Search Results for 'የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት'

Home Forums Search Search Results for 'የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት'

Viewing 11 results - 1 through 11 (of 11 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    ወሎ ዩኒቨርሲቲ ባደረገው ድጋፍ የተቋቋመው የባቲ ለይቶ ማቆያ ማዕከል ተመረቀ

    (ወሎ ዩኒቨርሲቲ) – ከአፋር ክልልና ከጅቡቲ የሚመጡ መንገደኞችን ለይቶ በማቆየት የኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል በባቲ ወረዳ የተቋቋመው የለይቶ ማቆያ ማዕከል (quarantine center) ተመርቋል።

    ወሎ ዩኒቨርሲቲ ባደረገው ድጋፍ የተቋቋመው የባቲ ለይቶ ማቆያ ማዕከል ከሰኔ 8 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ማዕከሉን የወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ የኦሮሚያ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር፣ የባቲ ወረዳና ከተማ አመራሮች፣ በጎ ፍቃደኞችና የሀገር ሽማግሌዎች በጋራ ተመርቋል።

    የቅኝት አምባ፣ የወሎየነት ተምሳሌትና የንግድ የመተላለፊያ አውድ ባቲ በታሪክ አጋጣሚ ከጅቡቲ አፋርን አቋርጠው በሚመጡ መንገደኞች የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መተላለፊያ ኮሪደር ልትሆን ትችላለች የሚል ስጋት ተጭኖባታል። ከጅቡቲና አፋር ክልል እያቋረጡ የሚመጡ መንገደኞች ምርመራና ክትትል ሳይደርግላቸው ከመሀል ሀገር እንዳይገቡ ለማድረግ የለይቶ ማቆያ ማዕከል በባቲ ወረዳ ማቋቋም ተገቢ መሆኑን በጥናት ለይተናል ያሉት የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አባተ ጌታሁን ባቲ ወረዳን ማዳን ወሎን፣ ሰሜን ሸዋን በአጠቃላይ ከቫይረስ ስርጭት ሀገርን መታደግ ነው ብለዋል።

    አያይዘውም ፕሬዚዳንቱ የኦሮሚያ ብሄረሰብ ዞንና የባቲ ወረዳ አስተዳደር ዩኒቨርሲቲው የሰጣቸውን የለይቶ ማቆያ ቁሳቁስ በቀናት ውስጥ ሁሉን ነገር አዘጋጅተው ለአገልግሎት ዝግጁ ማድረጋቸው የአመራሩ፣ የኮሚቴውና የማኅበረሰቡ የቅንጅት ውጤት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

    ወሎ ዩኒቨርሲቲ በደሴና ኮምቦልቻ ካቋቋመው የለይቶ ማቆያ ማዕከል እኩል ግብአቶችንና ቁሳቁሶችን በማሟላት ሦስተኛው ማዕከል እንዲሆን የቻልነውን ሁሉ ለማድረግ እንሞክራለን ያለት የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት አማረ ምትኩ (ዶ/ር) ባቲ ወረዳ ከጅቡቲና አፋር የሚመጡ የከባድ መኪና ሹፌሮችና መንገደኞች መተላለፊያ ማዕከል እንደመሆኗ መጠን ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መሥራት እንዳለበት ተናግረዋል።

    ወሎ ዩኒቨርሲቲ የወሎ ሕዝብ አምባሳደርነቱን በተግባር እያስመሰከረ ነው ያሉት የኦሮሚያ ብሔረሰብ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አህመድ ሀሰን ዩኒቨርሲቲው የዞናችንን አቅም መሠረት ያደረጉ የልማት ሥራዎችን ከመሥራትና ከማስተዋወቅ ጀምሮ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል ለከሚሴና ባቲ ወረዳዎች የለይቶ ማቆያ ማዕከሎች ያደረገው ድጋፍ በታሪክ የትውልድ ቅብብሎሽ የሚዘከር ይሆናል ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

    ዩኒቨርሲቲው የባቲ ወረዳ ለይቶ ማቆያ ማዕከልን ለማቋቋም ከ5 መቶ ሺ ብር በላይ የሚያወጡ የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን ወሎ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ በፊት ዘግቦ ነበር።

    ምንጭ፦ ወሎ ዩኒቨርሲቲ/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ወሎ ዩኒቨርሲቲ ባደረገው ድጋፍ የተቋቋመው የባቲ ለይቶ ማቆያ ማዕከል

    Semonegna
    Keymaster

    የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝን ምላሽ ለመስጠት ከ220 በላይ የሕክምና መስጫ እና ለይቶ ማቆያ ማዕከላት ዝግጁ ተደርገዋል ― የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

    አዲስ አበባ (የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት) – በሀገራችን የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝን ምላሽ ለመስጠት ከአንድ መቶ ሺህ በላይ ሰዎችን ሊይዙ የሚችሉ ከ220 በላይ የሕክምናና የለይቶ ማቆያ ማዕከላት ተዘጋጅተዋል።

    በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከል የኮቪድ-19 የተቋማት ዝግጁነት ክፍል አስተባባሪ አቶ ኢሳያስ መሠለ እንደገለጹት፥ የኮሮና ቫይረስ በቻይና ዉሃን ከተማ (Wuhan) ከተከሰተ ጀምሮ በሀገራችንም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተሠርተዋል። ከዚህም ውስጥ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸውን ሰዎች የሕክምና መስጫ ማዕከል (treatment centers)፣ የበሽታውን ምልክት የሚያሳዩ ሰዎች የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎላቸው ውጤታቸው እስኪታወቅ ተለይተው የሚቆዩበት (isolation centers) እንዲሁም ከመጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ማንኛውም ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ ግለሰብ ለ14 ቀናት ለይቶ ማቆያ መግባት እንዳለበት በተላለፈው ውሳኔ መሠረት የለይቶ ማቆያ ቦታዎችን (quarantine centers) መለየትና ዝግጁ ማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ናቸው።

