳሮቶችን በመቋቋም፣ ከአልባሌ ሱሶች (እና ድርጊቶች) በመራቅና በርትቶ በማጥናት ከቤተሰብና ሀገር የተጣለባቸውን አደራ ለመወጣት ራሳቸውን ማዘጋጀት እንዳለባቸው አቶ አያኖ በራሶ አስገንዝበዋል።

    የካምፓሱ ማኔጅንግ ዳይሬክቴር አቶ ገነነ ካቢሶ በበኩላቸው ካምፓሱ በእርሻ ሜካናይዜሼንና በመምህራን ስልጠና የትምህርት መስኮች ተማሪዎችን ተቀብሎ የሚያሰለጥን ሲሆን፥ በተማሪዎቹ በሚካሄዱ አሳታፊና ችግር ፌች ምርምሮች የአከባቢውን ማሀበረሰብ ያሳተፈ እንዲሆን ህብረተሰቡ እንዲተባበር ተከታታይ ስልጠናዎች የሚሰጡ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

    በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንቶች፣ የበንሳ ዳዬ ከተማ፣ የአከባቢው ቀበሌ ገበሬ ማኀበራት አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ከአከባቢው ማኀበረሰብ የወጣቶችና ሴቶች ተወካዮች መገኘታቸው ታውቋል።

    ምንጭ፦ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    በንሳ ዳዬ ካምፓስ

    Semonegna
    Keymaster

    የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል እና የፌዴራል ፖሊስ የደረሱበት ስምምነት በሆስፒታሉ የሚሰጠውን የፎረንሲክ ምርመራ ተከትሎ በህክምናና በሕግ ጉዳዮች ላይ መረጃን በወቅቱ ለማግኘት የሚያስችል ፈጣን አሠራር ለመዘርጋት ያለመ ነው።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ)– የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ህክምና ኮሌጅ ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ ጋር የፎረንሲክ ምርመራን በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ኅዳር 19 ቀን 2011 ዓ.ም. ተፈራርመዋል።

    ስምምነቱ በሆስፒታሉ የሚሰጠውን የፎረንሲክ ምርመራ ተከትሎ በህክምናና በሕግ ጉዳዮች ላይ መረጃን በወቅቱ ለማግኘት የሚያስችል ፈጣን አሠራር ለመዘርጋት ያለመ ነው ተብሏል።

    የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ዋና ፕሮቮስት ዶ/ር ወንድማገኝ ገዛኸኝ ስምምነቱ በተፈረመበት ጊዜ እንደገለጹት፥ ከምረዛና ከአደጋዎች ጋር የተያያዙ የሞት መንስዔዎችና የጤና ጉዳቶች በመለየት ለሕግ አካላት መረጃን በወቅቱ በማቅረብ ረገድ በአገሪቱ ውስጥ ክፍተቶች አሉ። በዚህም ሆስፒታሉ በቅርቡ በጀመረው አጠቃላይ የፎረንሲክ ምርመራ ማዕከል ለሕግ አካላትም ሆነ ለመረጃ የሚጠቅሙ መንስዔዎችን የማጣራት ሥራዎችን በስፋት እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

    ይህንን የፎረንሲክ ምርመራ በማጠናከር የወንጀል ምርመራን በፍጥነት በመለየት ከፌዴራል ፖሊስ በመተባበር ለመሥራት የሚያስችለውን ቅንጅታዊ አሠራር ማጎልበት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ይህን ሰነድ ከተፈረመበት ጊዜ ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ብለዋል ዶ/ር ወንድማገኝ።

    በስምምነቱ መሠረትም የአስክሬን ምርመራን ጨምሮ፣ የአስገድዶ መደፈር ጥቃት፣ የእድሜ ምርመራና የመኪና አደጋ በስምምነቱ የተካተቱ እንደሆኑ ተጠቁሟል። በዋናነትም ለፖሊስና ለሕግ ባለሙያዎች የፎረንሲክ ህክምናና ፎረንሲክ ሳይንስ ከተግባር ትምህርት ጋር ስልጠና የመስጠት ሥራ በሆስፒታሉ የሚከናወን እንደሆነና ምርመራውን የሚያግዙ መሣሪያዎችን በጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ሁኔታም በስምምነቱ ተካቷል።

    በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ ኃላፊ ምክትል ኮሚሽነር ጀኔራል ተኮላ አይፎክሩ በበኩላቸው ወንጀልን መርምሮ ተጠያቂውን አካል ለፍርድ በማቅረብ ረገድ የፎረንሲክ ምርመራን ዘመናዊና ፈጣን በሆነ መልኩ ማከናወን አስፈላጊ ነው። ”ይህም ደግሞ በአገሪቱ የሕግ የበላይነት ለማረጋገጥና የዜጎችን ሰላም ለማስፈን ሚናው የጎላ ከመሆኑም ባሻገር ዜጎች በፍትህ አካላት ላይ ያላቸውን እምነት እንዲያጠናክሩ ይረዳል” ብለዋል።

    ወንጀሎች በተፈጸሙባቸው አካባቢዎች ከሁለቱም ተቋማት የተውጣጣ የሙያተኞች ቡድን በስፍራው በመገኘት የማጣራት ሥራዎችን በጋራ ለመሥራት የሚያስችል አሠራር መስምምነቱ መካተቱን ጀኔራል ተኮላ ጠቅሰዋል። ሌላው አዲስ አበባን ጨምሮ በክልሎች ውስጥም ብሔራዊ የፎረንሲክ ተቋማትን ለመመስረት የሚያስችል አሠራር የሚዘረጋ እንደሆነና የጋራ የሆነ የስልጠናና የምርምር ፕሮግራሞች የሚካሄድ ይሆናልም ሲሉ አክለዋል።

    በአሁኑ ወቅት የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የፎረንሲክ ማዕከል በቀን ከ25 እስከ 30 የሚሆኑ ምርመራዎችን እንደሚያከናውን ከሆስፒታሉ የተገኘው መረጃ ያመላክታል ሲል የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዘግቧል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የፎረንሲክ ምርመራ

    Semonegna
    Keymaster

    ጅማ ዩኒቨርሲቲ ባስገነባው የህክምና ማዕከል ምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ ለዓመታት ያስተማራቸውን 331 የህክምና ዕጩ ምሩቃን እና በተለያዩ መስኮች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 2ሺህ የድህረ ምረቃ መርሀ ግብር ተማሪዎችን ያስመርቃል።

    ጅማ (ሰሞነኛ)– ጅማ ዩኒቨርሲቲ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የፌድራልና የክልል መንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የህክምና ማዕከሉን ኅዳር 29 ቀን 2011 ዓም እንደሚያስመርቅ ተዘግቧል።

    የህክምና ማዕከሉ 800 (ስምንት መቶ) አልጋዎች ያሉት ሲሆን፥ በደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍል ከ20 ሚሊየን በላይ ሰዎች የህክምና አገልግፍሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው ተብሏል። ማዕከሉ እንደ ደቡብ ሱዳን ላሉ ጎረቤት ሀገራትም አገልግሎት ለመስጠት ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ መሆኑን ተነግሯል።

    ዩንቨርሲቲው ያስገነባው ይህ የህክምና ማዕከል በህክምና እና ጤናው ዘርፍ የምርምር፣ የማስተማሪያ፣ እንዲሁም የማኅበረሰብ አገልግሎቶችን ለመስጠት የሚያስችል መሆኑም ነው የተገለጸው። በዚህም ጅማ ዩኒቨርሲቲ በሀገሪቱ ከሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ሲነጻጸር ልቆ የሚታይበትን የማኅበረሰብ ተኮር (community-based) ትምህርትና ምርምር ይበልጥ ያገለብትለታል ተብሎ ይታመናል።

    Ethio-American Doctors Group (EADG): Building a regional healthcare system & medical tourism

    ዩንቨርሲቲው በህክምና ማዕከሉ የምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ ለዓመታት ያስተማራቸውን 331 የህክምና ዕጩ ምሩቃን እና በተለያዩ መስኮች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 2ሺህ የድህረ ምረቃ መርሀ ግብር ተማሪዎችን እንደሚያስመርቅም ታውቋል።

    በተመሳሳይ መልኩ ዩንቨርሲቲው ያስገነባው 40 ሺህ ያህል ተመልካቾችን ማስተናገድ የሚችለው ስታዲየም፣ ሲቭክ አዳራሽ፣ መንገዶችና ሌሎች የመሠረተ ልማት ሥራዎች ይመረቃሉ ተብሏል። የሲቪክ አደራሹ በርካታ ተሰብሳቢዎችን በአንዴ የሚያስተናግድና የተለያዩ ኮንፈረንሶችን በተመሳሳይ ጊዜ ለማካሄድ የሚያስችሉ የተለያዩ ክፍሎች እንዳሉትም ተነግሯል። ከዚህ ጋር ተያይዞ እንደተዘገበው ይህ የሲቭክ አዳራሽ ከተማዋን የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ ስለመሆኑም ነው የተገለጸው።

