Search Results for 'ደብረ ብርሃን'

Home Forums Search Search Results for 'ደብረ ብርሃን'

Viewing 13 results - 16 through 28 (of 28 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር አልማዝ አፈራ በዚህ ፕሮጀክት የተሳተፉ ተመራማሪዎችን ያሉትን ተግዳሮቶች ተቋቁመው ለዚህ በመብቃታቸው ምስጋና ቸረዋቸዋል።

    ደብረ ብርሃን (ሰሞነኛ)– የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማኅበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ከኢፌዴሪ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ ይምሎ ቀበሌ በተቀናጀ የአሳ፣ የዶሮ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ላይ ሲያካሂድ የቆየውን የምርምር ፕሮጀክት አጠናቆ ለዞኑ አስተዳደርና ለአካበቢው ማኅበረሰብ አስረከበ።

    በርክክብ ሥነ-ስርዓቱ ወቅት የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ መምህርና መሪ ተመራማሪ ዶ/ር ገዛኸኝ ደግፌ እንደተናገሩት ምርምሩ በትንሽ ቦታ አሳን፣ ዶሮንና አትክልትን አቀናጅቶ ማልማት የሚያስችል የቴክኖሎጅ ዕውቀትን በመጠቀም የአሳ፣ የዶሮና የአትክልት ልማቱን አቀናጅቶ መሥራት እንደሚቻል ነው ብለዋል። በዚህም የዶሮ ኩስን ለአሳዎች ምግብ እንዲውል እንዲሁም “vermicompost” ቆሻሻን ወደ ጠቃሚ ነገርነትና ማዳበሪያነት የሚቀይሩ ትሎችን ለዶሮዎችና ለአሳ ምግብነት እንዲውል የሚያስችል እንደሆነ አብራርተዋል።

    በምስራቅ ጎጃም ዞን ስንዴ አምራች ወረዳዎች ለገበሬዎች የቀረቡላቸው ኮምባይነሮች በምርታቸው ላይ ጉልህ አስተዋጽዖ እያደረጉ ነው

    አቶ ተፈራ ወንድማገኘሁ የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳደሪ እንዳሉት ይህ ለምርቃት የበቃው የምርምር ሥራ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በዞኑ ከሚያከናውናቸው ምርምሮች አንዱ ሲሆን ፣ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ፈጻሚነትና በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የገንዘብ ድጋፍ የተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ዋና አስተዳዳሪው አክለው እንዳስታወቁት ይህንን ምርምር በዞኑ በሚገኙ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ለማስፋፋት ትልቅ ኃላፊነትና አደራ የተጣለባቸው መሆኑን አውስተው ለተግባራዊነቱም እንደሚሠሩ ተናግረዋል።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጅነር ጌታሁን መኩሪያ ባደረጉት ንግግር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤታቸው ከሚደግፋቸው በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በሚባል ደረጃ ከ60 በላይ ምርምሮች መካከል የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ አንዱና ውጤታማው በመሆኑ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ በሚችሉ ትናንሽ ፕሮጀክቶች በመደገፍ የሀገራችንን ልማት ማረጋገጥ ይኖርብናል ብለዋል። ይህን ፕሮጀከት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ለሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች እንዲተላለፍ ማኑዋልና ስታንዳርድ ተዘጋጅቷል። የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደርም በአማራ ክልል ለሚገኙ ሁሉም ዞኖች እንዲያደርስ ኃላፊነት የተሰጣቸው ሲሆን በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲሰራጭ አናደርጋለን ብለዋል።

    ዶ/ር አልማዝ አፈራ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዚዳንት በበኩላቸው በዚህ ፕሮጀክት የተሳተፉ ተመራማሪዎችን ያሉትን ተግዳሮቶች ተቋቁመው ለዚህ በመብቃታቸው ምስጋና ቸረዋቸዋል። እንደ ፕሬዚዳንቷ ገለፃ፥ በሀገራችን እስከ ሁለት ሚሊዮን የሚደርሱ ሥራ-አጥ ወጣቶች መኖራቸው የሚታወቅ ሲሆን እንደነዚህ ዓይነት የምርምር ሥራዎች ደግሞ ወጣቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚ በማድረግ ሚናቸው የጎላ ነው ብለዋል። ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲም ብዙ የምርምር ውጤቶች ያሉት ሲሆን እነዚህን ምርምሮች ወደ ፕሮጀክት መቀየር የሚያስችል ተሞክሮ ስለሆነ ይህ ትልቅ ማሳያ ይሆነናል ብለዋል። በመጨረሻም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርንና የኤፍራታና ግድም ወረዳ አስተዳደርን ላደረጉት ድጋፍና ትብብር ምስጋና አቅርበዋል።

    ምንጭ፦ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የተቀናጀ የግብርና ምርምር ፕሮጀክት


    Anonymous
    Inactive

    ተረፈ-ምርትን በመጠቀም ማምረት የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ ሆነ
    —–

    ቆሻሻና አነስተኛ ውሃን በመጠቀም የአሳና ዶሮ ምግብ፣ ማዳበሪያ፣ አትክልትና ፍራፍሬ በቀላሉ ማምረት የሚያስችል የተቀናጀ የግብርና ዘዴ የምርምር ፕሮጀክት ተጠናቆ ወደ ስራ ሊገባ ነው፡፡

    በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ድጋፍ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ለ3 ዓመታት ባደረገው ምርምር አርሶ አደሩ በአነስተኛ የጓሮ መሬትና ውስን የጉድጓድ ውሃ በማዘጋጀት ዘርፈ ብዙ ምርት መሰብሰብ የሚቻልበት ፕሮጀክት ተጠናቆ ለትግበራ ተዘጋጅቷል፡፡

    ምርምሩ በተደረገበት በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ ይምሎ ቀበሌ የተደራጁ ወጣቶችን በማሳተፍ ውጤታማ የአሳ፣ የዶሮ፣ የማዳበሪያ፣ የሙዝና የሸንኮራ አገዳ ምርቶችን በአነስተኛ መሬት ላይ ማሳካት ተችሏል፡፡

    በፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የተገኙት የአ.ፌ.ዴ.ሪ. ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ይህን ፕሮጀክት ትልቅ የሚያደርገው ወጣቶች በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሊጠቀሙበት የሚችሉበት መሆኑ ነው ብለዋል፡፡

    ሚኒስትሩ የፕሮጀክቱን የአተገባበር ሰነድ ለዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ለአቶ ተፈራ ወንድማገኘሁ አስረክበዋል፡፡

    ምንጭ፦ ዋልታ ሚዲያ

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – STEMpower የተሰኘ መቀመጫውን USA (ሳሌም፥ ማሳቹሴትስ፣ አሜሪካ) ያደረገ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሒሳብ ትምህርቶችን በዩኒቨርሲቲዎች እየረዳ የሚገኝ ሲሆን በአገራችን 13 ማዕከላትን ከፍቶ በትብብር እየሠራና እየረዳ ይገኛል።