    በዚህም መሠረት ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በአዲስ አበባና በክልሎች ሙሉ በሙሉ ለኮሮና ቫይረስ ህሙማን አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘውን የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ጨምሮ ከ10,000 በላይ ሰዎች የሕክምና አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ከ40 በላይ ማዕከሎች (treatment centers) ዝግጁ የሆኑ ሲሆን ከ15,000 በላይ ሰዎችን አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ከ100 የሚበልጡ የለይቶ ማቆያዎች (isolation centers) እንዲሁም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ ከ80 በላይ የለይቶ ማቆያዎች (quarantine center) ተዘጋጅተዋል።

    ከዚህ ጋር በተያያዘም የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ብሔራዊ የድንገተኛ ማዕከል የኢንፌክሽን መከላከልና መቆጣጠር የውሀ፣ ሳኒቴሽንና ሀይጅን (WASH) ክፍል አስተባባሪ ወ/ሮ ኢክረም ሬድዋን እንደተናገሩት፥ ለኮሮና ቫይረስ (የኮቪድ-19) በሽታ በተዘጋጁ የለይቶ ማቆያ እና ሕክምና ማዕከላት ያሉ የውሀ፣ ሳኒቴሽንና ሀይጅን (WASH) እንዲሁም ኢንፌክሽንን ከመከላከልንና መቆጣጠር አንፃር ያሉ ክፍተቶችን በመለየት ለመሙላት እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ከውሀ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ ከውሀ ልማት ኮሚሽን እና ከአጋር ድርጅቶች በተደረጉ ድጋፎች ሲሆን የውሀ መቆራረጥና እጥረት ያለባቸውን ተቋማት ክፍተት መሙላት፤ የውሀ አቅርቦት መቆራረጥን ለመቀነስ የውሀ ታንከሮችና ፓምፖችን መግጠም፣ ውሀን በትራክ ማቅረብ እንዲሁም የእጅ መታጠቢያ እጥረት ባለባቸው የለይቶ ማቆያ እና ሕክምና ማዕከላት ከእጅ ንክኪ የጸዱ በእግር መከፈት የሚችሉ ተንቀሳቃሽ የእጅ መታጠቢያዎች እንዲተከሉ ተደርጓል።

    በተጨማሪም ለሁሉም ለይቶ ማቆያ እና ሕክምና ማዕከላት የኢንፌክሽን መከላከልና መቆጣጠር ባለሙያ እና በአዲስ አበባ ለሚገኙ የለይቶ ማቆያ እና ሕክምና ማዕከላት የፀረ ተህዋሲያን ኬሚካል ርጭት ባለሙያዎች ተመድበዋል። ለነዚህ ባለሙያዎችም የኮቪድ-19 የኢንፌክሽን መከላከልና መቆጣጠር ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ባለሙያዎቹም በአጠቃላይ የሚከናወኑ ተግባራት ኢንፌክሽንን ከመከላከልና መቆጣጠር አንጻር በአግባቡ እየተካሄዱ መሆናቸውን በየዕለቱ ይከታላሉ ብለዋል።

    በአጠቃላይ በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከሚሰሩ ሥራዎች ባሻገር ህብረተሰቡ የሚያደርጋቸው ጥንቃቄዎች ለበሽታው ያለመስፋፋት ወሳኝ በመሆናቸው ህብረተሰቡ ሳይዘናጋ የሚተላለፉ መልዕክቶችን እና መከላከያ መንገዶችን ተግባራዊ በማድረግ የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል።

    ለተጨማሪ መረጃ በስልክ መስመር 8335 ወይም በ952 በመደወል ወይም በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኢሜል አድራሻ ephieoc@gmail.com በመጠቀም ወይም ባሉበት ክልል በተዘጋጁ ነፃ የስልክ መስመሮች በመደወል ሪፖርት እንዲያደርጉ ወይም በአካባቢው ለሚገኙ ጤና ተቋማት በስልክ እንዲያሳውቁ እንጠይቀለን።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

    የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ

    Anonymous
    Inactive

    የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ለ18 ወራት የሚበቃ የመድኃኒት ክምችት መኖሩን ገለጸ
    ለለይቶ ማቆያዎች የሕክምና ቁሳቁሶች ተሟልቶ እየቀረበ እንደሚገኝ ተጠቁሟል

    አዲስ አበባ (አዲስ ዘመን) – የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ለ18 ወራት የሚበቃ የመድኃኒት ክምችት ለመያዝ እየሠራ መሆኑ ተገለጸ። በፌደራልና በክልል ደረጃ ለሚገኙ ለይቶ ማቆያዎች የሕክምና ቁሳቁሶች ተሟልቶ እየቀረበላቸው እንደሚገኝም ተጠቁሟል።

    በኤጀንሲው የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ወ/ሮ አድና በሬ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፥ ኤጀንሲው በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሳቢያ በሀገሪቱ የመድኃኒት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት ከወዲሁ ለ18 ወራት የሚበቃ የመድኃኒት ክምችት ለመያዝ እየሠራ ይገኛል።

    እንደ ዳይሬክተሯ ማብራሪያ፤ ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነው የመድኃኒት አቅርቦት ከውጭ የሚገባ በመሆኑ በሀገሪቱ የመድኃኒት አቅርቦት እጥረት አንዴ ከተከሰተ የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለመመለስ ጊዜ ስለሚወስድ ችግሩን በፍጥነት ለመቅረፍ አዳጋች ያደርገዋል። ኤጀንሲው ችግሩን ከግምት ውስጥ በማስገባት ቫይረሱ ወደ ሀገሪቱ ቢገባ በመድኃኒት አቅርቦቱ ላይ ሊያሳድር የሚችለውን ተጽኖ ታሳቢ በማድረግ፥ ኮሚቴ ተቋቁሞ በመጋዘን ምን ያህል የመድኃኒት ክምችት እንዳለ፤ ከወርሃዊ ፍጆታው አንጻር በመጋዘንና በመጓጓዝ ላይ ያለው መድኃኒት ለምን ያህል ጊዜ እንደሚበቃ፣ መጠናቸውን፣ የትኛው መድኃኒት ቀድሞ መግባት እንዳለበት፣ እስከ መቼ መድኃኒቶቹ ወደ አገር ውስጥ ሊገቡ እንደሚችሉ ቀደም ብሎ ጥናት ተደርጓል።

    ወ/ሮ አድና ኮሚቴው ቫይረሱ በሀገሪቱ ከተከሰተ በኋላም ከተመላላሽ ታካሚዎች ባሻገር በተለይ ተከታታይ መድኃኒት የሚወስዱ ወገኖች እጥረት እንዳያጋጥማቸው፣ በመጋዘንና በመጓጓዝ ላይ ያለው መድኃኒት ለነዚህ ወገኖች አቅርቦት ሳይቆራረጥ ምን ያህል ጊዜ ሊያስኬድ ይችላል የሚለው ላይም በድጋሚ ጥናት ማካሄዱን ተናግረዋል።

    ኤጀንሲው በጥናቱ መሠረት የመድኃኒቶቹን የአገልግሎት ዕድሜ ታሳቢ በማድረግ ለ18 ወራት የሚበቃ የመድኃኒት ክምችት ለመያዝ እየሠራ እንደሚገኝ ገልጸው፥ በተለይ የስኳር፣ የደም ግፊት፣ የአስም፣ የልብ ህመምተኞች በተከታታይ ከሚወስዷቸው መድኃኒቶች በተጨማሪ ኤችአይቪ (HIV) በደማቸው የሚገኝባቸው ወገኖች የሚወስዷቸው የፕሮግራም መድኃኒቶችን ለ18 ወራት የሚበቃ ክምችት ለመያዝ ታሳቢ ተደርጎ ግዢ እንዲፈጸም፣ በመጓጓዝ ላይ ያሉት በወቅቱ እንዲገቡና በመጋዘን ተከማችተው ያሉ መድኃኒቶችም በወቅቱ ወደ ጤና ተቋማቱ ተልከው ለህመምተኞች እንዲደርስ የማድረግ ሥራ እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

    ወ/ሮ አድና የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በጤና ቀውስነቱ እስከመቼ ድረስ እንደሚቀጥል ስለማይታወቅ የመድኃኒት አቅርቦት እጥረቱ ተከስቶ ችግር ውስጥ ከመገባቱ በፊት የመድኃኒት ክምችቱን ማሳደግ ላይ መሠራቱ ዘርፈ ብዙ ጥቅም እንዳለው ጠቁመው፥ ቀደም ሲል በውል የታሰሩ የመድኃኒት ግዢዎች በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ዋጋ ከመጨመር ባለፈ በውሉ መሠረት ድርጅቶቹ ለማቅረብ እያመነቱ በመሆኑ በተፈለገው መጠን መድኃኒቶቹን ለማከማቸት እንቅፋት ሊፈጥር እንደሚችል ተናግረዋል።

    በተያያዘ ዜና የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ የኮሮና ቫይረስ በሀገሪቱ ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ ወረርሽኙን ለመከላከል የሚያስችሉ የሕክምና ግብዓቶችን እያሠራጨ እንደሚገኝ ዳይሬክተሯ ገልጸው፥ ኤጀንሲው የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በሚያቀርበው ጥያቄ መሠረት በፌዴራልና በክልል ደረጃ ለሚገኙ ለይቶ ማቆያዎች ሙሉ ለሙሉ የሕክምና ቁሳቁሶችን አሟልቶ እያቀረበ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ Ethiopian Pharmaceuticals Supply Agency EPSA

    Anonymous
    Inactive

    የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝን ምላሽ ለመስጠት ከ220 በላይ የሕክምና መስጫ እና ለይቶ ማቆያ ማዕከላት ዝግጁ ተደርገዋል

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – በሀገራችን የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝን ምላሽ ለመስጠት ከአንድ መቶ ሺህ በላይ ሰዎችን ሊይዙ የሚችሉ ከ220 በላይ የሕክምናና የለይቶ ማቆያ ማዕከላት ተዘጋጅተዋል።

    በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከል የኮቪድ-19 የተቋማት ዝግጁነት ክፍል አስተባባሪ አቶ ኢሳያስ መሠለ እንደገለጹት፥ የኮሮና ቫይረስ በቻይና ዉሃን ከተማ (Wuhan) ከተከሰተ ጀምሮ በሀገራችንም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተሠርተዋል። ከዚህም ውስጥ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸውን ሰዎች የሕክምና መስጫ ማዕከል (treatment centers)፣ የበሽታውን ምልክት የሚያሳዩ ሰዎች የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎላቸው ውጤታቸው እስኪታወቅ ተለይተው የሚቆዩበት (isolation centers) እንዲሁም ከመጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ማንኛውም ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ ግለሰብ ለ14 ቀናት ለይቶ ማቆያ መግባት እንዳለበት በተላለፈው ውሳኔ መሠረት የለይቶ ማቆያ ቦታዎችን (quarantine centers) መለየትና ዝግጁ ማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ናቸው።

    በዚህም መሠረት ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በአዲስ አበባና በክልሎች ሙሉ በሙሉ ለኮሮና ቫይረስ ህሙማን አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘውን የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ጨምሮ ከ10,000 በላይ ሰዎች የሕክምና አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ከ40 በላይ ማዕከሎች (treatment centers) ዝግጁ የሆኑ ሲሆን ከ15,000 በላይ ሰዎችን አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ከ100 የሚበልጡ የለይቶ ማቆያዎች (isolation centers) እንዲሁም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ ከ80 በላይ የለይቶ ማቆያዎች (quarantine center) ተዘጋጅተዋል።

    ከዚህ ጋር በተያያዘም የኮቪድ-19 ብሔራዊ የድንገተኛ ማዕከል የኢንፌክሽን መከላከልና መቆጣጠር የውሀ፣ ሳኒቴሽንና ሀይጅን (sanitation and hygiene) ክፍል አስተባባሪ ወ/ሮ ኢክራም ሬድዋን እንደተናገሩት፥ ለኮሮና ቫይረስ (የኮቪድ-19) በሽታ በተዘጋጁ የለይቶ ማቆያ እና ሕክምና ማዕከላት ያሉ የውሀ ሳኒቴሽንና ሀይጅን እንዲሁም ኢንፌክሽንን ከመከላከልንና መቆጣጠር አንፃር ያሉ ክፍተቶችን በመለየት ለመሙላት እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ከውሀ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ ከውሀ ልማት ኮሚሽን እና ከአጋር ድርጅቶች በተደረጉ ድጋፎች ሲሆን፥ የውሀ መቆራረጥና እጥረት ያለባቸውን ተቋማት ክፍተት መሙላት፤ የውሀ አቅርቦት መቆራረጥን ለመቀነስ የውሀ ታንከሮችና ፓምፖችን መግጠም፣ ውሀን በከባድ መኪና (truck) ማቅረብ እንዲሁም የእጅ መታጠቢያ እጥረት ባለባቸው የለይቶ ማቆያ እና ሕክምና ማዕከላት ከእጅ ንክኪ የጸዱ በእግር መከፈት የሚችሉ ተንቀሳቃሽ የእጅ መታጠቢያዎች እንዲተከሉ ተደርጓል።

    በተጨማሪም ለሁሉም ለይቶ ማቆያ እና ሕክምና ማዕከላት የኢንፌክሽን መከላከልና መቆጣጠር ባለሙያ እና በአዲስ አበባ ለሚገኙ የለይቶ ማቆያ እና ሕክምና ማዕከላት የፀረ-ተህዋሲያን ኬሚካል ርጭት ባለሙያዎች ተመድበዋል። ለነዚህ ባለሙያዎችም የኮቪድ-19 የኢንፌክሽን መከላከልና መቆጣጠር ስልጠና የተሰጠ ሲሆን፥ ባለሙያዎቹም በአጠቃላይ የሚከናወኑ ተግባራት ኢንፌክሽንን ከመከላከልና መቆጣጠር አንጻር በአግባቡ እየተካሄዱ መሆናቸውን በየዕለቱ ይከታላሉ ብለዋል።

    በአጠቃላይ በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከሚሠሩ ሥራዎች ባሻገር ሕብረተሰቡ የሚያደርጋቸው ጥንቃቄዎች ለበሽታው ያለመስፋፋት ወሳኝ በመሆናቸው ሕብረተሰቡ ሳይዘናጋ የሚተላለፉ መልዕክቶችን እና መከላከያ መንገዶችን ተግባራዊ በማድረግ የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል።

    ለተጨማሪ መረጃ በስልክ መስመር 8335 ወይም በ952 በመደወል ወይም የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኢሜል አድራሻ ephieoc@gmail.com በመጠቀም ወይም ባሉበት ክልል በተዘጋጁ ነፃ የስልክ መስመሮች በመደወል ሪፖርት እንዲያደርጉ ወይም በአካባቢው ለሚገኙ ጤና ተቋማት በስልክ እንዲያሳውቁ ኢንስቲትዩቱ ይጠይቃል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    EPHI NDMC new website for COVID-19 ለይቶ ማቆያ ማዕከላት

    Anonymous
    Inactive

    የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የተቋቋመው “ሰው ነኝ ሌሎችንም እረዳለሁ” የተባለው ኮሚቴ፣ በመንግሥት የተቋቋመው የአማካሪ ምክር ቤት እና ኢትዮጵያ ውስጥ በሽታው የተገኘባቸው ሰዎች ያሉበት ሁኔታ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ ግለሰቦች “ሰው ነኝ ሌሎችንም እረዳለሁ” በሚል መሪ ሃሳብ የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመግታት የሚሠራ ኮሚቴ አቋቋሙ። ኮሚቴው መጋቢት 19 ቀን 2012 ዓ.ም. በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የግንዛቤ ማስጨበጥና ሌሎች የእርዳታ ማሰባሰብ ሥራዎች ላይ እንደሚሠራ ነው ያስታወቀው።

    ተነሳሽነቱን ወስዶ ኮሚቴውን ያዋቀሩት ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) የተባለው መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት መሥራችና ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ኦባንግ ሜቶ “ኮሮናቫይረስ ዘር፣ ቀለምና ሀይማኖት ሳይለይ የሰው ልጅን በስፋት እያጠቃ ይገኛል” ብለዋል።

    ኮሮናቫይረስ የተከሰተባቸው አገሮች በራሳቸው መንገድ ችግሩን ለመፍታት እየተንቀሳቀሱ መሆኑን አስታውሰው፥ ”እኛ ኢትዮጵያውያን የሌሎችን እርዳታ ሳንጠብቅ ስርጭቱን መግታት እንችላለን” ብለዋል አቶ ኦባንግ። “ይህ እውን እንዲሆን ግን ራሳችንን በመጠበቅ አንድ ሆነን መቆም ይገባል” በማለት ጨምረው አስገንዝበዋል።

    ከአካለዊ ንክኪ ርቀን በመንፈስና ተግባር አንድ ሆነን የኮሮናቫይረስ ስርጭትን መግታት ይገባናል ሲሉ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ የኮሚቴው አባላትም ተናግረዋል።

    ሙዚቀኛ ዘለቀ ገሰሰ፥  ወጣቶችን ኮሮና አይዝም የተባለውን የተሳሳተ ግንዛቤ ማሰተካከልን እና ሕብረተሰቡ ሊያውቃቸው የሚገቡ ትክክለኛ መረጃዎች በኪነ-ጥበብ ለሕዝቡ ለማድረሰ እንደሚሠራ አሰታውቋል።

    ከዚሁ ጋር በተያያዘ በጤና ሚኒስቴር የሚመራውን የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የመከላከልና የመቆጣጠር ሥራ ለማጎልበትና ለማፍጠን በጤና ሙያ ማኅበራት የተመሠረተው የአማካሪ ምክር ቤት ሥራ ጀምሯል። ውጤታማ ሥራ ለመሥራትም በስድስት ግብረ ኃይሎች የተዋቀረ ሲሆን እነሱም፦

    1. ማኅበረሰቡን ስለ በሽታው መተላለፊያና መከላከያ መንገዶች በሳይንሳዊ ዘዴ ማስተማርና ማንቃት፣
    2. ጤና ተቋማት የባለሙያውንና የታካሚውን ደኅንነት በጠበቀ መንገድ የሕክምና አገልግሎት እንዲሰጡ ማዘጋጀት፣
    3. የሕክምና መሣሪያዎች መድኃኒቶችና ግባቶች አቅርቦት እንዲሻሻል ማድረግ፣
    4. የወረርሽኝ ስርጭት ቅኝትና በሽታው ከያዛቸው ሰዎች ጋር የተገናኙ ሰዎችን ፈልጎ ማግኘት፣
    5. የወረርሽኙንመጠነስርጭት፣ማንንእንዲሚያጠቃ፣የትበብዛትእንደሚከሰት፣በጊዜሂደትያለውንለውጥናለወረርሽኙአጋላጭሁኔታዎችንማጥናትናበመረጃማጠናቀር፣እና
    6. ከወረርሽኙጋርተያይዘውየሚመጡየአዕምሮጤናእናየሥነ-ልቦናእናማኅበራዊጫናዎችንመፍታትናቸው።

    ከኮሮናቫይረስ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በሰጠው ወቅታዊ መግለጫ፥ ማንኛውም ከውጭ ሀገር ወደ ኢትዮጵያ የሚገባ መንገደኛ በሆቴል ውስጥ ለ14 ቀናት ተለይቶ እንዲቆይ በተወሰነው መሠረት እስካሁን ስድስት መቶ ሰላሳ ስድስት (636) መንገደኞች ወደ ሀገራችን የገቡ ሲሆን፥ በተመረጡ አስር ሆቴሎች ማቆያ ውስጥ ይገኛሉ።

    መንገደኞቹ ባሉባቸው ሁሉም ሆቴሎች የጤና ባለሙያዎችን በመመደብ የጤና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።

    በሌላ በኩል ከላይ የተገለፀው ውሳኔ ከመተላለፉ በፊት ከተለያዩ ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ስምንት መቶ ሰባ ሶስት (873) ሰዎች በቤታቸው ሆነው በስልክ ለ14 ቀን በጤና ባለሙያዎች የጤና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል። ከዘሁ ጋር በተያያዘ ለ14 ቀናት ክትትል ሲደረግላቸው ቆይተው የበሽታው ምልክት ያልታየባቸው ሁለት ሺ ዘጠና (2,090) ሰዎች ክትትላቸው እንዲረቋጥ ተደርጓል።

    ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ይህ መረጃ እስከተጠናከረበት ሰዓት ድረስ የኮሮናቫይረስ በሽታ ምልክት ያሳዩ ሰባ ዘጠኝ (79) ሰዎች የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገላቸው ሲሆን ሁሉም ከቫይረሱ ነፃ መሆናቸው ተረጋግጧል።

    በሀገራችን እስካሁን አሥራ ስድስት (16) ሰዎች የኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው በላቦራቶሪ ምርመራ መረጋገጡ ኢንስቲትዩቱ እና የጤና ሚኒስቴር በመግለጫዎቻቸው ማሳወቃቸውን ተዘግቧል። ከእነዚህ አሥራ ስድስት (16) ታማሚዎች መካከል ሁለቱ ወደ ሀገራቸው የተመለሱ ሲሆን አሥራ አራት (14) ታማሚዎች በለይቶ ሕክምና መስጫ ማዕከል የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛሉ። የኮሮናቫይረስ ከተገኘባቸውና የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው ከሚገኙ ታማሚዎች ውስጥ አንድ (1) ታማሚ በድጋሚ በተደረገላቸው የላብራቶሪ ምርመራ ከኮሮናቫይረስ ያገገሙ መሆናቸው የተረጋገጠ ቢሆንም ለጥንቃቄ ሲባል በለይቶ ማቆያ ለ14 ቀናት ተጨማሪ የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው የሚቆዩ ይሆናል።

    ምንጮች፦ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት/ የጤና ሚኒስቴር/ አኢጋን/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኮሮናቫይረስ

    Semonegna
    Keymaster

    ዓለምን እጅግ ያሰጋው የኖቬል ኮሮና ቫይረስ የተጠቂዎች ቁጥር እጅግ አሻቅቧል፤ ቻይና ውስጥ በአንድ ቀን ብቻ 57 በበሽታው የተጠቁ ሰዎች ሞተዋል። የተለያዩ ሀገራት ዜጎቻቸውን ከዉሃን ከተማ ማስወጣት ጀምረዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የዓለም ጤና ድርጅት የኖቭል ኖቬል ኮሮና ቫይረስ በሽታ ከታሕሳስ 21, 2012 ዓ.ም. ጀምሮ በቻይና ዉሃን (Wuhan) ግዛት የተከሰተ መሆኑን ካሳወቀ ጀምሮ ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ሰዓት ደረስ (በኢትዮጵያ ቀንና ሰዓት አቆጣጠር እስከ ጥር 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ድረስ) በአጠቃላይ 17,488 ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን፥ ከእነዚህ ውስጥ 2,298 (13%) ታማሚዎች በሽታው ክፉኛ የጸናባቸው (in critical conditions) ናቸው። እስካሁን ድረስ በሽታው የተገኘባቸው የሀገራc ቁጥር ቻይናን ጨምሮ 24 የደረሰ ሲሆን፣ በበሽታው የሞቱት ሰዎች ቁጥር 362 ደርሷል (361 የሞቱደርሷል ቻይና ውስጥ ሲሆን፣ አንዱ ብቻ ፊሊፒንስ ውስጥ ነው)። ሰኞ ጥር 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ብቻ 57 በበሽታው የተጠቁ ሰዎች ቻይና ውስጥ ሞተዋል።

    በሀገረ ቻይና እንዲሁ ቫይረሱ ለመጀመሪያ ጊዜ በተስፋፋባቸው ግዛቶች ምንም ዓይነት የመግባትና የመውጣት አንቅስቃሴ እንዳይደረግ ቢታገድም የስርጭቱ መጠን ከሚታሰበው ባላይ አሳሳቢ አየሆነ እንደመጣ ለማወቅ ተችሏል።

    ይህ መላ ዓለምን እጅግ በሚያሰጋ ሁኔታ እየተስፋፋ እየተሰጨና፣ ብሎም ቻይና ውስጥ በበሽታው የሚሞቱት ሰዎች ቁጥር እያሻቀበ ያለው ኖቬል ኮሮና ቫይረስ ወደ ቻይና የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን (በተለይም የ አየር በረራዎችን) መቆጣጠር ጀምሯል። ከችግሩ አሳሳቢነት አንፃር ብዙ ጎረቤት ሀገራት ከቻይና ጋር የሚያዋስናቸውን ድንበር ለመዝጋት የተገደዱ ሲሆን፤ ሌሎች ሃገራትም ወደቻይና የሚደረጉ ማንኛውም በረራዎችን ለማቆም እንደተገደዱ ነው። ለምሳሌ የጀርመኑ ግዙፍ አየርመንገድ ሉፍታንዛ ወደ ቻይና የሚያደርጋቸውን በረራዎች (ቢያንስ እስከ የካቲት 1 ቀን 2012 ዓ.ም.) ሙሉ ለሙሉ አቁሟል። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች (UAE) ወደ ዋና ከተማ ቤጂንግ ከሚደረጉ በረራዎች በስተቀር ሌሎች ወደ ቻይና የሚደረጉ ሁሉንም በረራዎች እንደምትሰርዝ አስታውቃለች። ካናዳ በበኩሏ ዜግቿን ኖቬል ኮሮና ቫይረስ ለመጀመሪያ ጊዜ ከተነሳባት ሁቤይ (Hubei) ግዛት ከምትገኘው ዉሃን (Wuhan) ከተማ ማስወጣት ጀምራለ፤ ሌሎች ሀገራትም ተመሳሳይ እርምጃ ለመውሰድ እንቅስቃሴ ጀምረዋል።

    ቫይረሱ በሀገራቸው በሚኖሩ ዜጎች ላይ መታያቱን ያረጋገጡት የጂ-7 (G-7) ሀገራትም (ካናዳ፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ጣልያን፣ ጃፓን፣ እንግሊዝ እና አሜሪካ) በችግሩ ላይ በትብብር በመሥራት ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን የጀርመን የጤና ሚኒስቴር ጄንስ ፋህን በትላንትናው ጥር 24 ቀን 2012 ዓ.ም. ተናግረዋል።

    ወደ ሀገራችን ስንመለስ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር እና ሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን ለኖቬል ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን ሰኞ ጥር 25 ቀን 2012 ዓ.ም. በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል። እንደመግለጫው እየተወሰዱ ካሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ውስጥ ብሔራዊ ታስክ ፎርስ እና በኢንስቲትዩቱ ለኮሮና ቫይረስ ድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ የሚሰጠው ማዕከል ሥራ ጀምረዋል። ከኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ፣ ከኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ፣ ከቦሌ አየር መንገድ፣ ከግልና ከመንግስት ጤና ተቋማት ለተውጣጡ ተሳታፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ተሰጥቷል። በተመሳሳይ ጥር 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ለ200 የሚሆኑ የሆስፒታል አመራሮች እና ባለሞያዎች በጤና ሚኒስተር አማካኝነት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል። በቦሌ ኢንተርናሽናል ኤርፖርት እና 27 የተለያዩ የድምበር መግቢያ እና መውጫ ኬላዎች ላይ የሚደረገው የማጣራት ምርመራ በተጠናከረ ሁኔታ እየቀጠለ ይገኛል። የማጣራት ምርመራው ከፍተኛ የሙቀት መጠን ያላቸውን ተጓዦች የሚለይ ሲሆን ይሄም የቫይረሱ የበሽታ ምልክት የሚያሳዩትን ለመለየት ይረዳል።

    በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ አራት ሰዎች (አንድ ቻይናዊ እና ሦስት ኢትዮጵያውያን) በኖቬል ኮሮና ቫይረስ በሽታ ተጠርጥረው፥ አንድ በአክሱም እና ሦስት በቦሌ ጨፌ በለይቶ ማቆያ ክትትል እየተደረገላቸው ሲሆን፥ ናሙናቸው ተወስዶ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመላክ ዝግጅት ተጠናቋል።

    የኖቬል ኮሮና ቫይረስ አስካሁን ድረስ ምንም አይነት ፈዋሽ መድኃኒት ወይም ክትባት ያልተገኘለት ሲሆን በዋናነት የመተንፈሻ አካላትን በማጥቃት ሰዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሞት የሚዳርግ በሽታ ነው። የኖቬል ኮሮና ቫይረስ እንደአውሮፓውያኑ በ2003 በቻይና ከተከሰተው “ሳርስ” በሽታ ጋር የመተንፈሻ አካልን በማጥቃት በኩል ተመሳሳይ ቢመስልም፤ የስርጭት መጠኑ እና የሚያደርሰው ጉዳት ግን እጅግ ከፍተኛ መሆኑ የሚለየው ጉዳይ ነው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ኖቬል ኮሮና ቫይረስ

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢፌዴሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት የማቆም አድማ ላይ የተሰማሩ የሕክምና ተማሪዎችን በተመለከተ ያወጣው መግለጫ

    በተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙ የመጨረሻ ዓመት (intern) ተማሪዎችና ስፔሻሊቲ (resident) ተማሪዎች ላነሱዋቸው የተለያዩ ጥያቄዎች ክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከሴክተሩ ባለሙያዎች እና ተማሪዎች ጋር ሲወያዩ ተማሪዎች ላነሷቸው ጥያቄዎች በሰጡት አመራር የተለያዩ እርምጃዎች ተወስደዋል።

    በዚሁ መሠረት፦

    1. የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎችን በተመለከተ የሕክምና ተማሪዎች እንደ ሌሎች ተማሪዎች የወጣባቸውን ትክክለኛ ወጪ እንዲጋሩ (cost sharing) እና ከዚህ በፊት አምስት መቶ ሺህ (500,000) ብር ይፈርሙ የነበሩት እንዲቀር መደረጉ፤
    2. የተግባር ትምህርት አተገባበርን በተመለከተ የአዳርና ለረዥም ጊዜ በሥራ ላይ መቆየት ጋር ተያይዞ የሥርዓተ ትምህርት ፍተሻ እንዲደረግና የውሳኔ ሃሳብ እንዲቀርብ፤
    3. የማስተማርያ ሆስፒታሎችን ለሥራ ምቹ ማድረግንና ተያያዥነት ያላቸውን ጥያቄዎች በተመለከተ ተቋማት ባላቸው አቅም በፍጥነት እርምጃ እንዲወስዱ እየተደረገ መሆኑን በተለያዩ አካላት መገለጫ መሰጠቱ ይታወሳል።

    በተጨማሪም እነዚህንና ሌሎች ጉዳዮችን በዝርዝር አጥንቶ ዘላቂ መፍትሔ ለመሰጠት አራት ግብረ ሃይል ተቋቁመው ወደ ሥራ ገብተዋል። ይህ እንዳለ ሆኖ በጥቂት ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርት ያቋረጡ ተማሪዎች ተስተውለዋል። ይህ በፍጹም ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ተገንዝበው ተማሪዎቹ በፍጥነት ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ እያልን ከሰኞ ግንቦት 11 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ ትምህርታቸው የማይመለሱትን ተማሪዎች ተቋማት ባላቸው የመማር ማስተማር (academic) ሕግ ቀጣይ እርምጃ እንዲወስዱ መመሪያ የተላለፈ መሆኑን እንገልጻለን።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የሕክምና ተማሪዎችን


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በአማራ ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የአተት ወረርሽኝ (acute watery diarrhea /AWD/) ምልክት መታየቱን የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ የአተት ወረርሽኙን አስመልከቶ በሰጠው መግለጫ፥ በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር እና ዋግህምራ ዞኖች በተለያዩ ወረዳዎች እየተደረጉ ባሉ የቅኝት ሥራዎች የአተት ወረርሽኝ መከሰቱ የታወቀ ሲሆን የወረርሽኙን መንስዔ ለማረጋገጥ የላብራቶሪ ምርመራ እየተካናወነ መሆኑን አስታውቋል።

    ከዚህ ጋር ተያይዞ የአንድ ታማሚ ናሙና ቫይብርዮ ኮሌራባክቴሪያ (Vibrio cholera bacteria) የተገኘበት ሲሆን ወረርሽኙን ለማረጋገጥ በተጨማሪ ናሙናዎች ላይ የላብራቶሪ ምርመራ እንደሚከናወንም ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል።

    ከሚያዝያ 27 ቀን ጀምሮ በአማራ ክልል በዋግህምራ ዞን በአበርጌሌ ወረዳ 58 ሰዎች በበሽታው የተጠረጠሩ ሲሆን በሰሜን ጎንደር ዞን በጠለምት ወረዳ 90 ሰዎች፣ በበየዳ ወረዳ ደግሞ 4 ሰዎች በበሽታው ተጠርጥረዋል።

    እንደ ኢንስቲትዩቱ መግለጫ፥ በአጠቃላይ በክልሉ በበሽታው 151 ሰዎች የተጠረጠሩ ሲሆን ሁሉም በበሽታው የተጠረጠሩ ህሙማን በአቅራቢያው ለዚህ አገልግሎት ብቻ ተብሎ በተቋቋሙ ጊዚያዊ የሕክምና ማዕከላት በቂ ሕክምና እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን፤ በጠለምት ወረዳ ግን 3 ታካሚዎች በሕክምና ላይ እያሉ ህይወታቸው አልፏል።

    በፌደራል፣ በክልልና በዞን ደረጃ ፈጣን ምላሽ ሰጪ የሕክምና ቡድን ወደ አበርጌሌ፣ ጠለምትና በየዳ ወረዳዎች ተልኮ ምላሽ በመስጠት ላይ እንደሚገኝና የዓለም ጤና ድርጅትና ድንበር የለሽ የሃኪሞች ቡድንም በቦታው በመገኘት ድጋፍ እየሰጡ መሆኑም ተገልጿል።

    ከላይ ወደተጠቀሱት ወረዳዎች አስፈላጊ የሕክምና መስጫ መሣሪያዎች፣ መድኃኒቶችና መመርመሪያዎች እንዲቀርቡ መደረጉም ነው የተጠቆመው።

    በአጎራባች ወረዳዎች ወረርሽኙ ቢከሰት በቂ ሕክምና ለመስጠት የሚያስችሉ መድኃኒቶችና የሕክምና ግብአቶች በፍጥነት ማቅረብ እንዲቻል በጎንደር፣ በደሴና በሽሬ በሚገኙ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት ኤጀንሲ መጋዘኖች እንዲከማቹ መደረጉንም ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል።

    ከዚህ ጋር ተያይዞ ሕብረተሰቡ፡ ወረርሽኙን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የመፀዳጃ ቤት በመሥራት እና በአግባቡ በመጠቀም፣ የመመገቢያ፣ የመጠጫ እና የውሃ ማስቀመጫ እቃዎችን በንጹህ ውሃ በማጠብ እና ከድኖ በማስቀመጥ ከዝንቦችና ከበካይ ነገሮች በመጠበቅ፣ ለማንኛውም አገልግሎት የሚውልን ከጉድጓድ፣ ከምንጭ፣ ከወንዝ እና ከመሳሰሉት የተቀዳ ውሃን በማከም ወይም በማፍላት በመጠቀም፣ ምግብ ከማዘጋጀት፣ ከማቅረብ፣ ከመመገብ በፊት፣ ከመፀዳጃ ቤት መልስ እና ሕፃናትን ካፀዳዱ በኋላ እጅን በመታጠብ፣ ምግብን በሚገባ አብስሎ በመመገብ፣ ከድኖ እና በንጹህ ቦታ በማስቀመጥ ከዝንቦችና ከሌሎች ነፍሳት ንክኪ በመጠበቅ ራሱንና ቤተሰቡን ከተላላፊ በሽታዎች በመከላከል የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።

    የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) ወረርሽኝ በተበከለ ውሃ ወይም ምግብ አማካይነት የሚከሰት ሲሆን ይህንንም ከሚያመጡ ተህዋሲያን መካከል ኮሌራን የሚያስከትለው ቪቢሮ ኮሌሬ የተሰኘው ባክቴሪያ ይገኝበታል።

    በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ የኮሌራ ወረርሽኝ በህንድ፣ በየመን፣ በኔፓል ፣ በካናዳ ቫንኮቨር ደሴት እንዲሁም በአህጉራችን አፍሪካ በዘጠኝ ሀገራት ማለትም በካሜሩን፣ በኬኒያ፣ በሶማሊያ፣ በሞዛምቢክ፣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮነጎ፣ በታንዛኒያ፣ በሊቢያ፣ በዙምባብዌ እና በዛምቢያ የተከሰተ ሲሆን ሀገራቱ ችግሩን ለመቅርፍ እየሰሩ ናቸው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የአተት ወረርሽኝ A WHO/UNICEF Risk Communication team member explains AWD prevention and control to health workers (PHOTO: WHO Africa)


    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ላብራቶሪ ኃላፊ እንደተናገሩት፥ የላብራቶሪ መሣሪያዎቹ በአገሪቱ የመጀመሪያ መሆናቸውን እና በጣም ጠቃሚ የሆኑ የአሚኖ አሲድ መጠኖችን ከምግብና ከደም ናሙና ላይ ለመለየት የሚያግዙ እንደሆኑ ገልጸዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከጣሊያን መንግስት ግምታቸው 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር የሆኑ የላብራቶሪ እቃዎች በእርዳታ አገኘ።

    የጣሊያን መንግስት በተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (UNIDO) አማካኝነት የለገሰው በተለያዩ ምግቦች ውስጥ የሚገኘውን የአሚኖ አሲድ መጠን የሚለኩ የአሚኖ አሲድ እና የክሩድ ፋት አናላይዘር (amino acid and crude fat analyzer) የተሰኙ የላብራቶሪ መሣሪያዎች ሲሆኑ ግምታቸው 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር ይሆናል።

    ርክከቡ በኢንስቲትዩቱ ግቢ በተከናወነበት ወቅት የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ እንዳሉት፥ በልገሳ የተገኙት የላብራቶሪ እቃዎች ኢንስቲትዩቱ ለሚያከናውናቸው ጥራት ያላቸው የምርምር ሥራዎች ወሳኝ ጥቅም እንዳላቸው ጠቅሰው፤ የኢንስቲትዩቱን ማገዝ አገሪቱ የምግብ እጥረትን ለመቀነስ የምታደርገውን ጥረት ማገዝ ነው ብለዋል።

    በተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (UNIDO) ከሃያ ዓመት በፊት ጀምሮ በተለያዩ ሥራዎች እገዛ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸው፥ የጣሊያን መንግስት በተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት በኩል ላደረገው እርዳታ ምስጋና አቅርበዋል።

    ● SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest | Video | Forum

    የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት ተወካይና የቀጣናው ዳይሬክተር ሚስ ኢውሬሊያ ፓትሬዝያ ካላብሮ ካላብሮ (Aurelia Patrizia Calabrò) እንዳሉት፥ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከአጋር ድርጅቱ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን (EFDA) ጋር በመተባበር ለሚያከናውነውና በሞሪንጋ የምግብ ጠቀሜታና ይዘት ምርምር ላይ ጠቃሚ ሥራዎችን ለመሥራት የሚያግዝ መሆኑን አመልክተዋል።

    የጣሊያን የልማትና ትብብር ኤጀንሲ (Italian Agency for Development Cooperation/ AICS) ተወካይ ