Search Results for 'ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር'

Home Forums Search Search Results for 'ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር'

Viewing 7 results - 16 through 22 (of 22 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    የዘንድሮው የዓለም የስኳር ህመም ቀን  ቤተሰብ የስኳር ህመምን ለመከላከል ባለው ሚና ላይ ተመሥርቶና “የስኳር ህመም ይመለከተኛል” በሚል መሪ ሀሳብ ኅዳር 5 ቀን 2011 ዓ.ም. በብሔራዊ ትያትር ይከበራል።

    አዲስ አበባ (ኢ.ዜ.አ) – የጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ስኳር ህመም ማህበር ኅዳር 5 ቀን 2011 ዓ.ም. በዓለም አቀፍና በኢትዮጵያ ለ28ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም የስኳር ህመም ቀን አስመልክቶ በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።

    የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ ከዓለም አቀፉ ስኳር ህመም ፋውንዴሽን እና “Doctors with Africa CUAMM” ከተባለ ድርጅት ጋር በመተባበር ቀኑ ቤተሰብ የስኳር ህመምን ለመከላከል ባለው ሚና ላይ ተመሥርቶና “የስኳር ህመም ይመለከተኛል” በሚል መሪ ሀሳብ በብሔራዊ ትያትር ይከበራል።

    የኢትዮጵያ ስኳር ህመም ማህበር (EDA) ፕሬዚዳንት ዶ/ር አብዱራዛቅ አህመድ በኢትዮጵያ 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዜጎች ከስኳር ህመም ጋር እንደሚኖሩ ገልጸዋል።

    በኢትዮጵያ የስኳር ህመም ስሜትና ምልክት ሳይታይ የጤና ምርመራ የማድረግ ባህል አነስተኛ በመሆኑ ከስኳር ህመም ጋር እየተኖረ እንኳን ማወቅ ባለመቻሉ የችግሩን አሳሳቢነት እንደሚያጎላው ዶ/ር አብዱራዛቅ ተናግረዋል።

    በህመሙ ከተያዙት 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዜጎች በተጨማሪ ሌሎች 9 ነጥብ 1 ሚሊዮን ዜጎች በተለያየ አጋጣሚ የስኳር መጠን መዛባት እየጋጠማቸው መሆኑንና ይህም ችግር ካልተፈታ የታማሚዎች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ሊጨምር እንደሚችል አመልክተዋል። በአብዛኛው በኢትዮጵያ በስኳር ህመም የሚኖሩ ሰዎች በምርመራ የጤና ሁኔታቸውን ያላወቁ መሆናቸውን ነው ዶ/ር አብዱራዛቅ ያስረዱት።

    አሁን ባለው ሁኔታ የስኳር ህመም ስርጭት በቁጥጥር ስር ካልዋለ ህመሙ ልብን፣ ዓይንን፣ ኩላሊቶችን፣ ነርቮችንና የደም ቱቦዎችን ተግባር በመጉዳትና ተግባራቸውን በማስተጓጎል ከባድ የጤና ቀውስ እንደሚያስከትልም ጠቅሰዋል።

    የኢትዮጵያ ስኳር ህመም ማኅበር የህመም ስርጭቱን አሳሳቢነት በመገንዘብ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመሆን የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ፣ የመድኃኒት አቅርቦትና የህክምና ተደራሽነቱን ለማስፋትና ለጤና ባለሙያዎች ሙያዊ ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

    ጤናማ ያልሆነ የአኗኗርና የአመጋገብ ዘይቤ፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መቀነስ፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረትና የደም ግፊት ለስኳር ህመም አጋላጭ ሁኔታዎች እንደሆኑም ነው ዶ/ር አብዱራዛቅ ያስረዱት። በአጠቃላይ የስኳር ህመምን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ጤናማ የአኗኗር ዘይቤ መከተል በተለይ ሁለተኛውን የስኳር ዓይነት (Type 2 Diabetes) በ80 በመቶ ለመከላከል እንደሚያስችል ጠቅሰዋል።

    ህብረተሰቡ በተቻለው አቅም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማዘውተር እንደሚገባውና አትክልትና ፍራፍሬዎችን መመገብ እንዲሁም ህመም ቢሰማም ባይሰማም በዓመት አንድ ጊዜ የስኳር ህመም ምርመራ ማድረግ እንደሚገባውም ምክራቸውን አቅርበዋል።

    የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ባለሙያ አቶ አፈንዲ ኡስማን በበኩላቸው ሚኒስቴሩ አሁን ያለውን የስኳር ህመም ችግር አሳሳቢነት ለመከላከል የሚያስችሉ ጅምር ሥራዎችን እያከናወነ ነው ብለዋል።

    የስኳር ህመም መርሃ ግብር ከፌደራል እስከ ክልል ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች (non-communicable diseases) ላይ ከሚሰሩ ሥራዎች መካከል እንደ ዋና መርሃ ግብር በማካተት በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

    ሚኒስቴሩ የአምስት ዓመት አገር አቀፍ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ አቅድ የስኳር ህመምን በዋናነት ባከተተ መልኩ አዘጋጅቶ የመተግበር ሥራንም እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

    የጤና ባለሙያዎችን፣ የጤና ማኅበራትንና የባለድርሻ አካላትን ያካተተ ብሔራዊ የስኳር ህመምን መከላከልና መቆጣጠር አማካሪ ግብረ ኃይልም ተቋቁሞ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩንም ነው አቶ አፈንዲ ያስረዱት።

    በተጨማሪም የስኳር ህመምና ተጓዳኝ የጤና ችግሮች መድኃኒቶችን ተመጣጣኝ በሆነ ክፍያ እንዲገኝ ለማድረግም ሁኔታዎችን የማመቻቸት፣ በተቀናጀ መልኩ የስኳር ህመምን ለመከላከል በጤና ጣቢያዎችና ሆስፒታሎች የበሽታውን የመቆጣጠር መርሃ ግብር ሥራዎችና ሌሎችም ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል። የስኳር ህመምን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ሁሉም ባለድርሻ አካል አስፈላጊውን ጥረት እንዲያደርግም ጠይቀዋል።

    ዓለም አቀፉ የስኳር ህሙማን ቀን ኅዳር 5 ቀን 2011 ዓ.ም. በብሔራዊ ትያትር ሲከበር የፓናል ውይይት እንደሚካሄድና የህክምና ባለሙያዎችም ስለ በሽታው ገለጻ እንደሚያደርጉ በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ተጠቅሷል።

    የስኳር ህመም የሚከሰተው ሰውነታችን ለኑሮም ሆነ ለእድገት የሚያስፈልገውን ስኳር በትክክል ለመጠቀም ሳይችል ሲቀር ሲሆን አንድ ሰው የስኳር ህመም አለው የምንለው በደም ውስጥ ያለው የስኳር መጠን ከሚገባው በላይ ከፍ ብሎ ሲገኝ እንደሆነም የህክምና ባለሙያዎች ይገልጻሉ።

    እንደ ዓለም አቀፉ ስኳር ህመም ፌዴሬሽን እ.ኤ.አ በ2017 ባወጣው መረጃ መሠረት በዓለም ደረጃ ከ425 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ከህመሙ ጋር የሚኖሩ ሲሆን አስፈላጊው የበሽታው መከላከልና መቆጣጠር ካልተሰራ እ.አ.አ በ2045 የህሙማኑ ቁጥር 629 ሚሊዮን ሊደርስ እንደሚችል ቅድመ ትንበያውን አስቀምጧል።

    ዓለም አቀፉ የስኳር ህመም ፌዴሬሽን (IDF) እ.ኤ.አ ከ1991 ጀምሮ የያዝነው ኅዳር ወር በዓለም አቀፍ ደረጃ የስኳር ህመምና ተጓዳኝ ችግሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ወር በሚል ተሰይሟል።

    በኢትዮጵያ በበሽታው ከተያዙ 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዜጎች ውስጥ 90 በመቶው በሁለተኛው የስኳር ዓይነት (Type 2 Diabetes) የተያዙ ሲሆን የተቀሩት በአንደኛው የስኳር ዓይነት (Type 2 Diabetes) የተያዙ ናቸው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) | Semonegna Health

    የስኳር ህመም

    Semonegna
    Keymaster

    ኢትዮጵያ ውስጥ እስካሁን ድረስ የካንሰር ህክምና አገልግሎት በብቸኝነት ሲሰጥ የነበረው የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እንደነበረና የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ይህን አገልግሎት መጀመሩ ለታካሚዎች ትልቅ አስተዋጽዖ ይኖረዋል።

    አዲስ አባባ (ዋልታ/ ሰሞነኛ) – የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ከመስከረም 2 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ የካንሰር ህክምና አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ አስታውቋል። ሆስፒታሉ ህክምናውን ከጀመረበት ቀን አንስቶ እስካሁን ድረስ ከ300 በላይ የካንሰር ታማሚዎችን በተመላላሽ ማከሙንም ገልጿል።

    በሆስፒታሉ የካንሰር ህክምና ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር አብዲ አደም የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ይህንን ህክምና መጀመሩ ከዚህ በፊት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በቦታ ጥበት ምክንያት በወረፋ ለሚንገላቱ ታካሚዎች መፍትሔ ይዞ መምጣቱን ገልጸዋል።

    እስካሁን በተመላላሽ ህክምና ለታካሚዎች አገልግሎት ሲሠጥ መቆየቱን የገለጹት ዶ/ር አብዲ በቅርቡ አስተኝቶ ማከም የሚያስችል ወደ 350 የሚጠጋ አልጋ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታውቀዋል።

    ዋልታ ያነጋገራቸው በሆስፒታሉ የካንሰር ታካሚዎች እንደገለጹት ከዚህ በፊት ህክምናውን ለማግኘት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እስከ ስድስት ወር እንደሚወስድ ገልጸው አሁን ግን በቅዱስ ጳውሎስ አገልግሎት መጀመሩ ያለምንም ወረፋ ህክምናን ለማግኘት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።

    Ethiopia: Are Ethiopian hospitals constructed in environment-suitable and climate-friendly way?

    በኢትዮጵያ የተደራጀ የጥናት ውጤት ባይኖርም በግምት በዓመት ከ160 ሺህ በላይ የካንሰር ተጠቂዎች እንደሚኖሩ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። እ.ኤ.አ በ2012 በተደረገ ጥናት ኢትዮጵያ ውስጥ በዓመት ውስጥ ከሚሞቱ ሰዎች ውስጥ 5.8 በመቶ የሚሆኑት በካንሰር ምክንያት እንደሚሞቱ ይጠቁማል። በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ስር የብሔራዊ የካንሰር ቁጥጥር ፕላን ባወጣው በዚህ ጥናት ምንም እንኳን ከአዲስ አበባ ከተማ ውጪ አጠቃላይ የሕዝብ ቆጠራን ተገን ያደረገ አሀዝ (population-based data) ባይኖርም ኢትዮጵያ ውስጥ በየዓመቱ 60,960 ሰዎች በተለያዩ ዓይነት የካንሰር በሽታዎች እንደሚጠቁና 44,000 ሰዎች ደግሞ በካንሰር ምክንያት እንደሚሞቱ ያትታል። በዚህም የካንሰር በሽታ በከፍተኛ ቁጥር ሰዎችን ከሚያጠቁ አራት ተለላፊ ካልሆኑ በሽታዎች [non-communicable diseases] ውስጥ ከልብ በሽታ ቀጥሎ ሁለተኛው ነው። (እነዚህ አራቱ ተለላፊ ከሆኑ በሽታዎች የልብ በሽታ፣ ካንሰር፣ የስኳር በሽታ እና የሳንባ በሽታ ሲሆኑ ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎ ከሚሞቱት ሰዎች ቁጥር 80 በመቶ የሚሆነው ከእነዚህ በሽታዎች በአንዱ ምክንያት የሚሞት ነው።) ኢትዮጵያ ውስጥ ወንዶች ላይ የደምየ አንጀት ካንሰሮች፣ ሴቶች ላይ ደግሞ የጡት ካንሰር በከፍተኛ መጠን እንደሚታይ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ሪፖርት ያሳያል።

    የዓለም ጤና ድርጅት ለአንድ ሚሊዮን ሰዎች አንድ የካንሰር ህክምና ተቋም ሊኖር እንደሚገባ ቢመክርም በኢትዮጵያ ግን ከ1987 ዓ.ም ጀምሮ የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በብቸኝነት የህክምናውን አገልግሎት ይሰጥ እንደነበርና እ. ኤ.አ በ2017 በወጣ አሃዝ ከ6,000 በላይ የካንሰር ታካሚዎችን እያከመ እንደሚገኝ መረጃዎች ይጠቁማሉ። የስዊዘርላንዱ መድኃኒት አምራች ግዙፍ ኩባንያ ኖቫትሪስ (Novartis) እ.ኤ.አ በ2017 ባወጣው ዘገባ ከ100 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ በቁጥር ስምንት ኦንኮሎጂስቶች (የካንሰር ሀኪሞች) ብቻ እንዳላት አስታውቋል። ሌላ ተመሳስይ ጥናት ደግሞ ብቸኛው የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ካሉት 627 ነርሶች ውስጥ 26ቱ ብቻ የካንሰር ህክምና ነርሶች እንደሆነ ይጠቁማል።

    ዋልታ | ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል

    Semonegna
    Keymaster

    የማህፀን በር ካንሰር ክትባት መሰጠት ያለበት ከ9 ዓመት ጀምሮ ላሉ ልጃገረዶች ቢሆንም በዓለም አቀፍ ደረጃ ባጋጠመው ክትባት እጥረት ምክንያት ዕድሜያቸው 14 ዓመት ለሆኑ ብቻ እንደሚሰጥ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታውቋል።

    አዲስ አበባ (የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር) – ከመጪው ህዳር ወር 2011 ዓ.ም ጀምሮ የማህፀን በር ካንሰር ቅድመ መከላከያ ክትባት በአገር አቀፍ ደረጃ መሰጠት ሊጀመር መሆኑን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቀ።

    ክትባቱ ዕድሜያቸው 14 ዓመት ለሞላቸው ልጃገረዶች በጤና ተቋማት፣ በትምህርት ቤቶችና በጊዜያዊ የክትባት ማዕከሎች ይሰጣል። የማህፀን በር ካንሰር ክትባት በሙከራ ደረጃ በትግራይና ኦሮሚያ በተመረጡ ወረዳዎች ላለፉት ሁለት ዓመታት ሲሰጥ ቆይቷል።

    በሚኒስቴሩ የክትባት ባለሙያ አቶ ጌትነት ባየ እንዳሉት፥ ክትባቱን ለማስጀመር በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ለሚገኙ ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና ይሰጣል።

    “ከመጪው ህዳር ወር ጀምሮም በአገር አቀፍ ደረጃ ዕድሜያቸው 14 ዓመት ለሞላቸው ልጃገረዶች ክትባቱ መሰጠት ይጀምራል” ብለዋል አቶ ጌትነት ።

    የማህፀን በር ካንሰር ክትባት መሰጠት ያለበት ከ9 ዓመት ጀምሮ ላሉ ልጃገረዶች ቢሆንም በዓለም አቀፍ ደረጃ ባጋጠመው ክትባት እጥረት ምክንያት ዕድሜያቸው 14 ዓመት ለሆኑ ብቻ ነው የሚሰጠው።

    የማህፀን በር ካንሰር መንስኤው “ሂውማን ፓፒሎማቫይረስ” (Human papillomavirus) በሚባል ኢንፌክሽን የሚመጣ ሲሆን፥ የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) እንደሚያስታውቀው አግባብ የሆነ በሽታን የመከላከል አቅም ያላቸው ሴቶች (women with normal immune systems) በቫይረሱ ከተጠቁ በኋላ የማህፀን በር ካንሰር ምልክት ሳይታይባቸው ከ15 እስከ 20 ዓመታት ሊቆዩ እንደሚችሉ፣ ደካማ የሆነ በሽታን የመከላከል አቅም ያላቸው ሴቶች (women with weak immune systems) ደግሞ ምልክቱ ሳይታይባቸው ከ5 እስከ 10 ዓመታት ሊቆዩ እንደሚችሉ ያትታል።

    ለበሽታው ከሚያጋልጡት ምክንያቶች ውስጥ ዋነኞቹ ልጃገረዶች በለጋነት እድሜያቸው የግብረ ስጋ ግንኙነት መጀመርና ከተለያዩ ሰዎች ጋር ፆታዊ ግንኙነት ማድረግ ሲሆኑ፥ ሲጋራ ማጨስም ሌላው ምክንያት ነው።

    ከ30 እስከ 45 ዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ሴቶች የማህፀን በር ቅድመ ካንሰር ምርመራ እንዲያደርጉ እና ወደ ህክምና ተቋማት መጥተው ምርመራ በማድረግ ራሳቸውን ከበሽታው መጠበቅ እንደሚኖርባቸው ይመከራል።

    በታዳጊ ሀገራት የማህፀን በር ካንሰር በዓለም አቀፍ ደረጃ ከጡት ካንሰር ቀጥሎ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች በሁለተኛ ደረጃ ተቀምጧል። ከዚህ በተጨማሪ በዓለም ላይ እጅግ በብዛት ከሚታይባቸው ሀያ አገራት ውስጥ አስራ ዘጠኙ የአፍሪካ አገራት እንደሆኑ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

    HPV Information Centre የሚባለው ድርጅት እ.ኤ.አ በሀምሌ ወር በ2017 ዓ.ም ባወጣው ሪፖርት ኢትዮጵያ ውስጥ በየ ዓመቱ 7,095 ሴቶች ማህፀን በር ካንሰር የሚጠቁ ሲሆን፣ በየዓመቱም 4,732 ሴቶች በዚሁ ካንሰር ምክንያት ለሞት እንደሚዳረጉ ዘግቧል።

    ምንጭ፦ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) እና የዓለም የካንሰር ምርምር ፈንድ (WCRF)

    የማህፀን በር ካንሰር

    Semonegna
    Keymaster

    አዲሱ የካቢኔ አባላት ሹመት የቀረበው የአስፈፃሚ አካላት ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣውን አዋጅ እንደገና ለማሻሻል የቀረበውን አዲስ ረቂቅ አዋጅ በምክር ቤቱ መፅደቁን ተከትሎ መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት  አስታውቋል።

    አዲስ አበባ – የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከ20 አዳዲስ የካቢኔ አባላት ሹመት ውስጥ 50 በመቶ ሴቶች ሆነው እንዲያገለግሉ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) የቀረበውን ሹመት ጥቅምት 6 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ አፀደቀ።

    የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን እያደረገ የሚገኝ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከሚሾሙት 20 ካቢኔዎች ውስጥ 10 ሴቶች ሆነው በተሰጣቸው ኃላፊነት እንዲያገለግሉ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

    አዲሱ የካቢኔ አባላት ሹመት የቀረበው የአስፈፃሚ አካላት ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣውን አዋጅ እንደገና ለማሻሻል የቀረበውን አዲስ ረቂቅ አዋጅ በምክር ቤቱ መፅደቁን ተከትሎ ነው።

    በዚህም መሠረት የሹመቱ ዋና መስፈርት ብቃት፣ የትምህርት ዝግጅትና ለውጥን የመምራት አቅም መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ከሚሾሙት ካቢኔዎች 50 በመቶ (በቁጥር፥ ወይም ከ20ዎቹ 10 ሴት) ካቢኔዎች መሆናቸውንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልፀዋል።

    ይህም በኢትዮጵያ ምናልባትም በአፍሪካ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑም በምክር ቤቱ ተገልጿል።

    በዚህ በተደረገው የካቢኔ ሹመት ለውጥ ውስጥ ከዚህ በፊት “የፐብሊክ ሰርቪስ እና ሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር” ተብሎ ይጠራ የነበረው ሚኒስቴር ተለውጦ አሁን “ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን” (Civil Service Commission) በሚል እንደተተካ ታውቋል። ከዚህ በተጨማሪ ሶስት ኮሚሽኖችም በአዲስ መልክ ተካተዋል፤ እነዚህም (1) የሥራ ፈጠራ ኮሚሽን (Job Creation Commission)፣ የአካባቢ፣ የደንና የአየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽን (Environment, Forestry and Climate Change Commission) እና የፕላንና እድገት ኮሚሽን (Plan and Development Commission) ናቸው።