    ምንጭ፦ ኢቢሲ / ኤፍ.ቢ.ሲ. / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ጅማ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ማዕከል


    Semonegna
    Keymaster

    5ኛውን አዲስ ፎቶ ፌስት የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ ያዘጋጁት ደስታ ለአፍሪካ [የፈጠራ አማካሪ] ከስዊዘርላንድ ኤምባሲ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ሲሆን፥ አውደ ርዕዩ እስከ ታህሳስ 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ድረስ ይቆያል።

    አዲስ አበባ (ቢቢሲ አማርኛ) – በአፍሪካ ውስጥ ስመጥር ከሆኑት የፎቶ ፌስቲቫሎች ከፍተኛ ቦታ ያለው አዲስ ፎቶ ፌስት ኅዳር 27 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ሸራተን ሆቴል ተከፍቷል።

    ለአምስተኛ ጊዜ በተካሄደው በዚህ አውደ ርዕይ ላይ ከ61 ሃገራት የተወጣጡ 152 የፎቶ ግራፍ ባለሙያዎች የተለያዩ ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ። ይህ አውደ ርዕይ በየዓመቱ አሳታፊነቱ እየጨመረ የመጣ እንደሆነ የምትናገረው ‘ደስታለ አፍሪካ የፈጠራ አማካሪ’ (Desta for Africa Creative Consulting) የተባለ ድርጅት መሥራችና የአዲስ ፎቶ ፌስት ዋና አዘጋጅ የሆነችው የፎቶ ባለሙያዋ አይዳ ሙሉነህ ዋና ትኩረቱም የውክልና ጉዳይ ነው ትላለች።

    አፍሪካ በተለያዩ ምስሎችም ሆነ በውጭው ዓለማት የምትታወቀው ሁሌም ከችግር፣ ድርቅና ረሀብ ጋር ብቻ ከመሆኑ አንፃር አዲስ ፎቶ ፌስት በጎ ጎኗንም ለማሳየት እንዳለመ አይዳ ታስረዳለች።

    “ይህንን የፎቶ አውደ ርዕይ የምናየው እንደ አቅም ግንባታ ነው፤ እነዚህን ሁሉ ወጣት የፎቶ ባለሙያዎች ስናሰባስብ ወይም ስልጠና ስንሰጥ የኢትዮጵያን እውነታ በምን መንገድ ሊያሳዩ ይችላሉ የሚለውን ለማሳየት ነው” በማለት ታስረዳለች አይዳ።

    በተለይም አፍሪካ እንደ ጨለምተኛ ብቻ አህጉር ተደርጋ መታየቷ ትክክለኛ እይታ እንዳልሆነ የምትናገረው አይዳ “ሁሉም ነገር በጎ አይደለም፤ ነገር ግን ሁሉም ነገር ደግሞ መጥፎ አይደለም። በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ጎልቶና ገኖ የሚታየው መጥፎ ነገር ነው” በማለት ይህንንም ለመቀየር ኢትዮጵያዊ ወይም አፍሪካዊ ፎቶ ባለሙያዎችን ማፍራትና እይታዎችንም መፍጠር እንደሚያስፈልግ አፅንኦት ትሰጣለች።

    በዚህ ዓመት አዲስ ፎቶ ፌስት ዓውደ ርዕይ ላይ 1200 ፎቶዎች የሚቀርቡ ሲሆን ከዓመት ወደ ዓመት የተሳታፊዎች ቁጥር እየጨመረ እንደሆነ አይዳ ሙሉነህ ተናገራለች።

    በባለፈው አመት ለመሳተፍ የጠየቁ የፎቶ ባለሙያዎች ቁጥር 500 የነበረ ሲሆን በዚህ አመት ወደ 832 ደርሷል። ከነሱም ውስጥ 152 ባለሙያዎች ተመርጠው ተሳታፊ ሆነዋል። ለአይዳ ሙሉነህ የተሳታፊዎች ቁጥር መብዛት የሚያሳየው አዲስ ፎቶ ፌስት በዓለም ላይ ያለው ስፍራ እየጨመረ መሆኑን ነው።

    በተጀመረበት ወቅት አምስትዓ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ከኢትዮጵያ ያሳተፉ ሲሆን በአሁኑ ሰዓትም 35 እንደደረሱ አይዳ ትናገራለች። ምንም እንኳን በፈተናዎች የተሞላ መሆኑን አይዳ ባትክድም “ይሄን ሁሉ ሥራ የምንሰራው ሃገሪቷን ለማሳወቅ ነው” ትላለች።

    5ኛውን አዲስ ፎቶ ፌስት የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ ያዘጋጁት ደስታ ለአፍሪካ የፈጠራ አማካሪ ከስዊዘርላንድ ኤምባሲ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ሲሆን፥ አውደ ርዕዩ እስከ ታህሳስ 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ድረስ ይቆያል።

    ምንጭ፦ ቢቢሲ አማርኛ | ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አዲስ ፎቶ ፌስት

    Semonegna
    Keymaster

    አርባ ምንጭ (አ.ም.ዩ.)– አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለ5ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን 76 የህክምና ዶክተሮች ኅዳር 22 ቀን 2011 ዓ.ም. በደማቅ ሥነ ስርዓት አስመርቋል።

    የዩኒርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ በምርቃት ሥነ ስርዓቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ የትምህርት መርሀ ግብሮችን (ፕሮግራሞች)እና የሚካሄዱ ምርምሮች የማኅበረሰቡን ችግር የሚፈቱና ይበልጥ ተጠቃሚ የሚያደርጉ መሆን ይገባቸዋል ብለዋል። አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በአገር አቀፍ ደረጃ የተቀመጠውን የትምህርት ጥራት፣ አግባብነትና ተደራሽነት ግብ ለማሳካት በትኩረት እየሠራ መሆኑንም አክለው ተናግረዋል። ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ::

    ዩኒቨርሲቲው የጤና ዘርፍ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል በመምህራን ልማት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን የገለጹት ፕሬዝደንቱ፥ የዩኒቨርሲቲው የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 127 መምህራን እያስተማረ የሚገኝ ሲሆን 69ኙ 2ኛ ዲግሪ፣ 11ዱ 3ኛ ዲግሪ እና 41ዱ የስፔሻሊቲ መ/ራን ደረጃቸውን ሊያሻሽል ትምህርት በመከታተል ላይ ይገኛሉ ብለዋል።

    እንደ ፕሬዝደንቱ ማብራሪያ ዩኒቨርሲቲው ከአርባ ምንጭ ሆስፒታልና አጎራባች የጤና ተቋማት ጋር ትስስር በመፍጠር፣ በማኅበረሰቡ ጤና መሻሻል ላይ ትኩረት ያደረጉ ምርምሮችን በማከናወንና የማኅበረሰብ አገልግሎት ሥራዎችን በመሥራት ላይ ነው።

    Selale University (Fiche, Ethiopia) accepts students for the first time

    ፕሬዝደንቱ በህክምና ትምህርት የሴት ተማሪዎችን ተሳትፎ በተመለከተ በ2009 ዓ.ም. ከነበሩት 58 የህክምና ዶክትሬት ምሩቃን መካከል የሴት ምሩቃን ቁጥር 1 (አንድ) ብቻ የነበረ ሲሆን በ2011 ዓ.ም. ከተመረቁት 76 የህክምና ዶክተሮች የሴት ምሩቃን ቁጥር 18 መድረሱ የሴት ተማሪዎች ተሳትፎ ከዓመት ዓመት እየጨመረ መሆኑን ያሳያል ብለዋል። በተጨማሪም ምሩቃን በዩኒቨርሲቲው ያገኙትን ዕውቀትና ክህሎት ከሥራው ዓለም ጋር አዋህደው የማኅበረሰቡን ጤና ለማሻሻል የበኩላቸውን አስተዋፅኦ በማበርከት ለአገራችን ህዳሴ ታላቅ ሚና እንዲጫወቱም አሳስበዋል።

    የዩኒቨርሲቲው ኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተወካይ አቶ በድሩ ሂሪጎ በበኩላቸው እንደገለፁት ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ባሻገር የእናቶችንና ህፃናትን ሞት ለመቀነስ፣ የወባ በሽታን ለመከላከል እንዲሁም መሰል የጤና መሻሻል ሊያመጡ የሚችሉ አገር አቀፍ ምርምሮችን ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ሲሆን እየተገነባ ያለው የዩኒቨርሲቲው ዘመናዊ የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል ተጠናቆ ሥራ ሲጀምር ጥራት ያለው የጤና ትምህርትና የህክምና አገልግሎት ለማህበረሰቡ ለመስጠት ያስችላል።

