Search Results for 'የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር'

Home Forums Search Search Results for 'የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር'

Viewing 4 results - 16 through 19 (of 19 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    የጂንካ ዩኒቨርስቲ ባህላዊ እሴቶች ጉልተው እንዲወጡ የሚያደርገው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለጸ
    —–

    የጂንካ ዩኒቨርስቲ ባህላዊ እሴቶች ጎልተው እንዲወጡ የሚያድርገውን ጥረት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጅንካ ዩኒቨርስቲ ባዘጋጀው ባህላዊ ፌስቲቫል ላይ የተገኙ ተጋባዥ እንግዶችና ታዳሚዎች ገለጹ ።

    የጅንካ ዩኒቨርስቲ “ባህላዊ ዕሴቶቻችን ለአንድነታችንና ለልማታችን” በሚል መሪ ቃል በጅንካ ዩኒቨርሲቲ ደማቅ ባህላዊ ፌስቲቫል አካሂዷል፡፡
    በፌስቲቫሉ የተገኙ የተለያዩ ተጋባዥ እንግዶችና ታዳሚዎች ለዋልታ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው እያደረገ ያለውን ባህላዊ እሴቶች የማስተዋወቅ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንደለበት አንስተዋል፡፡

    ዩኒቨርሲቲው በበኩሉ የአከባቢውን ማህበረሰብ በጥናትና ምርምር በቴክኖሎጂ በማገዝ ባህላዊ እሴቶች ይበልጥ ጎልተው የሚወጡበትን የተጠናከረ ሥራ እያከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

    የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ደኤታ ፕሮፌስር አፈወርቅ ካሱ በበኩላቸው ፌስቲቫል በዞኑና አከባቢዋ የሚኖሩ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ይበልጥ ከማጠናክር አንፃር ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል፤ በተጨማሪም የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለአከባቢው ልዩ ትኩረት በመሥጠት እንደሚሠራ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ አክለው ገልፀዋል፡፡

    ዋልታ

    Semonegna
    Keymaster

    ድሬ ዳዋ (ሰሞነኛ)– የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዘላቂ የሆነ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር በአንድነት ለመሥራት ቃል ገቡ። ከሰሞኑ ግጭት ውስጥ የገቡ ተማሪዎች የሀይማኖት አባቶችና ከፍተኛ የመንግስት አካላት በተገኙበት ዕርቅ አውርደዋል።

    ሰሞኑን ዩኒቨርሲቲው ውስጥ ባልተከሰተና በሀሰት በተሰራጨ መረጃ ምክንያት በዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች መካከል የተፈጠረው ግጭት ዳግመኛ እንዳይከሰት ተማሪዎቹ ከፍተኛ ጥረት እንደሚያደርጉና በተማሪዎች መካከል የሚፈጠሩ የግለሰብ ግጭቶችንም ወደ ቡድንና የብሄር ግጭትነት ለመቀየር የሚፈልጉ አካላትን ጥረት እንደሚያወግዙ ተናግረዋል።

    ኅዳር 13 ቀን 2011 ዓ.ም. የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ስልጠና ማዕከል ውስጥ በተካሄደው የእርቅ ዝግጅት ላይ የተሳተፉ ተማሪዎች በሰጡት አስተያየት፥ ተማሪዎችን በብሄር እንዲጋጩ ሁኔታዎችን በሚፈጥሩና በሚያነሳሱ ተማሪዎችና አገልግሎት ሰጪ አካላት ላይ ዩኒቨርሲቲው ክትትል አድርጎ አስተማሪ እርምጃዎችን በመውሰድ የሕግ የበላይነትን እንዲያስከብር ጠይቀዋል።

    ከየትኛውም ብሄር ጥሩ ሰዎች እንዳሉ ሁሉ መጥፎዎችም ሊኖሩ እንደሚችሉና እነዚህ ሰዎች በዩኒቨርሲቲያችን ውስጥ የእኩይ ተግባራቸውን ለማስፈፀም ብሄራቸውን ሽፋን በማድረግ ለመጠቀም ስለሚሞክሩ ተማሪዎች ተሳስተው የወንጀለኞች ተባባሪና የእኩይ ተግባራት ማስፈፀሚያ እንዳይሆኑ መረጃዎችንና ሁኔታዎችን ከስሜት በጸዳና በምክንያታዊነት እንዲመለከቱ የመድረኩ ተሳታፊዎቹ ጥሪ አቅርበዋል።

    These two Ethiopian students are working to launch their own rocket – the future Eng. Kitaw Ejigu

    የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ባለፉት ዓመታት በአንድነት ጥያቄያቸውን ሲያቀርቡ እንደነበርና በመካከላቸውም አለመስማማቶች ሲፈጠሩ በራሳቸው መንገድ ተወያይተው ችግሮችን ሲፈቱ እንደነበር አስታውሰው ዘንድሮም ይህን አንድነታችንን በማስጠበቅ በመካከላችን ልዩነቶችን በመፍጠርና ግጭት እንዲቀሰቀስ በማነሳሳት የድብቅ ሴራቸው ማስፈፀሚያ ሊያደርጉን የሚፈልጉ አካላትን ሴራ እናከሽፋለን ብለዋል። ባለፉት ጥቂት ቀናት መለስተኛ ግጭት በመፈጠሩ ይቅርታ የተጠያየቁት ተማሪዎች አጋጣሚውን ለቀጣይ በመማሪያነት በመውስድ ችግሮችን በጋራ ለመከላከል እንደሚጠቀሙበት ተናግረዋል።

    የአማራ ክልልንና የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን (አዴፓ) ወክለው የተገኙት አቶ ባዘዘው ጫኔ እንደተናገሩት ችግሩ በመፈጠሩ የአማራ ክልልና የክልሉ ገዢ ፓርቲ አዴፓ ማዘኑን ገልፀው ግጭቱ ሳይሰፋና የከፋ ችግር ሳያስከትል በቁጥጥር ስር እንዲውል የዩኒቨርሲቲው አመራሮችና ተማሪዎች እንዲሁም የአካባቢው ማኅበረሰብ አካላት ላደረጉት ጥረት ደግሞ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

    ሰዎች በብዛት ተሰባስበው በሚኖሩባቸው አካባቢዎች ግጭት ሊከሰት እንደሚችል አቶ ባዘዘው አስታውሰው በግለሰቦች የሚጀመር ግጭትን ወደብሄር ማዞሩ አደገኛና ሊወገዝ የሚገባው መሆኑን ተናግረዋል። በሐረማያ ዩኒቨርሲቲም ሰሞኑን በተከሰተው ግጭት በርካታ ተማሪዎች ጉዳዩን በማውገዝ ወደ ግጭት ባለመግባታቸው ቶሎ በቁጥጥር ስር እንዲውል እንዳስቻለ የተናገሩት አቶ ባዘዘው ተማሪዎች በአንድነት ተሳስቦ በፍቅር የመኖር ልማዳቸውን በማጎልበት የዩኒቨርሲቲያቸውንና የአካባቢያቸውን ሰላም እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርበዋል።

    የኦሮሚያ ክልልንና የክልሉ ገዢ ፓርቲ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን (ኦዲፓ) ወክለው የተገኙት አቶ አብዱላዚዝ መሀመድ ባደረጉት ንግግር ተማሪዎቹ እርቅ ለማውረድ ያሳዩትን ፍላጎት አድንቀዋል። አቶ አብዱላዚዝ አያይዘውም ባለፉት ሰባት ወራት መንግስት ለዓመታት የተከማቹ የሕዝብ ጥያቄዎችን በመፍታት ላይ እንደሚገኝና በዚህም ከፍተኛ ለውጥ እየተመዘገበ በመሆኑ ይህን ለውጥ የማይፈልጉ አካላት የመንግስትን የለውጥ ጉዞን ለማደናቀፍ በየቦታው ግጭቶች እንዲነሱ በማድረግ መንግስትን ግጭቶችን በመከላከል ላይ እንዲጠመድ በማድረግ የተጀመሩ የለውጥ ጉዞዎችን ለማደናቀፍ ጥረት እያደረጉ እንደሆነ ተናግረዋል።

    ስለዚህ የነገዋ ባለተስፋና የዜጎቿ መኩሪያ የሆነች ኢትዮጵያን ተረካቢ የሆኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ይህን ተረድተው ራሳቸውን ከስሜታዊነት አርቀው፣ መረጃዎችን በጥንቃቄ በመመርመር ምክንያታዊ በመሆን ግጭቶች እንዳይከሰቱ ጥረት እንዲያደርጉና ከግጭቶች በመራቅ የእኩይ ተግባር ማስፈፀሚያ ከመሆን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አቶ አብዱላዚዝ ለተማሪዎች ጥሪ አቅርበዋል።

    በሀገራችን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የተሻለ አስተሳሰብ ያላቸው ወጣቶች የሚገኙበት እንደሆነ እንደሚታመን የተናገሩት የሳይንስና የከፍተኛ ትምህር ጉዳዮች ሚኒስቴር ተወካይ አቶ ጌታቸው ነጋሽ በአስተሳሰባችሁ መላቃችሁንና ማኅበረሰባችን የሰጣችሁን ይህን ግምት ትክክለኛነት ለማሳየት ምክንያታዊ በመሆን ለነገሮች መፍትሄ በመስጠት ልታስመሰክሩ እንጂ እንደዘይትና ውሃ የተፈጠራችሁበት ነገር ሳይለያይ በብሄር ልትከፋፈሉና ልትጋጩ አይገባም ብለዋል።

    የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተወካይ ፕሬዝዳንት ጀማል ዩሱፍ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተማሪዎች በብሄር ከማሰብ ወጥተው አንድነት ላይ በማተኮር የዩኒቨርሲቲውን ሰላም በጋራ በማስጠበቅ በቂ ዕውቀት ጨብጠው በሀገራችን የእድገት ጉዞ ላይ የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉና ራሳቸውን የጥፋት ኃይሎች ድብቅ ዓላማ አስፈፃሚ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

    በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዳይኖር እንቅፋት ይፈጥራሉ በማለት በተማሪዎች በቀረቡ ጥቆማዎች ላይም አስፈላጊውን ክትትል ግምገማ በማድረግ የእርምት እርምጃዎችና የሕግ የበላይነትን የማስከበር ሥራዎች እንደሚከናወኑ ዶ/ር ጀማል አረጋግጠዋል።

    በእርቅ መድረኩ ላይ የተሳተፉ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎችም በተማሪዎች መካከል ሰላም፣ ፍቅርና ይቅር ባይነት እንዲጎለብት የበኩላቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡ ቃል ገብተዋል።

    ምንጭ፦ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያ (HU FM 91.5 RADIO)

    የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአገር ውስጥ ሰላም እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን በሕዝቡ ፈቃድ ላይ የተመሠረተ አንድ የፖለቲካ ማኅበረሰብ በጋራ መገንባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራ የሰላም ሚኒስቴር እንዲቋቋም ተወስኗል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የሚኒስትሮች ምክር ቤት መስከረም 30 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የፌደራል መንግሥትን አስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በተዘጋጀ ረቀቅ አዋጅ ላይ መክሮ እንዲጸድቅ ለተወካዮች ምክር ቤት እንዲላክ ወስኗል።

    በውይይቱ ላይ የአስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን ያስፈለገበት ዋና ዋና ምክንያቶች እንደሚከተለው ቀርቧል፦

    1. የሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በቀሪው ጊዜ ያልተጠናቀቁ ሥራዎችን አካክሶ ለመፈጸም የሚያስችል አደረጃጀት በማስፈለጉ፤
    2. አገራችን የተያያዘችውን የለውጥ ጉዞ ለማስቀጠልና የማይቀለበስበት ደረጃ ላይ ለማድረስ የሚያስችል አደረጃጀትን መከተል በማስፈለጉ፤
    3. የአስፈጻሚ አካላትን ቁጥር ቀልጣፋ፣ ወጪ ቆጣቢና ውጤታማ ለማድረግ በማስፈለጉ፤
    4. ተደራራቢና ድግግሞሽ ሥልጣንና ተግባር የያዙ የመንግሥት ተቋማትን መቀነስ ወይም ለሥራቸው ቅርብ ከሆነ ሌላ የመንግሥት ተቋም ጋር እንዲዋሃዱ ማድረግ በማስፈለጉ፤

    እንደሆነ በስብሰባው ላይ ተብራርቷል።

    በምክር ቤቱም ውሳኔ የካቢኔ አባላት ቁጥር ከ28 ወደ 20 እንዲቀንስ ተደርጓል፤ ዋና ዋናዎቹ ለውጦችም:-

    • የንግድ ሚኒስቴር እና የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተዋህደው – የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እንዲሆን ፤
    • በየሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተዋህደው – የኢኖቬሽንና የቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንዲሆን ፤
    • የከተማ ልማት ሚኒስቴር እና የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ተዋህደው – የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር እንዲሆን
      ወስኗል።

    ሌሎች ተጠሪ ተቋማትም በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲዋሃዱ ውሳኔ የተሰጠባቸው ይገኛሉ።

    ሌላው ቁልፍ ውሳኔ በአገር ውስጥ ሰላም እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን በሕዝቡ ፈቃድ ላይ የተመሠረተ አንድ የፖለቲካ ማኅበረሰብ በጋራ መገንባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራ የሰላም ሚኒስቴር እንዲቋቋም ተወስኗል።

    ከትምህርት ሚንስቴር ሁሉንም ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን በመውሰድ እንዲሁም ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር ስር የሚገኙት ሁለቱን ዩኒቨርሲቲዎች በመጨመር “የከፍተኛ ትምህርትና የሳይንስ ሚንስቴር” ተብሎ እንዲደራጅ ተወስኗል።

    በተጨማሪም የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የገቢዎች ሚኒስቴር እና ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ የሆነ የጉምሩክ ኮሚሽን በመሆን ሁለት ተቋማት ሆነው እንዲደራጁ ተወስኗል።

    በአዲሱ አደረጃጀት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሚንስቴር ቀርቶ በቀጣይነት የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ለማስተዳደር መሠረታዊ ሚናቸው ንግድ የሆኑትን በመለየት የመንግስትን የባለቤትነት ሚና በተገቢው ሁኔታ የሚያስተዳደር “የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ” በገንዘብ ሚኒስቴር ሥር እንዲቋቋም ተወስኗል። ይህም የመንግሥት ቁልፍ ሚና የሆነው ቁጥጥር (regulation) በልማት ድርጅቶች ላይ ካለው የባለቤትነት ሚና ተለይቶ እንዲታይ እንደሚያግዝ ታምኖበታል።

    ረቂቅ አዋጁ ሌሎች መለስትኛ ለውጦችንም የያዘ ሲሆን፥ በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍጹም አረጋ የፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የሰላም ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአገር ውስጥ ሰላም እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን በሕዝቡ ፈቃድ ላይ የተመሠረተ አንድ የፖለቲካ ማኅበረሰብ በጋራ መገንባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራ የሰላም ሚኒስቴር እንዲቋቋም ተወስኗል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የሚኒስትሮች ምክር ቤት መስከረም 30 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የፌደራል መንግሥትን አስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በተዘጋጀ ረቀቅ አዋጅ ላይ መክሮ እንዲጸድቅ ለተወካዮች ምክር ቤት እንዲላክ ወስኗል።