    አዲስ በተዋቀረው ካቢኔ ውስጥ የተሰየሙት ባለስልጣናትና የተሰየሙበት ስልጣን ዝርዝር

    1. ዶ/ር ሂሩት ካሳው ― የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር
    2. ዶ/ር ሂሩት ወልደማርያም ― የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር
    3. ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ― የሰላም ሚኒስቴር
    4. ዶ/ር ሳሙኤል ሆርቃ ― የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር
    5. ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ― የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር
    6. አቶ ብርሃኑ ጸጋዬ ― ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ
    7. አቶ አህመድ ሺዴ ― የገንዘብ ሚኒስቴር
    8. ዶ/ር አሚን አማን ሐጎስ ― የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር
    9. ወ/ሮ አዳነች አበበ ― የገቢዎች ሚኒስቴር
    10. ኢ/ር አይሻ መሀመድ ሙሳ ― የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር
    11. አቶ ኡመር ሁሴን ― የግብርና ሚኒስቴር
    12. ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ ― የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር
    13. ወ/ሮ የዓለምፀጋይ አስፋው — የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር
    14. ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ― የትራንስፖርት ሚኒስቴር
    15. አቶ ጃንጥራር አባይ ― የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
    16. ዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን መኩሪያ ― የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር
    17. ዶ/ር ጥላዬ ጌጤ ― አምባዬ የትምህርት ሚኒስቴር
    18. ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ― የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
    19. ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረ-እግዚአብሔር ― የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር
    20. ዶ/ር ፍፁም አሰፋ ― የፕላን ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የካቢኔ አባላት ሹመት

    Semonegna
    Keymaster

    የአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (በተለምዶው አማኑኤል ሆስፒታል) ኢትዮጵያ ውስጥ የአዕምሮ ህክምና የሚሰጥ ትልቁ ሆስፒታል ሲሆን፥ የተቋቋመውም በጣልያኖች እ.ኤ.አ በ1937 ዓ.ም አካባቢ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ። 

    አዲስ አበባ – በየዓመቱ እ.ኤ.አ ጥቅምት 10 ቀን የሚከበረውን የዓለም የአዕምሮ ጤና ቀን የአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በአገራችን ለ26ኛ ጊዜ “ወጣቶች እና የአዕምሮ ጤና በተለዋዋጭ ዓለም ውስጥ” በሚል መሪ ቃል የተለያዩ ምሁራን፣ የህክምና ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም የሆስፒታሉ ሠራተኞች በተገኙበት መስከረም 30 ቀን 2011 ዓ.ም በአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ውስጥ በድምቀት ተከበረ።

    የዓለም የአዕምሮ ጤና ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች የተከበረ ሲሆን ቀኑን አስመልክቶ የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ኢዳኦ ፈጆ በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ “ወጣቶች ብዙ ጊዜያቸውን የሚያሳልፉት የዓለም መረጃ መረብ ላይ በመጠመድ የሳይበር ወንጀልን በመለማመድ፤ ይህንኑ የመገናኛ መረብ በመጠቀም ህዝብን ወደ አልተፈለገ የእርስ በርስ ግጭቶች ውስጥ በማስገባት እና ከዚህም ሲያልፍ ከማኅበረሰቡ ባህልና ሞራል ውጭ የሆኑ ባዕዳን ቪዲዮዎችን በመመልከት ላይ ነው” ሲሉ አስገንዝበዋል።

    አያይዘውም ራሳቸውን የሚያጠፉና በአደንዛዥ እፅ ሱስ ስር እየወደቁ የሚገኙ የማኅበረሰብ ክፍሎች ቁጥር እያሻቀበ መምጣቱ እማኝ የሚያሻው ጉዳይ እንዳልሆነ በመጥቀስ በዚህ አዙሪት ውስጥ የሚያልፉት ደግሞ አብዛኛውን ወጣቶች መሆናቸው እጅግ አስደንጋጭ ነው ብለዋል። ዋና ሥራ አስኪያጁ እንደገለፁት አብዛኛው የአዕምሮ ህመሞች በወጣትነት የእድሜ ክልል ውስጥ የሚከሰቱ መሆናችውና ወጣቶቹ ደግሞ ስለ አዕምሮ ጤና ያላቸው ግንዛቤ እና አስተምህሮ አናሳ መሆኑ ይበልጥ ተጋላጭ ያደርጋቸዋል ሲሉ አክለዋል።

    በመጨረሻም “ይህ ቀን ወጣቶቻችን እንዴት ጠንካራ፣ ችግር ፈች፣ ከሱስ አዙሪት፣ ከእርስ በርስ ግጭቶች፣ ከእፅ ተጠቃሚነት እና ከልክ ያለፈ የኢንተርኔት ተጠቃሚነት (substance abuse and internet overload) ሰብረው መውጣት የሚችሉበትን መፍትሄ የምናፈላልግበትና የምንመክርበት ጊዜው አሁን ነው” በማለት ለታሳታፊዎቹ መልእክታቸውን በአንክሮ አስተላልፈዋል።