    ዓለም የሚፈልገውን ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ኃይል ከማፍራት አንፃር በአገራችን ትምህርትና ሥልጠና አቅርቦት፣ ተገቢነትና ጥራት ላይ ትኩረት የሚሹ በርካታ ጉዳዮች አሉ ያሉት የኢፌዴሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር እና የዕለቱ የክብር እንግዳ ዶ/ር ሂሩት ወልደማርያም ያለነው በታዳጊና ኢኮኖሚዋ ባልዳበረ አገር እንደመሆኑ መጠን ምሩቃን ችግሮችን በሰከነ መንፈስ በመጋፈጥ በድል መወጣት፣ ቀና አስቢነትንና ትህትናን መላበስ እንዲሁም በአሸናፊነት እና በ”እችላለሁ!” ስሜት ተነሳሽነት የወገናችውን ህይወት የሚቀይር ሃሳብና አሠራር ሊቀይሱ ይገባል በማለት አሳስበን ንግግራቸውን በመቀጠል፦

    ‹‹ዛሬ ተንብዩ፤ ለነጋችሁ ያለእረፍት ሥሩ፤ የምትይዙት ጓደኛ፣ የምታዩት ፊልም ሁሉ ከህልማችሁ እና መድረሻችሁ ጋር የተገናኘና ግባችሁ ላይ ለመድረስ የሚያግዛችሁ መሆኑን አረጋግጡ›› ያሉት ሚኒስትሯ ዘረኝነት፣ ሌብነት እና ራስ ወዳድነት ከአገራችን ወግና ባህል የወጡ በመሆኑ ልትታገሏቸው ይገባል ብለዋል ።

    የኢትዮጵያ የህክምና ማኅበር ተወካይ እንዲሁም የእለቱ ተጋባዥ እንግዳ ዶ/ር መስከረም አለቃ በበኩላቸው የተመረቃችሁበት ሙያ ትልቁን የሰው ልጅ የማዳን ተግባር በመሆኑ በሥራው ዓለም የሚጠብቋችሁን ተግዳሮቶች በትጋት በመወጣት ለወገናችሁን ጤና መሻሻል ልትሠሩ ይገባል በማለት ለአገሪቱ ጤና መሻሻል በጋራ ለመሥራት ለምሩቃኑ በማኅበሩ ሥም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

    የሜዳሊያ ተሸላሚ መሆኑ እንዳስደሰተው የገለፀውና 3.54 አማካኝ ወጤት በማምጣት የከፍተኛ ማዕረግ ተሸላሚ የሆነው ምሩቅ መሠረት ሙሉ በቀጣይ የማህፀንና ፅንስ ሐኪም መሆን እንደሚፈልግና የእናቶችንና ህፃናትን ሞት ከመቀነስ አንፃር ከፍተኛ ኃላፊነት እንደሚጠብቀው ተናግሯል።

    አማካኝ ወጤት 3.46 የማዕረግ ውጤት በማምጣት ሴቶች በህክምና ትምህርት ዘርፍ የተሻለ ተሳትፎ መኖሩን ጥሩ ማሳያ የሆነችው ምሩቅ ትዕግስት ገረሱ የእናቶችንና ህፃናትን ሞት ሊቀንሱ የሚችሉ በቂ ምርምሮችን በማከናወን ባለት ዕውቀትና ክህሎት ማኅበረሰቡን ለማገልገል ዝግጁ እንደሆነች ገልፃለች።

    ምንጭ፦ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ

    የህክምና ዶክተሮችን አስመረቀ

    Semonegna
    Keymaster

    ኢትዮጵያዊያን አያሌ የሚያስተሳስሯቸው ነገሮች ያሏቸው በመሆኑ የሚያለያዩዋቸውን ጥቂት ነገሮች በመቻቻል አንድነታቸውን የሚያጎለብቱ ጉዳዮችን ጎልቶ እንዲወጣ የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሏል።

    አዲስ አበባ (ኢ.ፕ.ድ) – የዘንድሮ የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ከልዩነት በላይ ለሕዝቦች አንድነት መጠናከር ትኩረት እንደሚሰጥ የፊዴሬሽን ምክር ቤት ገለፀ።

    የፊታችን ህዳር 29 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀን በአዲስ አበባ ከተማ የሚከበረው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ዝግጅት መጠናቀቁንም ምክር ቤቱ አስታውቋል።

    ዘንድሮ ለ13ኛ ጊዜ የሚከበረውን በዓል ከልዩነት በላይ ለሕዝቦች አንድነት መጠናከር ትኩረት እንደሚሰጥ በምክር ቤቱ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ገብሩ ገብረሥላሴ በተለይ ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢ.ቢ.ሲ) ተናግረዋል። በዚህም ብሔረሰቦች የራሳቸውን ባህል ከማስተዋወቅ በዘለለ የባህል ልውውጥ የሚያደርጉበት መድረክ እንደሚፈጠር ገልፀዋል።

    በዚህም አንዱ ብሔር የሌላውን ባህል እንዲያንፀባርቅ በማድረግ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቱ እንዲጎለብት ይደረጋል ሲሉ ተናግረዋል ዳይሬክተሩ አቶ ገብሩ።

    ኢትዮጵያዊያን አያሌ የሚያስተሳስሯቸው ነገሮች ያሏቸው በመሆኑ የሚያለያዩዋቸውን ጥቂት ነገሮች በመቻቻል አንድነታቸውን የሚያጎለብቱ ጉዳዮችን ጎልቶ እንዲወጣ በዓሉ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል።

    አቶ ገብሩ አክለውም ዘንድሮ በአዲስ አበባ የሚከበረው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን የዝግጅት ሥራዎች ተጠናቀው የበዓሉ ተሳታፊዎች እየተጠበቁ መሆኑን ገልፀዋል። በበዓሉ ዕለትም በክልሎች ብሎም በሀገር አቀፍ ደረጃ ሲምፖዚየሞች፣ የተለያዩ ውይይቶችና ዝግጅቶች እንደሚካሄዱም ይጠበቃል ብለዋል።

    በበዓሉ በሚካሄዱ ውይይቶች ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በግጭቶች መንስዔ ዙሪያ ምክክር ተደርጎ የመፍትሄ ሀሳቦች እንዲቀመጡም እንደሚደረግ አቶ ገብሩ አመላክተዋል።

    የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዲሪ) ሕገ-መንግስት የፀደቀበት ቀን የሆነው ህዳር 29 ቀን‹‹በብዝሃነት የደቀመ ኢትዮጵያዊ አንድነት›› በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ ይከበራል።

    በበዓሉ ቅድመ ዝግጅት ወቅትም የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቶችን የሚያጠናክሩ የሰላም ጉባኤዎች በተለያዩ ክልሎች ሲካሄዱ መቆየታቸውንም ምክር ቤት አስታውቋል። ባለፈው ዓመት 12ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ዋና ከተማ በሆነችው ሰመራ መከበሩ ይታወሳል

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢ.ፕ.ድ) | ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል

    Semonegna
    Keymaster

    አዳማ ከተማ ውስጥ የሚገነባው የኮንፈረንስና ኮንቬንሽን ማዕከል ግንባታው ከ3 እስክ 5 ዓመት ጊዜ የሚፈጅ ሲሆን፥ የዘንድሮውን ዓመት ለዝግጅት በመያዝ በቀጣይ ወደ ግንባታ ለመግባት በትኩረት እንደሚሠራ የከተማዋ ከንቲባ አቶ መስፍን አሰፋ ገልጸዋል።

    አዳማ (ኢ.ፕ.ድ./ኤፍ.ቢ.ሲ.) – አዳማ ከተማን የኮንፈረንስና እና ኮንቬንሽን ማዕከል ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን የአዳማ ከተማ አስተዳደር ሠራ ገለጸ። የከተማ አስተዳደሩ የአዳማ ከተማ ሀገሪቱ ውስጥ ካላት መዕከላዊ አቀማመጥ እና ለዋና ከተማዋ አዲስ አበባ ያላትን ቅርበት መሠረት በማድረግ ከተማዋን የኮንፈረንስ እና ኮንቬንሽን ማዕከል ለማድረግ እየተንቀሳቀሰ መሆኑ ነው የተገለፀው።

    የማዕከሉ ዲዛይን ተሠርቶ የተጠናቀቀ ሲሆን፥ ዲዛይኑም የአካባቢውን ማኅበረሰብ ባህል እና እሴት በጠበቀ መልኩ የተሠራ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አቶ መስፍን አሰፋ ተናግረዋል።

    ከዚህ ባለፈም ማዕከሉ መንግስትን እና የአካባቢውን ባለሀብቶች በማሳተፍ የሚሠራ መሆኑ ነው የተገለፀው።

    ዲዛይኑ ተሠርቶ እንደተጠናቀቀም ከባለሀብቱ ጋር ወይይት ተደርጓል ያሉት ከንቲባው፥ የማዕከሉ ግንባታ ለከተማዋም ሆነ ለሀገሪቱ ፈርጀ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው አቶ መስፍን አንስተዋል።

    ግንባታው ከ3 እስክ 5 ዓመት ጊዜ የሚፈጅ ሲሆን፥ የዘንድሮውን ዓመት ለዝግጅት በመያዝ በቀጣይ ወደ ግንባታ ለመግባት በትኩረት እንሠራለን ነው ያሉት ከንቲባው። ግንባታውን አጠናቆ ለመጨረስም 2 ቢሊየን ብር ስፈልጋል ያሉት ከንቲባው፥ ለግንባታው የሚያስፈልገው የ10 ሄክታር መሬት የማዘጋጀት ሂደቱም ተጀምሯል ብለዋል።

    Addis-Africa International Convention and Exhibition Center (AAICEC) Share Company

    በሌላ በኩል በከተማዋ ከኢንቨስትመንት ጥያቄ ጋር ተያይዞ የሚነሳውን ቅሬታ መቅረፍም፥ በዚህ ዓመት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራበት ያለ ጉዳይ መሆኑን ነው ከንቲባው የተናገሩት።

    ፋና (ኤፍ.ቢ.ሲ.) እንደዘገበው ብዙ ጊዜ የከተማዋ አቅም እና የኢንቨስትመንት አማራጭ ላይ በቂ ዝግጅት ስለማይደረግ ባለሀብቱ የኢንቨስትመንት ፍቃድ ጠይቆ ምላሽ ሳያገኝ ለበርካታ ዓመታት ወደሥራ ሳይገባ መቆየቱ እና ይህም የተለያየ ቅሬታ መፍጠሩንም ከንቲባው አንስተዋል ።

    የተጠራቀሙ ጥያቄዎችን ለመመለስ እና የዘርፉን ውስንነቶች ለመቅረፍም የከተማዋን አቅም እና የኢንቨስትመንት አማራጮች የመለየት ሥራ እየሠራ ነው ብለዋል።

    አሁን ላይ ለመሥራት ከታሰበው የኮንፈረንስና የኮንቬንሽን ማዕከል አጋዥ የሆኑ ባለ አምስት ኮኮብ ሆቴሎች ለመስራት ፍቃድ የሚጠይቁ ባለሀብቶች በቅድሚያ የሚስተናገዱ መሆኑን ከንቲባው ጠቁመዋል።

    በመስከረም ወር 2007 ዓ.ም. በይፋ የተመረቀው የአዲስ-አዳማ የፈጣን መንገድ አገልግሎት መስጠት ከጀመረበት ጊዜ ጀመሮ ከከተማዋ ወደ አዲስ አበባ የሚደረገውን ጉዞ በእጅጉን እንዳቃለለውና በሁለቱ ከተሞች የነበረውን የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ሁነኛ በሚባል መልኩ እንዳሻሻለው ይታወቃል። ይህ 85 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለውና ወደጎን ስድስት መኪናዎችን ማስተናገድ የሚችለው መንገድ ከተገነባ በእላ አዳማ ከተማ ውስጥ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ መጨመሩን ብዙዎች ይመሰክራሉ።

    ምንጮች፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት፣ ፋና ብሮድካስቲንግ፣ ሰሞነኛ

    አዳማ ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢ

    Semonegna
    Keymaster

    በተበባሩት መንግስታት ድርጅት ስር የሚከበረው ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን ዘንድሮ የሚከበረው ለ26ኛ ጊዜ ሲሆን የዘንድሮ ክብረ በዓል መሪ ቃልም “የአካል ጉዳተኞችን ማበረታት፣ የአካል ጉዳተኞችን ታቃፊነትና እኩልነት ማረጋገጥ” የሚል ነው።

    ሀዋሳ (ሰሞነኛ ) – ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ26ኛ ጊዜ በሀዋሳ ከተማ ተከበረ።

    የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ በበዓሉ ላይ ተገኝተው አንደገለጹት፥ አካታችነትና እኩልነትን በማስፈን የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሁሉም የህበረተሰብ ክፍል የጋራ ጉዳይ መሆን አለበት ብለዋል።

    አሁን ላይ የአካል ጉዳተኞች ችግሮች ተቀርፈዋል ማለት ባይቻልም፥ ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠት በእየደረጃው አካታች እቅዶችን በማቀድ ለተግባራዊነታቸው እንቅሰቃሴ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

    ለአካል ጉዳተኞች የተለያዩ ድጋፎች ማድረጉ የተጀመረ ሲሆን፥ ሀገር ውስጥ ዊልቼር ለማምረት መታቀዱም ነው የተገለጸው።

    እንደ ፋና (ኤፍ.ቢ.ሲ.) ዘገባ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሚሊየን ማቲያስ በበኩላቸው፥ አካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ በርካታ ስራወች እየተከናዎኑ መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህ በፊት በክልሉ አርባ ምንጭ የአረጋውያን ማዕከል ብቻ የነበረ ሲሆን፥ አሁን ላይ በቤንች ማጅ ዞን ተጨማሪ የአረጋውያን ማዕከል ለመክፈት አየተሠራ መሆኑን ጠቁዋል።

    በበዓሉ ለመታደም የተገኙት የአካል ጉዳተኞች በበኩላቸው፥ የትምህርት አገልግሎት ለማግኘት አስካሁን ድረስ ችግሮች ያሉባቸው መሆኑን ነው የተናገሩት። አገልግሎቱ የሚያገኙበት እድል ቢፈጠርም እንኳ ረጅም ርቀት መጓዝ ግድ እንደሚላቸውም አስረድተዋል። ከዚህም ሌላ የአካል ጉዳተኞችን የተመለከቱ መመሪያዎችና ደንቦች ላይ የአፈጻጸም ክፍተት የሚታይ መሆኑን አመላክተዋል። ለአብነትም አንዳንድ የሚወጡ የሥራ ማስታወቂያዎች ሙሉ ጤንነትን የሚጠይቁና የአካል ጉዳተኞችን የማይጋብዙ መሆኑን አንስተዋል።

    አብዘኞቹ የአገለግሎት መስጫ ተቋማትም የአካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረጉ አለመሆናቸውንም ገልጸዋል።

    በተበባሩት መንግስታት ድርጅት ስር የሚከበረው ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን ዘንድሮ የሚከበረው ለ26ኛ ጊዜ (እ.ኤ.አ. ከ1992 ጀምሮ) ሲሆን የዘንድሮ ክብረ በዓል መሪ ቃልም “የአካል ጉዳተኞችን ማበረታት፣ የአካል ጉዳተኞችን ታቃፊነትና እኩልነት ማረጋገጥ” (“Empowering persons with disabilities and ensuring inclusiveness and equality”) የሚል ነው።

    ኢትዮጵያ ውስጥ ለአካል ጉዳት እና ለአካል ጉዳተኞች የሚሰጠው አመለካከት የተሳሳተ በመሆኑ ሀገሪቱ ውስጥ የአካል ጉዳተኞችን ቁጥር በትክክል ማወቅ እጅግ አዳጋች እንደሆነና፣ የሚገመተውም ቁጥር ከትክክለኛው ቁጥር ዝቅተኛ እንደሆነ (under-reported) የተለያዩ ጥናቶች ያመለታሉ።

    አብዛኛው የኢትዮጵያ ህብረተሰብ አካል ጉዳተኝነትን ከፈጣሪ እንደመጣ ቁጣ ወይም መርገም እንደሚመለከተውና አካል ጉዳተኛ የሆነ ሰው ያላቸው ቤተሰቦችም ይሁኑ ህብተረሰቡ ሰለአካል ጉዳተኛው፣ ስለሚያስፈልገው ነገር ብሎም እንደማንኛውም ሰው ሙሉ ፍላጎትና መብት እንዳለው በግልጽ ከመወያየት ይልቅ መደበቅና ማሸሽን ይመርጣሉ። በዚህም ምክንያት አካል ጉዳተኞች አጅግ አዳጋች የሆነ ሕይወት እንዲገፉ ይገደዳሉ።

    በሀገሪቱ የአካል ጉዳተኞችን ጉዳይ በበላይ የሚመለከተውና የሚቆጣጠረው የሠራተኛነ ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሲሆን፥ በዚህ ሚኒስቴር ስር የሚገኝው የማኅበራዊ ደህንነት ልማት ማስፋፊያ ዳይሬክቶሬት የአካል ጉዳነኞችን ከሥራ እና ከማኅበራዊ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በፌደራል ደረጃ ይመለከታል፣ ያስተባብራል።

    በተጨማሪም የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ብሔራዊ ማኅበራት ፌዴሬሽን (FENAPD) ጥላ ስር ተደራጅተው ከ አካል ጉዳተኞች ጋር በተያያዘ የሚንቀሳቀሱ ስድስት ብሔራዊ ድርጅቶች ይገኛሉ። እነሱም፦

    1. የኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ብሔራዊ ማኅበር፣
    2. የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ብሔራዊ ማኅበር፣
    3. የኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ብሔራዊ ማኅበር፣
    4. የኢትዮጵያ ማየትና መስማት የተሳናቸው ብሔራዊ ማኅበር፣
    5. የኢትዮጵያ ሥጋ ደዌ ተጠቂዎች ብሔራዊ ማኅበር፣ እና
    6. የኢትዮጵያ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው ብሔራዊ ማኅበር ናቸው።