    በውይይቱ ላይ የአስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን ያስፈለገበት ዋና ዋና ምክንያቶች እንደሚከተለው ቀርቧል፦

    1. የሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በቀሪው ጊዜ ያልተጠናቀቁ ሥራዎችን አካክሶ ለመፈጸም የሚያስችል አደረጃጀት በማስፈለጉ፤
    2. አገራችን የተያያዘችውን የለውጥ ጉዞ ለማስቀጠልና የማይቀለበስበት ደረጃ ላይ ለማድረስ የሚያስችል አደረጃጀትን መከተል በማስፈለጉ፤
    3. የአስፈጻሚ አካላትን ቁጥር ቀልጣፋ፣ ወጪ ቆጣቢና ውጤታማ ለማድረግ በማስፈለጉ፤
    4. ተደራራቢና ድግግሞሽ ሥልጣንና ተግባር የያዙ የመንግሥት ተቋማትን መቀነስ ወይም ለሥራቸው ቅርብ ከሆነ ሌላ የመንግሥት ተቋም ጋር እንዲዋሃዱ ማድረግ በማስፈለጉ፤

    እንደሆነ በስብሰባው ላይ ተብራርቷል።

    በምክር ቤቱም ውሳኔ የካቢኔ አባላት ቁጥር ከ28 ወደ 20 እንዲቀንስ ተደርጓል፤ ዋና ዋናዎቹ ለውጦችም:-

    • የንግድ ሚኒስቴር እና የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተዋህደው – የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እንዲሆን ፤
    • በየሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተዋህደው – የኢኖቬሽንና የቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንዲሆን ፤
    • የከተማ ልማት ሚኒስቴር እና የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ተዋህደው – የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር እንዲሆን
      ወስኗል።

    ሌሎች ተጠሪ ተቋማትም በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲዋሃዱ ውሳኔ የተሰጠባቸው ይገኛሉ።

    ሌላው ቁልፍ ውሳኔ በአገር ውስጥ ሰላም እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን በሕዝቡ ፈቃድ ላይ የተመሠረተ አንድ የፖለቲካ ማኅበረሰብ በጋራ መገንባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራ የሰላም ሚኒስቴር እንዲቋቋም ተወስኗል።

    ከትምህርት ሚንስቴር ሁሉንም ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን በመውሰድ እንዲሁም ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር ስር የሚገኙት ሁለቱን ዩኒቨርሲቲዎች በመጨመር “የከፍተኛ ትምህርትና የሳይንስ ሚንስቴር” ተብሎ እንዲደራጅ ተወስኗል።

    በተጨማሪም የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የገቢዎች ሚኒስቴር እና ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ የሆነ የጉምሩክ ኮሚሽን በመሆን ሁለት ተቋማት ሆነው እንዲደራጁ ተወስኗል።

    በአዲሱ አደረጃጀት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሚንስቴር ቀርቶ በቀጣይነት የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ለማስተዳደር መሠረታዊ ሚናቸው ንግድ የሆኑትን በመለየት የመንግስትን የባለቤትነት ሚና በተገቢው ሁኔታ የሚያስተዳደር “የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ” በገንዘብ ሚኒስቴር ሥር እንዲቋቋም ተወስኗል። ይህም የመንግሥት ቁልፍ ሚና የሆነው ቁጥጥር (regulation) በልማት ድርጅቶች ላይ ካለው የባለቤትነት ሚና ተለይቶ እንዲታይ እንደሚያግዝ ታምኖበታል።

    ረቂቅ አዋጁ ሌሎች መለስትኛ ለውጦችንም የያዘ ሲሆን፥ በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍጹም አረጋ የፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የሰላም ሚኒስቴር

Viewing 4 results - 16 through 19 (of 19 total)