    በዝግጅቱ ላይ ቀኑን አስመልክቶ የአዕምሮ ጤና ምንነት፤ በአዕምሮ ጤና ላይ የማኅበረሰቡ የግንዛቤ ደረጃ ፤ በአገር አቀፍ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው የስርጭት ሁኔታ እንዲሁም ወጣቶች እና የአዕምሮ ጤና በአሁኑ ወቅት ምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ስፔሻሊስት በሆኑት በዶ/ር ሙሃመድ ንጉሴ እና በዶ/ር ዮናስ ላቀው ለተሳታፊዎቹ ገለፃ ቀርቧል። በመቀጠልም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በእንግድነት የተገኙት ፕሮፌሰር አታላይ ዓለም እንደተናገሩት በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ እየንተሰራፋ የመጣውን የአዕምሮ ጤና ችግር ለመቀነስና መፍትሄ ለማበጀት መንግስት፤ ባለድርሻ አካላት እና ሚዲያዎች የአንበሳውን ድርሻ ሊወስዱ እንደሚገባ ገልፀዋል።

    በመጨረሻም በተለያየ የአዕምሮ ህመም ተጠቂ ሆነው አማኑኤል ሆስፒታል ውስጥ ህክምና ተደርጎላቸው በመልካም ጤና ላይ የሚገኙ ሶስት ፈቃደኛ ግለሰቦች ሆስፒታሉን ከማመስገን ባለፈ በአዕምሮ ጤና ላይ የነበራቸውን ግንዛቤ እና ልምድ ለተሳታፊዎች ያካፈሉ ሲሆን በመልእክታቸውም የአዕምሮ ህመም እንደማንኛውም ህመም ውጤታማ ህክምና ያለው መሆኑን በማስተላለፍ በማኅበረሰቡ ዘንድ ስለ አዕምሮ ህመም ያለውን የተዛባ ግንዛቤ ለመቅረፍ መንግስት እና ህዝብ በጋራ ሊሰሩ እንዲሚገባ አስተላልፈዋል።

    ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ስር የሚተዳደረው የአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (በተለምዶው አማኑኤል ሆስፒታል) ኢትዮጵያ ውስጥ የአዕምሮ ህክምና የሚሰጥ ትልቁ ሆስፒታል ሲሆን፥ የተቋቋመውም በጣልያኖች እ.ኤ.አ በ1937 ዓ.ም አካባቢ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሆስፒታሉ ዘርፈ ብዙ ማስፋፋቶችን እያከናወነ ሲሆን፥ በየካቲት ወር 2009 ዓ.ም. በሆስፒታሉ ስር ሆኖ የየካ ኮተቤ ሆስፒታል የአዕምሮ ህክምና መስጠት ጀምሯል

    ምንጭ፦ የአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

    አማኑኤል ሆስፒታል

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር)– ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ የ20ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን እያከበረ ሲሆን ይህን ተከትሎም ኦርቢስ በራሪው የአይን ሆስፒታል በቦሌ ኢንተርናሽናል አየር ማረፊያ የስልጠና አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

    የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ከበደ ወርቁ በመክፈቻ ስነ ሥርዓቱ ላይ በመገኘት እንደተናገሩት ሀገሪቱ በአይን ህክምና ዙሪያ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነች ትገኛለች። ለነዚህ ሥራዎች መሳካትም በርካታ በአይን ህክምና ዙሪያ የሚሠሩ አጋር አካላት ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በትብብር እየሠሩ መሆናቸውን የተናገሩት ዶ/ር ከበደ ወርቁ በተለይም ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ሊታከም የሚችል አይነ-ስውርነትን አስቀድሞ በመከላከል ረገድ፣ የዘርፉን ባለሞያዎች በዕዉቀት እና በክህሎት በማብቃት፣ በአይን ህክምና ዙሪያ የሚሠሩ የትምህርት ተቋማትን አቅም በመገንባት፣ ለአይን የሚደረጉ ጥንቃቄዎችን አስመልክቶ ግንዛቤ በመፍጠር እንዲሁም በዘርፉ የሚደረጉ ጥናትና ምርምሮች ላይ በመሥራት እና የተለያዩ ግብአቶችን በማቀረብ ላለፉት ሀያ አመታት ከፍተኛ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰው አመስግነዋል።

    በቀጣይም ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በአይን ህክምና ዙሪያ ለሚያከናውናቸው ስራዎች በትብብር እንደሚሰራ እና ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። በዕለቱም ዶ/ር ከበደ ወርቁ በቦሌ ኢንተርናሽናል አየር ማረፊያ በመገኘት ኦርቢት በራሪውን የአይን ሆስፒታል ወይም የአውሮፕላን ውስጥ የአይን ሆስፒታል ጎብኝተዋል።

    ኦርቢስ ኢንተርናሽናል

    በኢትዮጵያ የኦርቢስ ዳይሬክተር ዶ/ር አለማየሁ ሲሳይ በበኩላቸው ስለበራሪው የአይን ሆስፒታል እንደተናገሩት ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህክምና ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር ለአምስተኛ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ የመጣ ሲሆን አውሮፕላኑ በረቂቅ ቴክኖሎጂ የበለጸገ የማስተማሪያ ተቋም በመሆን ያገለግላል።

    በዚህም ለዶክተሮች፣ ለነርሶች እና ለህክምና ቴክኒሺያኖች ስልጠና ከመስጠት በተጨማሪ ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በመተባበር የአይን ህክምና ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲደርስ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። በራሪው የአይን ሆስፒታል በውስጡ እጅግ ዘመናዊ የቀዶ ጥገና፣ የመማሪያና የማገገሚያ ክፍሎች ያሉት እንደሆነ የተናገሩት ዳይሬክተሩ፥ የበጎ ፈቃደኛ ሀኪሞች ስልጠናን በአውሮፕላን ወስጥ እና በአካባቢው ከሚገኙ ሆስፒታሎች ጋር በመተባበር ይሰጣልም ብለዋል።

    በራሪው የአይን ሆስፒታል ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ ከከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህክምና ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር ለአምስተኛ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ እንደመጣም ገልጸዋል። ለሚቀጥሉት 15 ቀናትም በራሪው ሆስፒታል በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚቆይ ለማወቅ ተችሏል።

    ኦርቢስ ኢንተርናሽናል መንግስታዊ ያልሆነና የበጎ አድራጊ ዓለማቀፋዊ ድርጅት ሲሆን ዋነኛ ተግባሩም ዓይነ ስውርነትን መከላከልና የዓይን ህክምናን መስጠት ነው። ኦርቢስ ኢንተርናሽናል እ.ኤ.አ በ1960ዎቹ አሜሪካዊ የዓይን ህክምና ባለሙያ ዶ/ር ዴቪድ ፓተን (Dr. David Paton) ጽንሰ ሀሳቡን ጀምሮት በድርጅት ደረጃ የተቋቋመው  ደግሞ እ.ኤ.አ በ1982 ዓ.ም ሲሆን ዋና መቀመጫውን ኒው ዮርክ ከተማ (ኒው ዮርክ፣ አሜሪካ) አድርጎ ከ90 በላይ ሀገራት ይሠራል።

    ምንጭ፦ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    በኢትዮጵያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የጤናውን ዘርፍ ለማገዝ የተሰራችው ሰው አልባ አውሮፕላን (drone) ከቢሾፍቱ አየር ኃይል ወደ አዳማ ከተማ የተሳካ በረራ አድርጋለች።

    የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሰው አልባ አውሮፕላንን በመጠቀም የህክምና መሣርያዎችን እና መድኃኒቶችን ለማጓጓዝ የሚያስችል ስምምነትም ተፈራርመዋል።

    ስምምነቱ በ6 ጣቢያዎች 24 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን በመጠቀም እስከ 5ኪ.ግ. የህክምና ቁሳቁሶችንና መድኃኒቶችን ለማድረስ የሚያስችል ነው።
    ስምምነቱን የተፈራረሙት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስተር ጌታሁን መኩርያ (ዶ/ር ኢንጂ.) እና የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን ናቸው።

    የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌታሁን መኩርያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ሰው አልባ አውሮፕላንኗ በሳይንስና ቴክኖሎጂ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዞች መሠራቷን ጠቅሰው ለሳይንስና ቴክኖሎጂ መዳበር የበለጠ አስተዋጽዖ ሊያደርጉ የሚችሉ የሙያ ማኅበራትንና ወጣት የፈጠራ ባለሙያዎችን በመደገፍ በቀጣይ መሰል ቴክኖሎጂዎች ሽግግር ዙርያ ከቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዞች ጋር በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።

    ምንጭ፦ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

Viewing 7 results - 16 through 22 (of 22 total)