    ከእነዚህ ብሔራዊ ማኅበራት በተጨማሪ የአካል ጉዳተኞችን ታቃፊነትና እኩልነት በማረጋገጥ እንቅስቃሴዎች ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ጉልህ አስተዋጽዖ እያደረጉ የሚገኙ ማኅበራት ያሉ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ፦

    1. የኢትዮጵያ ብሔራዊ የአካል ጉዳተኞች ማኅበራት ኔትዎርክ (ENDAN)፣
    2. የኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኛ ሴቶች ብሔራዊ ማኅበር፣
    3. የትግራይ አካል ጉዳተኛ የቀድሞ ወታደሮች ማኅበር (ማኅበር ጉዱአት ኲናት ትግራይ) እና
    4. በኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞችና ልማት ማዕከል (ECDD) ተጠቃሽ ናቸው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን

    Semonegna
    Keymaster

    ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለም ከዚህ በኋላ በልማት ሰበብ የሚፈናቀልና የአርሻ መሬቱ የሚነጠቅ አርሶ አደር እንደማይኖር አረጋግጠውላቸዋል። በእስካሁኑ ሂደት የተጎዱ አርሶ አደሮችን በዘላቂነት ለማቋቋም እና ሕይወታቸውን ለመቀየር አስተዳደሩ ከምንም በላይ ትኩረት ሰጥቶ ይሠራልም ብለዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ የሚገኙ አርሶ አደሮችን አወያዩ። ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የካቢኔ አባላት እንዲሁም የክፍለ ከተማ አመራሮች አርሶ አደሮችን ያወያዩ ሲሆን በውይይታቸው መጀመርያም ኢንጂነር ታከለ ኡማ “የአርሶ አደሮችን ሕይወት መቀየር ታሪካዊ ኃላፊነት የጣለብን ግዴታ ነው፣ ይህንን ታሪክ የጣለብንን ኃላፊነት እንወጣዋለን” ብለዋል።

    አርሶ አደሮችም አላግባብ ከቀያቸው ስለመፈናቀላቸው፣ ከካሳ ክፍያና በማቋቋሚያ ድጎማ፣ በመሠረተ ልማት አቅርቦት፣ በካርታ አሰጣጥና የአርሶ አደር ልጆች ካሳ ክፍያ ዙሪያ እንዲሁም በክፍለ ከተሞች ስላለው የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ለምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ጥያቄ አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።

    ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለም ከዚህ በኋላ በልማት ሰበብ የሚፈናቀልና የአርሻ መሬቱ የሚነጠቅ አርሶ አደር እንደማይኖር አረጋግጠውላቸዋል። በእስካሁኑ ሂደት የተጎዱ አርሶ አደሮችን በዘላቂነት ለማቋቋም እና ሕይወታቸውን ለመቀየር አስተዳደሩ ከምንም በላይ ትኩረት ሰጥቶ ይሠራልም ብለዋል።

    ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት
    ——
    ሌሎች ዜናዎች:

    ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ኢዜአ)– በኢትዮጵያ ንብን በዘመናዊ መንገድ በማነብ የአገሪቱን የማር ምርት ለማሳደግ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በቅንጅት እንደሚሠራ የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ። በአገሪቱ ማርን በብዛትና በጥራት ለማምረት የንብ እርባታ ኢንዱስትሪ መቋቋም ይኖርበታል ተብሏል።

    በኢትዮጵያ ከመቶ ዓመት በላይ የንብ ማነብ ልምድ ቢኖርም አሠራሩ ዘመናዊ የንብ አነባብ ግብአቶችን መሠረት ያላደረገ፣ ይልቁንም ባህላዊ መንገድ የተከተለ በመሆኑ የሚፈለገውን ያህል የማር ምርት ማምረትና ለገበያ ማቅረብ አልቻለችም።

    በአገሪቱ ከ2 ሚሊየን በላይ ንብ አናቢዎች ያሉ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም በዓመት እስከ 50 ሺህ ሜትሪክ ቶን ማር በመመረት ላይ ይገኛል። ያም ሆኖ ግን የአመራረት ስርዓቱ እንዲዘምን ቢደረግ በአገሪቱ ከዚህ የበለጠ መጠን ማር ማምረት እንደሚቻል ነው ህዳር 21 ቀን 2011 ዓ.ም. አዲስ አበባ በተጀመረውና በዓለም አቀፉ አናቢዎች ፌዴሬሽን (Apimondia) በተዘጋጀው ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይ የተመለከተው።

    Ahadu Beekeeping and Honey Processing Factory inaugurated in Tigray Region, Ethiopia

    “በምግብ ምርት ላይ የንቦች አስተዋጽኦ” በሚል ርዕስ እየተካሄደ ባለው ጉባኤ ላይ የተገኙት የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ዑመር ሁሴን የንብ እርባታ ለዜጎች ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ከመሆን ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ዓይነተኛ ሚና እንዳለውም ገልፀዋል። ሆኖም በኢትዮጵያ በርካታ የንብ ዝርያዎችና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አናቢዎች ቢኖሩም በተለያዩ ችግሮች ሳቢያ አገሪቱ ከዘርፉ ማግኘት የሚገባትን እያገኘች እንዳልሆነ ነው የተናገሩት። በመሆኑም መንግስት ገበያ-ተኮር የማር ምርት ለማምረት በዘርፉ ከተሰማሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።

    ኢትዮጵያን ጨምሮ በዓለም የንቦች ቁጥር እየተመናመነ መምጣቱን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ችግሩን ለመከላከል ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብረ መሥራት የግድ መሆኑን አስረድተዋል።

    የአየር ንብረት መዛባት፣ በሽታና የተክሎች መጠን መመናመን ለንቦች ቁጥር እንዲቀንስ ካደረጉት ምክንያቶች መካከል የችግሩ መንስዔ በመሆኑ የጋራ መፍትሄ መፈለግ ይኖርብናል ብለዋል።

    ለንቦች ቁጥር መመናመን አንዱ ምክንያት የሆነው በአርሶ አደሩ ዘንድ በብዛት ጥቅም ላይ እየዋለ ላለው የጸረ-አረም ርጭት ዘላቂ መፍትሄ ሊሰጠው እንደሚገባ ገልጸዋል። በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ እድገት እያሳየ ያለውን የግብርና ዘርፍ ዘመናዊ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት አነስተኛ እንደሆነም ሚኒስትሩ አክለዋል።

    Ethiopia’s apiculture and huge honey production potential need to look for modern techniques

    በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ዓለም አቀፍ ጉባኤም መንግስትን፣ በዘርፉ የተሰማሩ አናቢዎችን፣ ማኅበራትና ተቋማትን የሚያበረታታ ነው ብለዋል።

    የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ካሊድ ቦምባ በኢትዮጵያ የማር ምርትን ለማሳደግ አሠራሩን ዘመናዊ ማድረግ ይገባል ብለዋል። በአገሪቱ ማርን በብዛትና በጥራት ለማምረት የንብ እርባታ ኢንዱስትሪ መቋቋም አንዳለበትም አሳስበዋል። ዘርፉን ማሳደግ አንዲቻል አዳዲስ ቴክኖሎጂ ማላመድ፣ ዛፎችን በብዛት መትከል፣ የገበያ ትሰስር መፍጠር፣ አመራረቱን ዘመናዊ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

    ዓለም አቀፉ አናቢዎች ፌዴሬሽን (Apimondia) ምክትል ፕሬዚዳንት ፒተር ኮዝሙስ ኢትዮጵያ ካላት የማምረት አቅም አኳያ አሁን ያለው ምርት ከ10 በመቶ እንደማይበልጥ ገልጸዋል። የአየር ንብረት ለወጥ፣ የንቦች በሽታ እና የዓለም ገበያ መለዋወጥ የዘርፉ ችግር በመሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ውይይት ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል። “ንቦች ከሌሉ ህይወት የለም” የሚሉት ምክትል ፕሬዘዳንቱ ተመራማሪዎች፣ እውቀት ያላቸው ሰዎች ልምዳቸውን ማካፈል አለባቸው ብለዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    የማር ምርት

    Semonegna
    Keymaster

    በሐረር የሚኖሩ የጉራጌ ህብረተሰብ አባላት በመስቃን እና ማረቆ በተፈጠረው ግጭት ለተጎዱ ወገኖች የሚውል ስልሳ ኩንታል ሩዝ እና አስር ኩንታል የፉርኖ ዱቄት ድጋፍ ማድረጋቸዉና ይህም በገንዘብ ሲተመን ከ1 መቶ 41 ሺህ ብር በላይ ነው።

    ሀረር (ሰሞነኛ) – በሐረር የሚኖሩ የጉራጌ ብሔረሰብ ተወላጆች በመስቃን እና በማረቆ ብሔረሰብ አባላት መካከል በተፈጠረዉ ግጭት ለተጎዱ እና ለተፈናቀሉ ወገኖች ከአንድ መቶ ሺህ (100,000) ብር በላይ ድጋፍ ማበርከታቸው ተገለጸ።

    በግጭቱ በርካታ ቁጥር ያላቸዉ የህብረተሰብ ክፍሎች ከቤት ንብረታቸዉ ተፈናቅለዉ በአንድ ማዕከል እየተረዱ እንደሆነም ተዘግቧል።

    በሐረር ከተማ የጉራጌ ማህበረሰብ የድጋፍ አሰባሰብ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዱላ ሟኖጂ በርክክቡ ወቅት በሰጡት አስተያየት ለዘመናት ተዛምደውና ተከባብረው በሚኖሩ በመስቃንና ማረቆ ህብረተሰብ መካከል በተፈጠረዉ ግጭት ለጠፋው የሰዉ ሕይወትና ለወደመው ንብረት እጅግ ማዘናቸዉም ገልፀው፥ ተፈናቅለዉ የሚገኙ ወገኖችም መላዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ በሚችለው መንገድ (በገንዘብ፣ በቁሳቁስ፣ ወዘተ) ተገቢዉን ድጋፍ ሊያደርግላቸዉ ይገባል ብለዋል።

    አሁን የተፈጠረው የለዉጥ ሂደት ባልጣማቸውና የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተከባበረው እንዲኖሩ የማይፈልጉ ጥቂት ግለሰቦች ቡድኖች በጠነሰሱት ተንኮል ምንም የማያዉቁ ጨቅላ ሕፃናት፣ እናቶች፣ እንዲሁም አቅመ ደካሞች መሰቃየታቸውና ቀዬአቸውን ጥለው መፈናቀላቸው በጣም ልብ የሚነካ ነዉ ብለዋል።

    መንግስት እንደሀገር የጀመረውን አብሮ የመኖር (‘የመደመር’) አሰተማሪ እርምጃ አጠናክሮ በማስቀጠል ሕይወት እንዲጠፋ፣ ንብረት እንዲወድምና ዜጎች ከቀዬአቸው አንዲፈናቀሉ ያደረጉ አካላትና ድርጊቱን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የፈጸሙ ግለሰቦች ወይም ቡድኖች በአስቸኳይ ለፍርድ መቅረብ አለባቸው ብለዋል።

    ሀገራችን ኢትዮጵያ ከወራት በፊት የጀመረችውን የጀመረችውን የለወጥ ጎዞን ለማደናቀፍ ሕዝቡ የሚያነሣቸ የወሠንና የመልካም አሰተዳደር ጥያቄዎችን በተሳሳተ ወይም አጥፊ በሆነ መንገድ በማሳየት ሕዝቡን ወደ እልቂትና የማያባራ ግጭት እንደገባ የሚየደርጉ አካላትን ከየተኛውም ወገን ሕዝቡ ከመንግሥት ጋር በመተባበር አጋልጦ መስጠት አንዳለበት አሳስበዋል።

    በተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ የቤተ ጉራጌዎች እምቅ አቅም ከዞኑ አልፈው ከጂግጂጋ፣ በቡራዪና በተለያዩ አካባቢ ጉዳት ለደረሰባቸው ኢትዮጵያውያን ድጋፍ ማድረጋቸው አሰታዉሰዉ አሁንም በዞኑ በተለያዩ ምክንያት ለችግር የተጋለጡ እንዲሁም ከመኖርያ መንደራቸው ወገኖችን ለማቋቋም የሚደረገው ደጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አቶ ዱላ ሟኖጂ አሳስበዋል።

    በሐረር የሚኖሩ ቤተ ጉራጌዎች በመስቃንና ማረቆ በተፈጠረው ግጭት ለተጎዱ ወገኖች የሚውል ስልሳ ኩንታል ሩዝ እና አስር ኩንታል የፉርኖ ዱቄት ድጋፍ ማድረጋቸዉና ይህም በገንዘብ ሲተመን ከ1 መቶ 41 ሺህ ብር በላይ እንደሆነም አስረድተዋል።

    በመጨረሻም ለወገን ደራሽ ወገን ነዉና በቀጣይ እነዚህ ወገኖች በቋሚነት እስኪቋቋሙ ድረስ ደጋፋቸዉን አጠናከረዉ እንደሚቀጥሉ የኮሚቴዉ ሰብሳቢ አቶ ዱላ ተናግረዋል።

    ምንጭ፦ የጉራጌ ዞን ግንኙነት ጽህፈት ቤት | ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የጉራጌ ህብረተሰብ

    Semonegna
    Keymaster

    ወራቤ (ሰሞነኛ)–በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ክልላዊ መንግስት፣ በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ የሚገኘው የወራቤ ዩኒቨርሲቲ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ክብርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም እና ሌሎች የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት በተገኙበት ኅዳር 17 ቀን 2011 ዓ.ም. ተመርቋል።

    የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ምረቃ ሥነ-ስርዓት ላይ ክብርት ሚኒስትሯ ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ካስተላለፉት መልዕክት ስለ ክልላዊነትና ዓለም አቀፋዊነት (localization and internationalization) የተናገሩት የሚገኝበት ሲሆን በንጽጽር መልክ ባስቀመጡት በዚህ ንግግራቸው ዓለማቀፋዊነት አጉልተው በማሳየት የሚከተለውን ብለዋል።

    ብዝሃነትና ዓለም አቀፋዊነት የዩኒቨርሲቲ መሰረታዊና ልዩ መለያ ባህሪዎች ናቸዉ። በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚገኙት የተለያዩ ማኅበረሰቦች የብዝሃነት ባህሪን የሚገልጹ ሲሆን፤ ይህም በተማሪዎች፣ በመምህራን፣ በአመራሩ እና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች አከባቢያዊ እና ህብረብሄራዊ አመጣጥ ይገለጻል።

    ስለሆነም ዩኒቨርሲቲዎች የፌደራል ተቋማት እንደመሆናቸዉ መጠን ተማሪዎች በየአካባቢያቸው ባለው ዩኒቨርሲቲ ብቻ እንዲማሩ፣ መምህራንም በአካባቢያቸው ባለው ዩኒቨርሲቲ ብቻ ተቀጥረው እንዲያስተምሩ፣ አመራሩም በተወለዱበት አከባቢ የሚገኘውን ዩኒቨርሲቲ ብቻ እንድያስተዳድሩ የሚለው አስተሳሰብ ከዩኒቨርሲቲ ብዝሃነትና ዓለም አቀፋዊነት የማስተናገድ ባህሪ የወጣ ስለሚሆን የዩኒቨርሲቲዎቻችንን ደረጃ ዝቅ የሚያደርግ ነዉ።

    ዓለም አቀፍ ቶሞክሮዎች እንደሚያሳዩት፣ ዩኒቨርሲቲዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚወዳደሩበት አንዱና ዋነኛው መስፈርት፣ ከተለያዩ የዓለማችን ክፍል ለሚመጡ ተማሪዎችና ሠራተኞች አቃፊ በመሆናቸውና ዓለም አቀፋዊነትን በማስተናገዳቸው ነው። ዩኒቨርሲቲዎች አለማቀፋዊነት ባህሪ እንጂ አካባቢያዊ ዉስንነት እንደማይመጥናቸዉ ያሳያል።

    ስለዚህ ከዓለም አቀፍ ተሞክሮ እና አሠራር በተቃራኒ አቅጣጫ መሄድ የለብንም! የከፍተኛ ትምህርት ተቋሞቻችን ከብሄራዊ አስተሳሰቦች አልፎ ዓለም አቀፋዊነት ላይ ማተኮር ይገባቸዋል። በመሆኑም ዩኒቨርሲቲዎቻችንን በአካባቢያዊነትና በባህል በመከፋፈል፣ ባህላዊና ክልላዊ ማድረግ ወይም መከፋፈል አያስፈልግም።

    በሌላ የከፍተኛ ትምህርት እንቅስቃሴ ዜና፥ የጎንደር የኒቨርሲቲ ለሴት መምህራንና ሠራተኞች በወሊድ ወቅት በመደበኛነት የሚፈቀድላቸውን የወሊድ ፈቃድ አጠናቀው ወደ ሥራ በሚመለሱበት ጊዜ ህፃናትን በሥራ ቦታ የማቆያና የመንከባከቢያ ማዕከል ኅዳር 19 ቀን 2011 ዓ.ም. ተመርቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆኗል።

    በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ክብርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ባስተላለፉት መልዕክት “የህፃናት ማቆያ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ መጀመሩ ትልቅ ሥራ በመሆኑ በዩኒቨርሲቲ ያሉ ሴቶችን ተሳትፎና ስኬታማነት ከማረጋገጥ አኳያ በጣም ትልቅ ሚና መኖሩን ገልፀው፥ ሴት መምህራን በሥራ ገበታቸው ላይ ቤት ትተው የመጡትን ህፃን በማሰብ በተከፈለ ልብ እንዳይሰማሩና ከወንድ አቻቸው ጋር ወደ ኋላ እንዳይቀሩ ይህ የህፃት ማቆያ ችግራቸውን እንደሚቀርፍላቸው ተናግረዋል።

    የዚህ ዓይነቱ የህፃናት ማቆያ ማዕከል በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቢስፋፋ ሴቶች መምህራን በጥናትና ምርምር ሥራቸው ላይ አትኩረው እንዲሠሩ እገዛ እንደሚያደርግላቸውም ሚኒስትሯ ዶ/ር ሂሩት ወልደማርያም ጨምረው ገልፀዋል።

    ከዚህ በፊት የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2011 በጀት ዓመት በሁሉም ካምፓሶች የህፃናት ማዋያ ለማቋቋም በዝግጅት ላይ መሆኑን መዘገባችን ይታወሳል

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የወራቤ ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ – አዋሽ ባንክ 23ኛውን የባለአክሲዮኖች ዓመታዊ መደበኛና 15ኛውን የባለአክሲዮኖች ድንገተኛ ጉባዔ ኅዳር 15 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ሂልተን ተካሂዷል።

    በጉባዔው ላይ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት እና ባለአክሲዮኖች የተገኙ ሲሆን፥ በስብሰባው ላይ የባንኩ የዳሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ታቦር ዋሚ የባንኩን ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በዝርዝር አቅርበዋል።

    የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢው በሪፖርታቸው እንደጠቀሱት ያሳለፍነው በጀት ዓመት ለአገራችንም ሆነ ለግል ባንኮች እጅግ ፈታኝ ጊዜ የነበረ ቢሆንም ባንኩ እነዚህን ፈታኝ ተግዳሮቶችን በመቋቋምና ወደ መልካም አጋጣሚ በመለወጥ በሁሉም የሥራ ዘርፎች አመርቂ ውጤት ማስመዘገቡን ገልጸዋል። የተመዘገበው ውጤት እ.ኤ.አ ለ2017/18 ሒሳብ ዓመት በአስር ዓመት ስትራቴጂ ውስጥ ከተቀመጠው  ግብ አኳያም ሲታይ እጅግ የላቀ ውጤት መሆኑን የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አብራርተዋል።

    አዋሽ ባንክ እ.ኤ.አ በ2017/18 የሒሳብ ዓመት ባንኩን ካጋጠሙት ተግዳሮቶች መካከል ዋና ዋናዎቹ የዋጋ ግሽበት፣ የውጭ ምንዛሪ እጥረት፣ የብድር ጣሪያ መኖር እና ከሚገኘው የውጭ ምንዛሪ 30 በመቶውን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገቢ እንዲያደርጉ መደረጉ በጉልህ ይጠቀሳሉ።

    አዋሽ ባንክ ይህንን ሁሉ ፈተናዎች ተቋቁሞ በሁሉም የሥራ ዘርፎች አመርቂ ውጤቶችን በማስመዘገብ ከሀገርቷ የግል ባንኮች መካከል የቀዳሚነት ሥፍራውን እንደያዘ መቀጠሉን ገልፀዋል።

    Wegagen Bank grosses more than 1 billion birr, which is 49% up from previous fiscal year

    እ.ኤ.አ በ2017/18 የሒሳብ ዓመት የባንኩ ያልተጣራ ትርፍ ብር 1.96 ቢሊዮን ሲሆን ይህም ትርፍ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የብር 650 ሚሊዮን ወይም የ49 በመቶ ዕድገት አሷይቷል። ይህም ትርፍ ለአዋሽ ባንክም ሆነ በግል ባንኮች ታሪክ ውስጥ ከፍተኛው ትርፍ እንደሆነ ታውቋል።

    ለባንክ ሥራ እንደ ደም ስር የሚታየውን የተቀማጭ ሒሳብን በማሰባሰብ ረገድም ጠቅላላ የባንኩ ተቀማጭ ሒሳብ ኤልሲ ማርጅንን ጨምሮ የብር 13 ቢሊዮን ወይም የ40 በመቶ ዕድገት በማሳየት እ.ኤ.አ ሰኔ 2018 መጨረሻ ላይ ብር 45.9 ቢሊዮን ደርሷል።

    አዋሽ ባንክ ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሰጠው የብድር መጠን ብር 31.3 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን ይህም ብድር ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት አንጻር ሲተያይ የብር 8.7 ቢሊዮን ወይም የ38 በመቶ ጭማሪ አስመዝግቧል።

    እ.ኤ.አ በ2017/18 የሒሳብ ዓመት የባንኩ ጠቅላላ ገቢ አምና ከነበረበት ብር 3.76 ቢሊዮን የብር 1.7 ቢሊዮን ወይም የ44 በመቶ ዕድገት በማስመዝገብ ብር 5.4 ቢሊዮን ሆኗል።

    Berhan Bank, one of the private banks in Ethiopia, registers more than 410 million birr before tax

    በሌላ መልኩ የባንኩ ጠቅላላ ወጪም የብር 1 ቢሊዮን ወይም የ41 በመቶ ዕድገት በማስመዝገብ ብር 3.4 ቢሊዮን ሁኗል። ለወጪዎቹ ማደግ ዓብይት ምክንያቶች የወለድ ምጣኔ መጨመር፣ የሠራተኞች ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ዕድገት፣ የዕቃዎች ዋጋ መናር እና የባንኩ የሥራ ዘርፎች መስፋፋት እንደሆነ ታውቋል።

    ባንኩ ለደንበኞቹ የተቀላጠፈና ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት ከመስጠት አኳያም የተለያዩ ሥራዎችን ያከናወነ ሲሆን አገልግሎቶቹንም በዘመናዊ የክፍያ ማሽኖች ማለትም በኤቲኤም እና ፖስ ማሽኖች እንዲሁም በሞባይል ባንኪንግ እና በኢንቴርኔት ባንኪንግ አገልግሎቶች በመታገዝ ለደንበኞቹ በቀን የ24 ሰዓት እና በሳምንት የ7 ቀናት የባንክ አገልግሎቶችን በመስጠት ላይ ነው። ለወደፊቱም ዘመናዊ የሆነ የግንኙነት ማዕከል (Contact Center) እና የደንበኞች ግንኙነት አመራር (Customer Relationship Management – CRM) አገልግሎቶችን በሥራ ላይ ለማዋል በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። ደንበኞች ሳይጉላሉ በአቅራቢያቸው የባንክ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻልም እ.ኤ.አ በ2017/18 ሒሳብ ዓመት ሃምሳ አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት የቅርንጫፎቹን ብዛት 366 አድርሷል።

    ባንኩ ባለፉት ዓመታት ባከናወናቸው አመርቂ ውጤቶች የተነሳም የባንኩ ጠቅላላ ሀብት የዛሬ 3 ዓመት ከነበረበት ብር 25 ቢሊዮን ከእጥፍ በላይ ጭማሪ በማሳየት ብር 55 ቢሊዮን ሁኗል። እንደዚሁም የባንኩ ጠቅላላ ካፒታል መጠባበቂያዎችን ጨምሮ ብር 6.5 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን የባንኩ የተከፈለ ካፒታል ደግሞ ብር 2.9 ቢሊዮን ሆኖ ተመዝግቧል።

    የባንኩ ባለአክሲዮኖች በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት ውስጥ የባንኩን የተከፈለ ካፒታል ብር 6 ቢሊዮን ለማድረስ በተሰማሙት መሠረት በሚቀጥሉ ዓመታት የባንኩ የተከፈለ ካፒታል ከፍተኛ ጭማሪ እንደሚያሳይ ይጠበቃል።

    አዋሽ ባንክ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የቆየ ሲሆን በዘንድሮ ዓመትም በተመሳሳይ መልኩ ለበጐ ሥራዎች የሚውል የብር 30,000,000.00 (ሰላሳ ሚሊዮን) እርዳታ እንዲሰጥ የዳይሬክተሮች ቦርድ ወስኗል።

    ምንጭ፦ አዋሽ ባንክ

    አዋሽ ባንክ

    Semonegna
    Keymaster

    ኢትፍሩት የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ሌሎች ሸቀጦችን ጨምሮ በመዲናችን አዲስ አበባ ከ60 በላይ ኮንቴነሮችን ይዞ የደንበኞችን ፍላጎት የማርካትና ገበያዉን የማረጋጋት ዓለማ ሰንቆ እየ ሠራ ቢሆንም የተፈለገውን ውጤት አያመጣሁ አይደለም ብሏል።

    አዲስ አበባ (ኢቢሲ)– የቀድሞው የኢትዮጵያ አትክልትና ፍራፍሬ ገበያ (ኢትፍሩት) ለአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ እየሰጠ ያለው አገልግሎት የደንበኞቹን ፍላጎት እያረካ አለመሆኑን ተጠቃሚዎች ገለጹ።

    የከተማዋ ሸማቾች ምርትና ሸቀጦችን በግል ከሚያቀርቡ የንግድ ተቋማት ይልቅ ኢትፍሩት በዋጋ የተሻለ መሆኑን የሚገልፁት አስተያየት ሰጪዎቹ ፥ ዘይትና ስኳርን ፍለጋ ከጠዋት ተነስቶ እስከ እኩለ ቀን ድረስ በኢትፍሩትና ሸማቾች ሱቆች በራፍ መሰለፍ የተለመደ ተግባር መሆኑን ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ገልፀዋል።

    ኢትፍሩት የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ሌሎች ሸቀጦችን ጨምሮ በመዲናችን አዲስ አበባ ከ60 በላይ ኮንቴነሮችን ይዞ የደንበኞችን ፍላጎት የማርካትና ገበያዉን የማረጋጋት ዓለማ ሰንቆ እየ ሠራ ቢሆንም የተፈለገውን ውጤት አያመጣሁ አይደለም ብሏል።

    ድርጅቱ የፍራፍሬና አትክልት ምሮቶችን ጨምሮ ከሌሎች አምራቾች እየገዛ ስለሚሸጥ በሚፈለገዉ ልክ የአቅርቦት መጠኑን ማሻሻል አለመቻሉን ለኢቢሲ አመልክቷል።

    Business Cooperation: Meki Batu Vegetable & Fruit Growers and Ethiopian Airlines

    ኢትፍሩት ለከተማዋ ነዋሪ በተመጣጣኝ ዋጋ ሸቀጥና ምርትን በማቅረብ የተጠቃሚዎችን ፍላጎት ለሟሟላት ከአዲስ አበባ ዉጭ በአንዳንድ ክልሎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ህብረተሰቡን በማገልገል ላይ መሆኑን በኮሮፕሬሽኑ የንግድ ሥራ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መህዲ አስፋው ተናግረዋል።

    ከመሠረታዊ የፍጆታ እቃዎች አቅርቦትና ቁጥጥር ጋር በተያያዘ እየተስተዋሉ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ዘመናዊ አሠራር በመዘርጋት ሂደት ላይ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ አመልክቷል።

    በቢሮው የግብይት ተሳታፊዎች ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን በቀለ እንደሚሉት እያንዳንዱን ተጠቃሚ ጋር ለመድረስ እንዲያስችል ከኢትፍሩት ሱቆች ባሻገር በግለሰብ ሱቆች መገልገል የሚያስችሉ ከ1 ሚሊየን በላይ ካርዶች ተዘጋጅተዉ ለህብረተሰቡ በመሰረጨት ላይ ናቸዉ።

    ኃላፊው እንደሚሉት ካርዶቹን በመያዝ ህብረተሰቡ ትስስር ከተፈጠረባቸዉ ሱቆች የፍጆታ ሸቀጦችን በመሸመት ካለአስፈላጊ መጉላላትና ሰልፍ ራስን ማዳን ይቻላል።

    ከ8 በላይ የአትክልትና ፍራፍሬና የፋብርካ ምርቶችን ለህብረተሰቡ በማቅረብ ላይ የሚገኘዉ ኢትፍሩት ከ5 መቶ በላይ ሠራተኞችን ይዞ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች በ60 ኮንቴኔር ሱቆች አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።

    በቅርቡም በንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ስር ተደራጅቶ ለህብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እይተንቀሳቀሰ መሆኑን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

    ኢትፍሩት የተመሠረተው በቀድሞ የኢትዮጵያ መንግስት (ደርግ)የመንግስት እርሻ ልማድ ድርጅት ስር እ.ኤ..አ በ1980 ዓ.ም. ሲሆን የተመሠረተበትም ዓላማ በመንግስት እርሻ ልማቶች የተመረቱ አትክልትና ፍራፍሬዎችን ለገበያ ለማቅረብ ነበር። ከመንግስት ስርዓት ለውጥ (እ.ኤ..አ 1991 ዓም) በኋላ የሽግግሩ መንግስት በመንግስት የተያዙ ንብረቶችን ለግልና ለሕዝብ ለማስተላለፍ በወጣው አዋጅ መሠረት እ.ኤ.አ በ1993 ዓ.ም.  በአዋጅ ቁጥር 131/1993 ኢትፍሩት የሕዝብ ድርጅት (public enterprise) ሆኖ ዕውቅናን አግኝቷል።

    ምንጭ፦ ኢቢሲ እና ኢትፍሩት 

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አፍሪካዊ የአመራር መጽሔት (African Leadership Magazine) በሚያዘጋጀው የዓመቱ ምርጥ አፍሪካዊ ምርጫ ላይ ለ2018 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ) የዓመቱ ምርጥ አፍሪካዊ መሪ ለመባል ዕጩ ሆነው ተመርጠዋል።

    መጽሔቱ የዓመቱ ምርጥ ሰው ብሎ የሚመርጠው በተለያዩ ዘርፎች ለአፍሪካ እና አፍሪካውያን የላቀ አስተዋጽዖ ያበረከቱ እና እጅግ ጉልህ የሆነ ተጽዕኖ የፈጠሩ አፍሪካውያንን በማወዳደር ሲሆን፥ መጽሔቱ መታተም ከጀመረበት እ.ኤ.አ 2008 ዓ.ም. ጀምሮ ሽልማቱ ይሰጣል።

    ዘንድሮ በእጩነት ከቀረቡት መካከል በወንድ መሪዎች ዘርፍ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በ97.25% ድምጽ በማግኘት ቀዳሚውን ቦታ ሲይዙ፣ የቀድሞው የቦትስዋና ፕሬዝደንት የሆኑት ሰረትሴ ካማ ኢያን ካማ (Serêtsê Khama Ian Khama) በ2.00% የምርጫ ድምጽ ሁለተኛ፣ የነዳጅ ላኪ ሀገራት ህብረት (Organization of the Petroleum Exporting Countries – OPEC) ጠቅላይ ሰብሳቢ የሆኑት ናይጀርያዊው መሐመድ ሳኑሲ ባርኪንዶ (Mohammed Sanusi Barkindo) በ0.75% የምርጫ ድምጽ በሦስተኝነት ይከተላሉ።

    የአፍሪካዊ የአመራር መጽሔት ዋና አዘጋጅ ዶ/ር ኬን ጊያሚ (Dr. Ken Giami) እንደገለጸው የዘንድሮው ምርጫ ከሌሎች ጊዘያት በተለየ መልኩ ብዙ ሰዎች፣ ከሁሉም የ አፍሪካ አቅጣቻዎች ድምጽ የሰጡበት ሁሉም ዕጩዎች ያጋጠማቸውን ተግዳሮቶች አሸንፍው በተሠማሩባቸው መስኮች ሁሉ የሚጠበቅባቸውን በመወጣት ልቀው ሊታዩ ችለዋል ብሏል።

    በሰባት የዕጩነት ቦታዎች (ስድስት ዘርፎች) በአጠቃላይ ሰላሳ (30) አፍሪካውያን ለዕጩኘት የቀረቡ ሲሆን፥ በሀገር ደረጃ በአጠቃላይ ናይጄርያ አስር (10) ዕጩዎችን በማስመረጠ ቀዳሚውን ስፍራ ይዛለች። የሰላሳዎች ዕጩዎች ሀገራዊ ስብጥር፥ ቦትስዋና (2)፣ ኬፕ ቨርዴ (1)፣ ግብጽ (1)፣ ኢትዮጵያ (1)፣ ጋና (4)፣ ኬንያ (1)፣ ሞሮኮ (2)፣ ናይጄርያ (10)፣ ሴኔጋል (1)፣ ደቡብ አፍሪካ (5)፣ እስዋቲኒ/ስዋዚላንድ (1)፣ እና ታንዛንያ (1) መሆናቸው ታውቋል።

    ከዕጩዎቹ መካከል አሸናፊዎቹን ለመለየት ማንኛውም ግለሰበ የመጽሔቱ ድረ-ገጽ ላይ ሄዶ መምረጥ (ድምጽ መስጠት) ይችላል። (ድረ-ገጹን እዚህ ጋር ያገኙታል)። በድረ-ገጽ ድምጽ የመስጠት ተግባር እ.ኤ.አ ታህሳስ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. በመካከለኛው አፍሪካ ሰዓት እኩለ ሌሊት (10th December 2018, at midnight Central African Time.) ላይ ይጠናቀቃል ይዘጋል።

    አምና እ.ኤ.አ በ2017 ዓ.ም. በተደረገው ተመሳሳይ ምርጫ የሩዋንዳው ፕሬዚደንት ፖል ካጋሜ (Paul Kagame) የዓመቱ ምርጥ አፍሪካዊ መሪ ሆነው መመረጣቸው ይታወሳል።

    አፍሪካዊ የአመራር መጽሔት (African Leadership Magazine) መቀመጫነቱን በእንግሊዝ ሀገር፣ ፖርትስማውዝ ከተማ አድርጎ አፍሪካንና አፍሪካውያንን ከተቀረው ዓለም ጋር ለማገናኘት፣ ለማቀራረብ የሚሠራ የህትመት ድርጅት ነው። በየዓመቱም በተለያዩ ዘርፎች አፍሪካና አፍሪካውያን ላይ በተለያየ መልኩ ጉልህ ሚና የተጫወቱ አፍሪካውያንን “የዓመቱ ምርጥ አፍሪካውያን” ብሉ ይመርጣል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ዐቢይ አህመድ

Viewing 15 results - 631 through 645 (of 730 total)