    ድርጅቱ የድጋፍ አድማሱን በማስፋት በኢትዮጵያ ተጨማሪ 10 ማዕከላትን (ሰባት ማዕከላትን በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች፣ ሶስቱን በተለያዩ ከተሞች እ.አ.አ. በ2019) ለመክፈት ከኢፌዴሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም ከሰባቱ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የትብብር ስምምነት የካቲት 14 ቀን 2011ዓ.ም. ተፈራርመዋል።

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ሂሩት ወልደማርያም (ፕ/ር) STEMpower ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ትምህርቶችን ለማበልጸግ እያደረገ ያለውን ትብብር በማመስገን፥ ዩኒቨርሲቲዎችም ዕድሉን በመጠቀም በአግባቡ ማዕከላቱን ማሳለጥ እንደሚጠበቅባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

    አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በማስተማሪያ ክፍሎቹ ውስጥ ዲጂታል ሰሌዳዎችን መጠቀም ጀመረ።

    የሳንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር) በበኩላቸው ለሰባቱ ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚዳንቶች (አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲአዲግራት ዩኒቨርሲቲአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲጅማ ዩኒቨርሲቲ እና ወሎ ዩኒቨርሲቲ) ማዕከሉን በመጠቀም በአካባቢዎቻቸው ያሉትን የማኅበረሰብ ችግሮች መፍታት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

    የSTEMpower አስተባባሪ ዳይሬክተርና ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ቅድስት ገብረአምላክ፥ “STEMpower ከየት ወዴት?” በሚል ርዕስ ከድርጅቱ አመሠራረት ጀምሮ ዓላማውን፣ አሁን ያለበት ሁኔታ እና የወደፊት ዕቅድ አጭር ማብራሪያ ለተሳታፊዎቹ አቅርበዋል። ለወደፊትም ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በስፋት እንደሚሠሩ ፣ በ2040 የበለጸገች ኢትዮጵያን ማየት እንደሆነ ገልጸዋል።

    አገራችን ኢትዮጵያ የራሷን የሆነ ጥንታዊ ታሪክና ባህል ያላት አገር እንደመሆኗ ድርጅቱ በማኅበራዊ ሳይንስ ላይም ትኩረት እንዲያደርግ ከተሳታፊዎቹ አስተያየት ተሰንዝሯል።

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ማዕከሎቹ በከፍተኛ ትምህርት እና በሳይንስ ትምህርቶች አከባቢ የሚስተዋሉትን ችግሮች በመቅረፍ የአገሪቱን ብልጽግና ከማረጋገጥ ረገድ መልካም ሁኔታ እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    STEMpower


    Semonegna
    Keymaster

    የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ያዘጋጁት የዘንድሮው ውድድር ለ2ኛ ጊዜ የተካሄደ ሲሆን፥ በባለፈው ዓመት የተመረጠችው ወ/ሪት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በአማራ ክልል በተካሄደው የቁንጅና ውድድር ላይ ተሳትፋ 3ኛ ደረጃ መውጣቷም ተገልጿል።

    ደብረ ብርሃን (ሰሞነኛ)– በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ‹‹ቱሪዝም ለአካባቢ እንክብካቤና ለማኅበረሰብ አቅም መጎልበት›› በሚል መሪ ቃል ሲከበር የቆየው የቱሪዝም ሳምንት ጥር 24/2011 ዓ/ም የቁንጅና ውድድር በማካሄድ ተጠናቀቀ።

    በውድድሩም ወ/ሪት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ያብፀጋ አይነኩሉ ከሁለተኛ ዓመት የሎጅስቲክና ሰፕላይ ቼን ማኔጅመንት (Logistics and Supply Chain Management) ትምህርት ክፍል ተመርጣለች። በሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ኤልሳቤጥ ደስታ የ3ኛ ዓመት የባዮቴክኖሎጂ (Biotechnology) እና በሦስተኛነት ደረጃ ተማሪ ትንሳኤ ፀጋዬ አንደኛ ዓመት የሳይኮሎጂ (Psychology) ትምህርት ክፍል እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።

    VIDEO: The Yellow Movement AAU: Speaking up for women and girls – empowering women (Ethiopia)

    የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዘዳንት ተወካይ ዶ/ር ጌትነት አሸናፊ በፕሮግራሙ መዝጊያ ላይ ተገኝተው እንደገለጹት የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ከሳምንት በፊት ጀምሮ በዩኒቨርስቲው ግቢና ውጪ ያለውን አካባቢ በማጽዳት ለሌሎች ምሳሌ የሚሆኑ ተግባራት በማከናወን የቆዩ መሆናቸውን በመግለፅ ላደረጉት በጎ ተግባር ምስጋና አቅርበዋል።

    የቱሪዝም ማኔጅመንት የትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ አብርሃም ኪዳኔ እንደገለፁት የዘንድሮው ውድድር ለ2ኛ ጊዜ የተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው፥ በባለፈው ዓመት የተመረጠችው ወ/ሪት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በአማራ ክልል በተካሄደው የቁንጅና ውድድር ላይ ተሳትፋ 3ኛ ደረጃ በመውጣቷ በርካታ ሽልማቶችን ያገኘች መሆኗን ተናግረዋል።

    በመጨረሻም ለጓሳ ማኅበረሰብ ጥብቅ ስፍራ መታሰቢያነት ‹‹ቱሪዝም ለአካባቢ እንክብካቤና ለማህበረሰብ አቅም መጎልበት›› በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የቱሪዝም ሳምንት 8 /ስምንት/ ተወዳዳሪዎችን ያሳተፈው የቁንጅና ውድድር ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ የወጡትን አሸናፊዎችን በመምረጥና እውቅና በመስጠት በዓሉ ተጠናቋል።

    ምንጭ፦ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በ2006 ዓ.ም. በሰባት የየመገናኛ ብዙሃን (ሚዲያ) እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የተቋቋመው ጉዞ ዓድዋ፥ አንድ ሺሕ አስር ኪሎሜትሮችን የሚሸፍን፣ ከኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ተነስቶ መዳረሻውን የዓድዋ ድል አምባ ተራሮች ጫፍ ላይ የሚያደርግ ረዥም የእግር ጉዞ ነው። ላለፉት ስድስት ዓመታት ከጥር ወር ጀምሮ የዓድዋ ድል በዓል እስከ ሚከበርበት የካቲት 23 ቀን ድረስ ከስድስት ሳምንታት ላላነሰ በየዓመቱ ሳይቋረጥ የቆየው ጉዞ ዓድዋ፥ ዘንድሮ የኢትዮጵያዊነቱ ስሜት እጅግ ጎልቶ በጉዞው ላይ የሚሳተፉት ቁጥርም ጨምሯል። በዘንድሮው ጊዞ ዓድዋ 44 ተጋዦች ከአዲስ አበባ እና 4 ተጓዦች ከሐረር በአጠቃላይ 48 ተጓዦች ጥር 7 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀን ከአዲስ አበባ ተነስተዋል።

    የመላው አፍሪቃውያን ድል እስከመባል የደረሰው ታላቁ የዓድዋ ድል፥ የግዝፈቱን ያህል ክብር እና መታወሻ ሥነሥርዐት ሳይኖረው እየተከታተለ ከመጣው ትውልድ ጋር የበዓሉ አከባበር ዐውድ እየወረደ ጭራሽ እየተዘነጋ እና እየደበዘዘ መሔድ ያሳሰባቸው የጉዞ ዓድዋ መሥራቾች ትውልዱ ትኩረት ሰጥቶ የድሉን መንፈስ እንዲጋራ ለማድረግ ይህንን የጉዞ ሐሳብ አመንጭተዋል።

    ◌ የጉዞ ዓድዋ ተጓዦችና የኢትዮጵያዊያን አስተያየት

    በዚህም የተነሣ ጉዞ ዓድዋ ባለፉት ስድስት ዓመታት ብቻ ከታለመው ዓላማ አንጻር ከፍተኛ የሆነ አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ የዓድዋ ድል በዓል ቀድሞ ከነበረበት አከባበር የላቀ ተሳትፎ ያለው የድል በዓል እንዲሆን አስተዋጽዖ ለማድረግ ተችሏል።

    ጉዞውን ከማካሔድ በተጓዳኝ በየመንገዱ ተንቀሳቃሽ የመጻሕፍት ንባብ መሰናዶ በማካሔድ በየዓመቱ የሚጓዙ አባላትን በዓድዋ ጦርነት እና ድል ዙሪያ በቂ የሆነ ግንዛቤ እና ዕውቀት የማጋራት ዝግጅቶችን ሲያካሂድ ቆይቷል። ከአንድ ወር በላይ በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ሰፊ ሽፋን የሚሰጠው የጉዞው የዕለት ተእለት ውሎ፣ በዓሉ ከመድረሱ አስቀድሞ በበርካታው ሕዝባችን ላይ የካቲት 23 ዕለትን በጉጉት የመጠበቅ ስሜት እንዲፈጠር አድርጓል።

    ◌ የዓድዋ ድል በዓል በጎሰኞች ዓይን የዲያቆን ዳንኤል ክብረት መጣጥፍ

    ከዚህ ቀደም የድል በዓሉ በብቸኝነት ከሚከበርባቸው የአዲስ አበባ እና የዓድዋ ከተሞች በተጨማሪ ከ28 በላይየሚሆኑ የክልል ከተሞች እና በርካታ ሕዝብ የሚኖርባቸው የገጠር ወረዳዎች ተጓዥ ቡድኑ በየደረሰበት በሚኖሩ ደማቅ አቀባበሎች ላይ በሚሰጡ የግንዛቤ መስጫ መልዕክቶች ስለ ዓድዋ ድል ታሪክ ግንዛቤ በመሰጠቱ የበዓሉአከባበር ከፍተኛ ለውጥ በማምጣት ላይ ይገኛል። የጉዞ ዓድዋ ትሩፋቶች፦

    • በዓድዋ ከተማ ውስጥ በአምስት ዓመት አንድ ጊዜ ብቻ የነበረው የዓድዋ ድል በዓል አከባበር ሥነ ሥርዐትበየዓመቱ እንዲካሔድ አስችሏል።
    • የበዓሉ አከባበር በፌደራል መንግሥት ደረጃ እንዲከበር ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጓል።
    • ከ120 ዓመታት በፊት መቀሌ ከተማ በሚገኘው የእንዳየሱስን ምሽግ ለማስለቀቅ ከጣሊያን ጦር ጋር ሲዋጉ ሕይወታቸው ያለፉ ጀግና ኢትዮጵያውያን አጽም የትም ተበታትኖ በመቅረቱ፥ ጉዞ ዓድዋ በአሁኑ ሰዓት የቦታው አስተዳዳሪ የሆነውን የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ በማንቃት፤ የካቲት 26 ቀን 2008 ዓ. ም አጽማቸውን አሰባስቦ በክብር እንዲያርፍ ተደርጓል። ከዚህም ባሻገር በዓመቱ የካቲት 26 ቀን 2009 ዓ.ም በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ወጪ “የጀግኖች ኢትዮጵያዊያን መታሰቢያ ሙዚየም” የተሰኘ ጣራ አልባ ቤተ መዘክር በእንዳየሱስ ታሪካዊ ምሽግ ላይ ተገንብቶ ለመመረቅ በቅቷል።
    • የዓድዋ ጦርነት መንስዔ የሆነው የዉጫሌ ውል የተፈረመበት “ይስማ ንጉሥ” የተባለው ታሪካዊ ቦታ ተከልሎ ጥበቃ እንዲደረግለት በማድረግ ጉዞ ዓድዋ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል። ከዚህም በተጨማሪ ውሉ በተፈረመበት ዕለት ሚያዝያ 25 ቀን በየዓመቱ፤ ምሁራዊ ተዋስዖ የሚደረግባቸው መድረኮች በመፍጠር፣ ላለፉት ስድስት ዓመታት ባበረከተው የላቀ አስተጽዖ የአምባሰል ወረዳ የዓድዋ ድልን ለመዘከርና ቦታውን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ያለመቋሚ ቤተ መዘክር በቦታው ላይ እንዲገነባ የሚያስችል የ19 ሚልዮን ብር የበጀት ድጋፍ ከአማራ ክልል መንግሥት እንዲያገኝ ጉዞ ዓድዋ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል።
    • ለበርካታ ዓመታት አገልግሎቱ ተዘግቶ የቆየው በዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ የትውልድ መንደር “አንጎለላ” የሚገኘው የዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ መታሰቢያ ክሊኒክ እንዲከፈት ከፍተኛ ቅስቀሳ በማድረግ፤ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ድጋፍ ክሊኒኩ ታዳጊ የጤና ጣቢያ ሆኖ በድጋሚ አገልግሎት እንዲሰጥ ጉዞ ዓድዋ አስተዋጽዖ ካደረጉ መካከል ግንባር ቀደሙን ሚና ተጫውቷል።
    • የዓድዋ ጀግና የሆኑት ራስ አሉላ አባ ነጋ የቀብር ቦታ በሆነው የአባ ገሪማ ገዳም ውስጥ ለሁለቱም ጾታዎች ጉብኝት ምቹ በሆነ ቦታ ላይ ሐውልት እንዲቆምላቸው ጉዞ ዓድዋ ባመቻቸው ዕድል በአንድ ባለ ሀብት ሐውልታቸው ተሠርቶ ለምረቃ በቅቷል።
    • በየዓመቱ በሚካሔዱ ጉዞዎች ከዓድዋ ድል ጋር ግንኙነት ያላቸው ቦታዋችን እና ልዩ ታሪካዊ መረጃዎችን በምስል እና በጽሑፍ በመሰብሰብ ለጥናትና ምርምር አስተዋጽዖ ማበርከት የሚችሉ የታሪክ ግብዓቶችን በማደራጀት በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በተለይም የማኅበራዊ ድረ ገጽን በመጠቀም ቅርሶችን የማስተዋወቅና የመጠበቅ ሥራዎችንበ መሥራት ላይ ይገኛል።

    የጉዞ ዓድዋ ማኅበር የዓድዋ ድል በዓል በኢትዮጵያውያን እንዲሁም በጥቁር አፍሪካውያን ዘንድ የሚገባውን ክብር እንዲያገኝ ላደረገው ጥረት፣ ከላይ ለተጠቀሱት እና በየዓመቱ በሚያደርጋቸው እጅግ አመርቂ ክንዋኔዎች ምክንያት በ2009 ዓም በቅርስና ባሕል ዘርፍ የዓመቱ በጎ ሰው ተሸላሚ ሆኗል።

    ላይ የሚሳተፉ ተጓዦች በጉዞአቸው ላይ የሚያደርጓቸውን የተለያዩ ክንዋኔዎችና የሚዘግቧቸውን ታሪክ ተኮር ዘገባዎች ለመከታተል የማኅበሩን የፌስቦክ ገጽ ይጎብኙ።

    ◌ ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ በደብረ ብርሃን ከተማ ሃውልት ሊቆምላቸው ነው

    ምንጭ፦ በጎ ሰው ሽልማት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ጉዞ ዓድዋ


    Semonegna
    Keymaster

    የከተማዋን የቱሪዝም ዕድገት ከፍ ለማድረግ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ምኒልክ ሃውልቶችን የከተማ አስተዳደሩ ኅብረተሰቡን በማሳተፍ ያስገነባል። ስለሆነም የሁለቱ ታላላቅ መሪዎች ሃውልት በከተማዋ እንዲቆም እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ከ6 መቶ ዓመታት በላይ ባስቆጠረችው የድሮዋ ደብረ ኤባ የዛሬዋ ደብረ ብርሃን ከተማ ለዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሃውልት ሊቆምላቸው እንቅስቃሴ መጀመሩን ከተማ አስተዳደሩ አስታውቋል።

    የከተማዋ ምክትል ከንቲባ እና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ብርሃን ገብረሕይወት ጥር 9 ቀን 2011 ዓ.ም. አዲስ አበባ ላይ በሰጡት መግለጫ ደብረ ብርሃን ከተማን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የከተማ አስተዳደሩ እየሠራ ነው፤ ከተማዋን የኮንፈረንስ ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግም ከተማ አስተዳደሩ ባዛሮችን በተለያዩ ጊዚያት እንደሚያካሂድ ተገልጿል።

    የከተማዋን የቱሪዝም ዕድገት ከፍ ለማድረግ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ምኒልክ ሃውልቶችን የከተማ አስተዳደሩ ኅብረተሰቡን በማሳተፍ ያስገነባል። ስለሆነም የሁለቱ ታላላቅ መሪዎች ሃውልት በከተማዋ እንዲቆም እንቅስቃሴ እየተደረገ ነውም ተብሏል።

    ደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ በከተማዋ ለሚኖሩ ዜጎች የተለያዩ የሥራ ዕድሎችን ፈጥሯል

    ከተማ አስተዳደሩ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እየሠራ እንደሆነም አስታውቋል። ደብረ ብርሃን ከተማ በዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ መመሥረቷ ይታወቃል።

    አጼ ዘርአ ያዕቆብ

    አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስትክብረ እግዚ እ.ኤ.አ. በ1399 ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮው ፈታጃር ክፍለ ሀገር ተወለዱ። የነገሡበትም ዘመን እ.ኤ.አ. ከ 1434 እስከ 1468 (እስከሞቱበት ጊዜ) ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው።

    ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ

    ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ከአባታችው ከሸዋው ንጉሥ ኃይለ መለኮት ሣህለ ሥላሴና ከእናታቸው ወይዘሮ እጅጋየሁ ለማ አድያም እ.ኤ.አ. ነሐሴ 17 ቀን 1844 ደብረ ብርሃን አካባቢ አንጎለላ ከሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ በአንጎለላ መቅደላ ኪዳነ ምኅረት ቤተ ክርስቲያን ክርስትና ተነሱ። የነገሡበትም ዘመን እ.ኤ.አ. ከ 1889 እስከ 1913 (እስከሞቱበት ጊዜ) ነበር። ያረፉትም ተዓካ ነገሥት ለማርያም ወደብረ መንክራት ስዕል ቤት ኪዳነ ምኅረት ገዳም (አዲስ አበባ) ነው።

    ምንጭ፦ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሃውልት


    Semonegna
    Keymaster

    ጅማ ዩኒቨርሲቲ ባስገነባው የህክምና ማዕከል ምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ ለዓመታት ያስተማራቸውን 331 የህክምና ዕጩ ምሩቃን እና በተለያዩ መስኮች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 2ሺህ የድህረ ምረቃ መርሀ ግብር ተማሪዎችን ያስመርቃል።

    ጅማ (ሰሞነኛ)– ጅማ ዩኒቨርሲቲ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የፌድራልና የክልል መንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የህክምና ማዕከሉን ኅዳር 29 ቀን 2011 ዓም እንደሚያስመርቅ ተዘግቧል።

    የህክምና ማዕከሉ 800 (ስምንት መቶ) አልጋዎች ያሉት ሲሆን፥ በደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍል ከ20 ሚሊየን በላይ ሰዎች የህክምና አገልግፍሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው ተብሏል። ማዕከሉ እንደ ደቡብ ሱዳን ላሉ ጎረቤት ሀገራትም አገልግሎት ለመስጠት ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ መሆኑን ተነግሯል።

    ዩንቨርሲቲው ያስገነባው ይህ የህክምና ማዕከል በህክምና እና ጤናው ዘርፍ የምርምር፣ የማስተማሪያ፣ እንዲሁም የማኅበረሰብ አገልግሎቶችን ለመስጠት የሚያስችል መሆኑም ነው የተገለጸው። በዚህም ጅማ ዩኒቨርሲቲ በሀገሪቱ ከሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ሲነጻጸር ልቆ የሚታይበትን የማኅበረሰብ ተኮር (community-based) ትምህርትና ምርምር ይበልጥ ያገለብትለታል ተብሎ ይታመናል።

    Ethio-American Doctors Group (EADG): Building a regional healthcare system & medical tourism

    ዩንቨርሲቲው በህክምና ማዕከሉ የምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ ለዓመታት ያስተማራቸውን 331 የህክምና ዕጩ ምሩቃን እና በተለያዩ መስኮች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 2ሺህ የድህረ ምረቃ መርሀ ግብር ተማሪዎችን እንደሚያስመርቅም ታውቋል።

    በተመሳሳይ መልኩ ዩንቨርሲቲው ያስገነባው 40 ሺህ ያህል ተመልካቾችን ማስተናገድ የሚችለው ስታዲየም፣ ሲቭክ አዳራሽ፣ መንገዶችና ሌሎች የመሠረተ ልማት ሥራዎች ይመረቃሉ ተብሏል። የሲቪክ አደራሹ በርካታ ተሰብሳቢዎችን በአንዴ የሚያስተናግድና የተለያዩ ኮንፈረንሶችን በተመሳሳይ ጊዜ ለማካሄድ የሚያስችሉ የተለያዩ ክፍሎች እንዳሉትም ተነግሯል። ከዚህ ጋር ተያይዞ እንደተዘገበው ይህ የሲቭክ አዳራሽ ከተማዋን የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ ስለመሆኑም ነው የተገለጸው።

    ምንጭ፦ ኢቢሲ / ኤፍ.ቢ.ሲ. / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ጅማ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ማዕከል


    Semonegna
    Keymaster

    ደብረ ብርሃን (ኢዜአ)–በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በአንጎለላና ጠራ ወረዳ ሀሰተኛ ሰነድ በመጠቀም ከመንግሥት ካዝና ከ466 ሺህ ብር በላይ ለግል ጥቅሟ ያዋለችው ግለሰብ በ18 ዓመት ጽኑ እስራትና የገንዘብ ቅጣት ተጣለባት።

    በሰሜን ሸዋ ዞን ፍርድ ቤት የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ወ/ሪት ዘርትሁን ያዘው ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንደገለጹት ፍርድ ቤቱ በግለሰቧ ላይ ቅጣቱን የወሰነው በወረዳው ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ጽህፈት ቤት ገንዘብ ያዥ ሆና ስትሠራ የመንግሥትን ገንዘብ ለግል ጥቅሟ ማዋሏ በመረጋገጡ ነው።

    ተከሳሿ ወ/ሮ አበበች ጽጌ ከ2007 እስከ 2009 ዓ.ም ድረስ በጽህፈት ቤቱ ስትሠራ ሀሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀትና መንግሥታዊ ሰነድ በመደበቅ የሙስና ወንጀል መፈፀሟ በሰውና በሰነድ ማስረጃ እንደተረጋገጠባትም አስረድተዋል።

    ግለሰቧ በአገር አቀፍ ደረጃ በውሃና በአካባቢ ንጽህና ፕሮጀክት (WASH) ግዢ ከአቅራቢዎች ላይ የተሰበሰበ ሁለት በመቶ ገንዘብ 171 ሺህ 417ብር ለግል ጥቅም ማዋሏ ተረጋግጦባታል ነው የተባለው።

    እንዲሁም በ56 ደረሰኞች ላይ በበራሪው ትክክለኛዉን የገንዘብ መጠን በመመዝገብና የከፋዮችን ስም በመቀያየር የገቢ መጠኑን በመቀነስ ለመንግሥት መግባት የነበረበት 94 ሺህ 90 ብር ሰነድ በማበላለጥ መጠቀሟም ነው የተገለፀው። በተጨማሪም በራሪ ደረሰኞችን ለከፋይ በትክክል ቆርጣ ከሰጠች በኋላ በሁለተኛና ሦስተኛ ካርኒዎች ላይ አቀናንሳ 181ሺህ 16 ብር ለግል ጥቅሟ ማዋሏን መረጋገጡን ባለሙያዋ ገልጸዋል።

    ግለሰቧ ወንጀሉን ከፈጸሟ በኋላ ከአካባቢው በመሰወሯ ፖሊስ ወንጀለኛዋን አድኖ በመያዝ ለማረሚያ ቤት እንዲያስረክብም ትዕዛዝ ተሰጥቷል። ከዚህ በተጨማሪ ለአምስት ዓመታት ከማንኛውም የእንቅስቃሴ መብቷ እንደታገደችም ተወስኖባታል።

    በሌላ ዜና፥ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለረጅም ጊዜ ታጥረው በቆዩ ቦታዎች ንብረታቸውን በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ባላነሱት ላይ እርምጃ መውሰድ ተጀመረ።

    የከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማት ማኔጅመንት ፅህፈት ቤት የደንብ ማስከበር ፅህፈት ቤት ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በጋራ በመሆን እርምጃ መውሰድ መጀመሩን አስታውቋል።

    በዚህም ያለ ልማት ለረጅም ጊዜ ታጥረው የቆዩ ቦታዎች ላይ የሚገኙ የአጥር ቆርቆሮዎችን ማንሳት መጀመሩን ገልጿል።

    አስተዳደሩ ባልለሙ ቦታዎች ላይ ንብረቶቻቸውን ያስቀመጡ አካላት ንብረታቸውን እንዲያነሱ ከሳምንት በፊት መግለጫ መስጠቱ የሚታወስ ነው። ይሁን እንጅ እነዚህ አካላት ንብረቶቻቸውን ማንሳት ባለመጀመራቸው ምክንያት አስተዳደሩ በዛሬው ዕለት ወደ እርምጃ መግባቱን ነው የገለጸው።

    አስተዳደሩ የሕዝብን ሃብት ለተገቢው ልማትና ለነዋሪዎች ተጠቃሚነት እንዲውል በጀመረው ተግባር ህገ ወጥነትን እንደማይታገስና፥ ህግ የማስከበር ሃላፊነቱን እንደሚወጣ መግለጹን ከከተማዋ ከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

    ምንጮች፦ ኢዜአ እና ኤፍቢሲ

    ለግል ጥቅሟ

    Semonegna
    Keymaster

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ድረስ በ14 የትምህርት ክፍሎችን በመክፈት ተማሪዎችን እያስተማረ መሆኑንና የኒቨርሲቲው የትምህርት ክፍሎቹን ወደ 41 ለማሳደግ ዕቅድ ይዞ እየሠራ መሆኑንም የኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ተናግረዋል።

    ጂንካ፣ ደቡብ ኦሞ ዞን (ዋልታ) – ጂንካ ዩኒቨርሲቲ በ2011 ዓ.ም የትምህርት ዘመን 1ሺ 500 አዳዲስ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።

    የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ፕሮፌሰር ገብሬ ይንቲሶ ለዋልታ እንደገለጹት በዘንድሮ የበጀት ዓመት እና የትምህርት ዘመን የተማሪዎችን ቅበላ የተሳካ ለማድረግ በሁለት ዘርፍ የተከፈሉ ዝግጅቶች እየተካሄዱ ይገኛሉ።

    የኒቨርሲቲው የዘንድሮ ዓመትን የመማርና ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር የመምህራን ዝግጅትን ጨምሮ የተማሪዎች የአገልግሎት መስጪያ ተቋማት የሆኑት ቤተ መጽሐፍትና የመመዝገቢያ ሥፍራዎች በቴክኖሎጂ የታገዙ እንዲሆኑ የማስቻል ሥራዎች ተከናውነዋል ብለዋል ፕሬዚደንቱ።

    በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች አገልግሎት መስጪያ ህንጻዎች ግንባታ መዘግየታቸውን የገለጹት ፕሮፌሰር ገብሬ አዳዲስ ተማሪዎችን በጊዚያዊ የመጠሊያ ህንጻዎች እንዲገቡ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የዘንድሮ ዓመት የተማሪዎች የመግቢያ ቀንም እስካሁን አለመቆረጡን ፕሬዚደንቱ አያይዘው ገልጸዋል።

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ድረስ በ14 የትምህርት ክፍሎችን በመክፈት ተማሪዎችን እያስተማረ መሆኑንና የኒቨርሲቲው የትምህርት ክፍሎቹን ወደ 41 ለማሳደግ ዕቅድ ይዞ እየሠራ መሆኑንም ፕሬዚደንቱ አብራርተዋል።

    አዳዲስ የሚከፈቱት የትምህርት ዘርፎችም በደቡብ ኦሞ ዞን የሚታዩ የሙያ ክፍተቶችን ለመሙላት በሚያስችል መልኩ የሚከፈቱ መሆኑም ተገልጿል።

    የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ባለፈው ዓመት 1ሺህ 100 ያህል ተማሪዎችን የተቀበለ ሲሆን በዘንድሮ ዓመት 1ሺ500 አዳዲስ ተማሪዎችን በመቀበል በአጠቃላይ ተማሪዎችን 2ሺህ 600 ለማድረስ እየሠራ ይገኛል።

    በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል (ደብብሕክ)፣ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና ከተማ በሆነችው ጂንካ የሚገኘው ጂንካ ዩኒቨርሲቲ በ2010 ዓ.ም. በትምህርት ሚኒስቴር ስር ከተከፈቱት 11 አዳዲስ የሕዝብ ዩኒቨርሲቲዎች (public universities) አንዱ ነው።

    ምንጭ፦ ዋልታ

    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ

     

    Semonegna
    Keymaster

    ዩኒቨርሲቲው ለሠራተኞቹ ያስተላለፋቸው መኖርያ ቤቶች ስቱዲዮ፣ ባለ አንድ መኝታ፣ ባለ ሁለት መኝታ እና ባለ ሦስት መኝታ ሲሆኑ ሠራተኞቹ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በሠራተኝነት እስካሉ ድረስ ቤቶቹን በነጻ ይገለገሉባቸዋል።

    ነቀምቴ (ኢዜአ) – ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ከ37 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባቸውን መኖርያ ቤቶች ለሠራተኞቹ አስረከበ።

    የዩኒቨርሲቲው የመሠረተ ልማትና የሕንፃ ግንባታ ዳይሬክተር ዶክተር ደረጄ አደባ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው የመኖርያ ቤት ለሌላቸው ሠራተኞቹ የቤት ባለቤት ለማድረግ ያስገነባቸውን 134 መኖሪያ ቤቶች ትናንት አስረክቧል። ለመኖሪያ ቤቶቹ ከ37 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጉንም ገልጸዋል።

    ከዚህ በተጨማሪ በ1999 ዓ.ም በከተማ አስተዳደሩ የተጀመሩና በገንዘብ እጥረት ምክንያት ግንባታቸው የተቋረጡ 10 ሕንፃዎችን በመግዛት ሠራተኞቹን ተጠቃሚ ለማድረግ እየሠራ መሆኑን፥ ሕንጻዎቹ ሲጠናቀቁ 150 የሚሆኑ የተቋሙን ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለማድረግ የሚያስችሉ መሆናቸውንም ዶክተር ደረጄ አክለው ገልጸዋል።

    ዶክተር ደረጄ እንዳሉት መኖርያ ቤቶቹ ስቱዲዮ፣ ባለ አንድ መኝታ፣ ባለ ሁለት መኝታ እና ባለ ሦስት መኝታ ሲሆኑ ሠራተኞቹ በተቋሙ እስካሉ ድረስ ቤቶቹን በነጻ ይገለገሉባቸዋል።

    ከዩኒቨርሲቲው ሠራተኞቹ መካከል መምህር ተስፋዬ ፍቃዱ በሰጡት አስተያየት ተቋሙ በግል የኪራይ ቤት ሲንከራተቱ ይገጥማቸው ከነበረው ችግር እንደተፈታላቸው ተናግረዋል። በግል ተከራይቶ መኖር ብዙ አስቸጋሪ ሁኔታዎች እንዳሉት ገልጸው በአከራዩና በተከራይ መካከል ቅሬታ በተፈጠረ ቁጥር ይደርስባቸው በነበረው መጉላላት ይማረሩ እንደነበር ገልጸዋል።

    መምህር እሱባለሁ ዳባ በበኩላቸው የግል ቤት በተከራዩበት ወቅት ከውሃና መብራት ክፍያ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ጭቅጭቅና ግጭት ውስጥ ይገቡ እንደነበር አስታውሰዋል።

    በተመሳሳይ፦ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ እና ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛና በሶስተኛ ዲግሪዎች በርካታ መርሀ ግብሮችን ከፈቱ

    በአሁኑ ወቅት በዩኒቨርሲቲው በኩል የመኖሪያ ቤት ችግራቸው መፈታቱ የትምህርትና የምርምር ሥራቸውን ተረጋግተው ለማከናወን እንደሚያስችላቸው ጠቁመው በተቋሙ በኩል ለተደረገላቸው የመኖርያ ቤት ስጦታ መስጋናቸውን አቅርበዋል።

    መኖርያ ቤት ማግኘታቸው ከዚህ ቀደም ለግለሰብ ይከፍሉት የነበረውን የቤት ኪራይ ወጪ ከመቀነሱ ባለፈ ከሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር በማኅበራዊ ጉዳዮች እንዲተሳሰሩ የሚያደርግ መሆኑን የገለጹት ደግሞ መምህር ኤልያስ ቱጁባ ናቸው። መምህሩ እንዳሉት ሠራተኞች አንድ አካባቢ መሆናቸው ለትራንስፖርት አገልግሎትና ለኢንቴርኔት አገልግሎት ምቹ ሁነታ ከመፍጠር አኳያ ጠቀሜታው የጎላ ነው።

    ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ከዚህን ቀደም ከ19 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመኖርያ ቤት ሕንፃ በማስገንባት ከ60 በላይ ለሚሆኑ ሠራተኞቹ ማሰረከቡ የተቋሙን መረጃ ያሳያል።

    በየካቲት ወር 1999 ዓ.ም የተቋቋመው ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በአሁኑ ወቅት 82 በመጀመሪያ (bachelors)፣ በሁለተኛ (masters) እና በዶክትሬት ዲግሪዎች ተማሪዎችን እንደሚያስተምር የዩኒቨርሲቲው ድረ ገጽ ያስረዳል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    ወለጋ ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    እንደ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ገለጻ፥ እስካሁን ባለው ተሞክሮ የአንድ ፓርክ ግንባታ ከዘጠኝ ወር እስከ አንድ ዓመት ይጠናቀቃል፤ በዚህ መሠረት  አሁን በግንባታ ላይ ያሉት የኢንዱስትሪ ፓርኮች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ይጠናቀቃሉ።

    አዲስ አበባ – እስከ አሁን ወደ ምርት የገቡትን አራቱን የኢንዱስትሪ ፓርኮችና በቅርቡ የተመረቀውን የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ጨምሮ በ2012 ዓ.ም ማጠናቀቂያ 15 የኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ማምረት እንደሚገቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ።

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኦፕሬሽንና ማኔጅመንት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ሰለሞን በተለይ እንደተናገሩት፤ እስካሁን የሀዋሳ፣ የቦሌ ለሚ ቁጥር አንድ አይሲቲ፣ የመቐለ እና ኮምቦልቻ ፓርኮች ግንባታቸው ተጠናቆ ወደ ሥራ ገብተዋል። ከቀናት በፊት የተመረቀውን የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ጨምሮ የጅማና የደብረ ብርሃን በሁለት ወራት ውስጥ ወደ ሥራ ይገባሉ።

    የቦሌ ለሚ ቁጥር ሁለት፣ የባህር ዳር፣ የድሬዳዋና የቂሊንጦ ፋርማስቲዩካል ፓርኮች በተያዘው በጀት ዓመት የሚጠናቀቁ መሆናቸውን ገልፀው ከዚህ በተጨማሪ የአይሻ፣ የአረርቲ የአሶሳና ሠመራ ፓርኮች በዚሁ ዓመት ግንባታቸውን ለመጀመር የአዋጭነት ጥናቶቻቸው ተጠናቆ ወደ ስምምነት እየተገባ መሆኑን ተናግረዋል። እስካሁን ባለው ተሞክሮ የአንድ ፓርክ ግንባታ ከዘጠኝ ወር እስከ አንድ ዓመት ይጠናቀቃል ያሉት ኃላፊው ሌሎቹም በዚሁ መሠረት በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ይጠናቀቃሉ ብለዋል።

    ተያያዥ ዜና፦ ቬሎሲቲ አፓረልዝ ኩባንያ ኢትዮጵያ ውስጥ የመጀመርያ የሆነውን የግል የኢንዱስትሪ ፓርክ ሊገነባ ነው።

    ፓርኮቹ የተለያዩ ምርቶችን የሚያመርቱ ቢሆንም በዋናነት መንግሥት በኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ ባስቀመጠው መሠረት በአልባሳትና ጨርቃ ጨርቅ፣ በህክምና መገልገያዎችና የኮንስትራክሽን ግብዓቶች ላይ የሚያተኩሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል። እነዚህ ዘርፎች በአነስተኛ ካፒታል የሚንቀሳቀሱ ሲሆን ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚያስችሉም ናቸው። በተጨማሪም ፓርኮቹ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችን ከማበረታታት ባሻገር የውጭ ባለሀብቶችን በስፋት ለመሳብ የሚያስችሉ እንደሚሆኑም ጠቁመዋል።

    እንደ አቶ ሽፈራው ገለፃ፤ ፋብሪካዎቹ በሙሉ አቅማቸው ወደ ሥራ ሲገቡ በውጭ ምንዛሬ የሚገቡትን ምርቶች የሚተኩና ለውጭ ገበያ በማቅረብ የውጭ ምንዛሬ የሚያሳድጉ ይሆናሉ። በዚህ ረገድ የቂሊንጦ ኢንዱስትሪያል ፓርክ በመድኃኒት ምርት፣ የድሬዳዋና የአዳማ ደግሞ በኮንስትራክሽን ማቴርያልና ከውጭ የሚገቡ ኬሚካሎችን በአገር ውስጥ ለመተካት የተያዙ ሲሆን፤ በአልባሳትና ጨርቃ ጨርቅ ዘርፍ የሚሰማሩት የወጪ ንግድ ላይ የሚያተኩሩ እንደሆኑም ገልፀዋል።

    በ2006 ዓ.ም. የተቋቋመው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን (IDPC) ሀገሪቱ ውስጥ በመንግስት ውጪ የሚገነቡትናና ወደ ሥራ የገቡትን የኢንዱስትሪ ፓርኮች በበላይነት ይቆጣጠራል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬሥ ድርጅት

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች

    Semonegna
    Keymaster

    ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ፣ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በዶክትሬት ዲግሪ አዳዲስ የትምህርት መርሀ ግብሮችን ከፍተው ተማሪዎችን ይቀበላሉ።

    ደብረ ብርሃን/ባህር ዳር – ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በዘንድሮ (2011 ዓ.ም) የትምህርት ዘመን በመጀመሪያ ዲግሪ (bachelor degree) አራት በሁለተኛ ዲግሪ (master degree) አስራ ሁለት መርሃ ግብሮችን እንደሚከፍት አስታወቀ።

    የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ፕሮግራም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶክተር ጌትነት አሸናፊ ለኮሙኒኬሽን ጉዳዮች እንደገለጹት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በዘንድሮው የትምህርት ዘመን አስራ ስድስት አዳዲስ የትምህርት መርሀ ግብሮችን ይከፍታል።

    ዶክተር ጌትነት አሸናፊ እንዳሉት የትምህርት ክፍሎቹ ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያና ሁለተኛ ድግሪ ዲግሪ የሚሰጣቸውን የትምህርት መርሀ ግብሮች የመጀመሪያ ድግሪ ከ49 ወደ 53 እንዲሁም 34 የነበረውን የሁለተኛ ዲግሪ የትምህርት መርሀ ግብር ወደ 46 ከፍ ያደርገዋል ብለዋል።

    ከተመሠረተ 11 ዓመት የሞላው ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በአሁኑ ሰዓት ከ12 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በተለያዩ መስኮች እያስተማረ ይገኛል።

    በተመሳሳይ ዜና ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2011 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በመጀመሪያ፣ በበሁለተኛ እና በዶክትሬት (doctorate) ዲግሪ በሚከፍታቸው 18 አዳዲስ የትምህርት መስኮች ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ። ዩኒቨርሲቲው በዚህ ዓመት ከ8 ሺህ 700 በላይ አዲስ ተማሪዎችን ለመቀበልም አስፈላጊው ዝግጅት ማድረጉም ተጠቁሟል።

    የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር እሰይ ከበደ ዛሬ ለኢዜአ እንዳስታወቁት ተቋሙ በአዲሱ የትምህርት ዘመን ከወቅቱ ጋር የሚሄዱ አዳዲስ የትምህርት መስኮችን በመክፈት አገራዊ እድገቱን በእውቀት ለማገዝ እየሠራ ነው።

    በተያዘው የትምህርት ዘመንም ሁለት የመጀመሪያ ዲግሪ፣ 12 የሁለተኛ ዲግሪና አራት የዶክትሬት ዲግሪ የትምህርት መስኮችን ከፍቶ 250 ተማሪዎችን ለመቀበል የሚያስችል ዝግጅት ማድረጉን ገልጸዋል።

    ዶክተር እሰይ እንዳሉት ህግ፣ መሬት አስተዳደር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ ጨርቃጨርቅ፣ ትምህርት፣ ፖለቲካል ሳይንስና የመሳሰሉት የትምህርት መስኮች አዲስ የሚከፈቱባቸው ናቸው። “የተሳካ የመማር ማስተማር ተግባር ለማካሄድም ቀደም ብሎ የሥርአተ ትምህርት ቀረጻ መደረጉንና የመምህራን ቅጥርም ሆነ ሌሎች አስፈላጊ ዝግጅቶች ተጠናቀዋል” ብለዋል።

    የኒቨርሲቲው በአፋን ኦሮሞ ትምህርትም በዚህ ዓመት አጋማሽ መደበኛ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር የሥርአተ ትምህርት ቀረጻ ሥራ ማካሄዱንና የመምህራን ቅጥር እየፈጸመ መሆኑን ዶክተር እሰይ አስታውቀዋል።

    ተቋሙ በህክምናው ዘርፍ የተሻለ እውቅት ያላቸው ባለሙያዎችን ለማፍራት በትኩረት እየሠራ መሆኑን ጠቁመው፣ “የተሻለ የማስተማርም ሆነ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት አዲስ የማስተማሪያ ሆስፒታል ገንብቶ የ170 መምህራንን በመቅጠር ላይ ነው” ብለዋል።

    ዩኒቨርሲቲው በመደባኛው የትምህርት መርሀግብር ብቻ ከመጀመሪያ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ከ8 ሺህ 700 በላይ አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ እንደሚያስተምርም ምክትል ፕሬዚዳንቱ አያይዘው ገልጸዋል።

    በተለይም እንደ ሀገርም ሆነ እንደ ዩኒቨርሲቲ እየወረደ የመጣውን የትምህርት ጥራት ለማስጠበቅ የተሻለ አቅም ያላቸውን መምህራን በመመደብ፣ ቤተ ሙከራዎችንና ቤተ መጻህፍትን በማደረጀት ጥራትን ለማምጣት እየሠራ መሆኑንም ገልፀዋል። ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ቆይታቸውን አጠናቀው ከመውጣታቸው በፊትም አጠቃላይ የጥራት መለኪያ ፈተና እንዲወስዱም እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል።

    ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በመደበኛውና መደበኛ ባልሆኑ የትምህርት መርሃ ግብሮች ዓመታዊ የተማሪ የቅበላ አቅሙ በአሁኑ ወቅት ከ50 ሺህ በላይ ደርሷል።

    ምንጭ፦ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ እና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ዶ/ር ጌትነት አሸናፊ (ፎቶ፦ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ)

    Semonegna
    Keymaster

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያስገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የግንባታ ሥራው የተጀመረው በጥቅምት ወር 2009 ዓ.ም ሲሆን የቻይናው ግዙፍ ኩባንያ ቻይና ሲቪል እንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ግንባታውን ሲያከናውን ነበር።

    አዳማ (Semonegna) – በኦሮሚያ ክልል፣ አዳማ ከተማ የተገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በዛሬው ዕለት (መስከረም 27 ቀን 2011 ዓ.ም.) ተመርቋል። በምርቃቱ ስነ ስርዓት ላይም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) እና የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዝደንት አቶ ለማ መገርሳ፣ የአማራ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ የእንደስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አርከበ ዕቁባይ እና የኮርፖሬሽኑዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ት ሌሊሴ ነሜ እንዲሁም ሌሎች የክልልና የፌደራል ባለስልጣናት ከፍተኛ ተገኝተዋል።

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያስገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የግንባታ ሥራው የተጀመረው በጥቅምት ወር 2009 ዓ.ም ሲሆን የቻይናው ግዙፍ ኩባንያ ቻይና ሲቪል እንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን (China Civil Engineering Construction Corporation/ CCCC) ግንባታውን ሲያከናውን ነበር።

    ከአዲስ አበበ ከተማ 99 ኪሎ ሜትሮች ርቆ የሚገኘው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በተለያየ ዘርፍ ለሚሰማሩ አምራች ኩባንያዎች የሚያገለግሉ በአጠቃላይ 19 (በዝርዝር፦ ስድስት 11 ሺህ ካሬ ሜትር፣ ዘጠኝ 5 ሺህ 500 ካሬ ሜትር፣ አራቱ ደግሞ በ3 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፉ) የመሥሪያ ጠለላዎች ወይም የመሥሪያ ቦታዎችን (shades) የያዘ ነው። የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በአጠቃላይ ሊለማ ከታቀደው 2 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በመጀመሪያው ዙር ልማት 354 ሄክታር መሬት የሚይዝ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ለምቶ ለዛሬ ምረቃ የበቃው በ100 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባው ክፍል መሆኑን፣ ይህም ግንባታ 4.1 ቢልዮን ብር መፍጀቱን፣ እንዲሁም ፓርኩ በመጀመሪያው ምዕራፍ በሙሉ አቅም ወደ ምርት ሲገባ እስከ 25 ሺህ ለሚደርሱ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ወ/ት ሌሊሴ ነሜ በምረቃው ንግግራቸው ላይ አስታውቀዋል።

    ◌ RELATED: A visit to Hawassa Industrial Park by Dire Dawa Industrial Park & City’s Administration people

    የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ሥራ መጀመር በሀገሪቱ ወደማምረት የገቡ የኢንዱስትሪ ፓርክኮች ቁጥር ወደ አምስት የሚያሳድገው ሲሆን፥ ከሌሎቹ አራቱ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለየት የሚያደርገው ፓርኩ ያለበት ከተማ (አዳማ) በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ አስተዋጽዖ ያመጣል ተብሎ የታመነበተና አምና ሥራ የጀመረው የአዲስ አበባ-ጅቡቲ የባቡር መስመር በሚያልፍባት የአዳማ ከተማ መገኘቱ ነው። ይህ የባቡር መስመርና የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ እርስ በርሳቸው ጉልህ የሆነ የጥቅም ግንኙነት ይኖራቸዋል ተብሎ ይታመናል። ከዚህ በተጨማሪ የኢንዱስትሪ ፓሩኩ በከተማ ከሚገኘው የአዳማ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ጋር በማምረት ዘርፍ እና በመማር፣ ማስተማርና ምርምር ዘርፎች መካከል ቁልፍ የሆነ ግንኙነት ይፈጥራሉ ይጠበቃል።

    የሀገሪቱ የማኑፋክቸሪንግ ሴክተር (manufacturing sector) ከኢትዮጵያ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) መጠን አራት ነጥብ አምስት በመቶ (4.5%) ድርሻ ብቻ የሚሸፍን ሲሆን፥ መንግስት እስከ 2022 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) ይህን አናሳ ድርሻ ወደ ሀያሁለት በመቶ (22%) ለማሳደግ አቅዳለች። ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጵያ እስከ 2025 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) አሁን ያሏትን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ቁጥር ከአምስት ወደ ሀያ አምስት የማሳደግ ዕቅድ አላት። በያዝነው ዓመት ስድስት የኢንዱስትሪ ፓርኮች (ድሬ ዳዋ፣ ቂሊንጦ II፣ ቦሌ ለሚ II፣ ጅማ፣ ባህር ዳር እና ደብረ ብርሃን) ግንባታቸው ተጠናቆ ወደምርት ተግባር እንደሚገቡ ዶክተር አርከበ ዕቁባይ አስታውቀዋል። 

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ

Viewing 13 results - 16 through 28 (of 28 total)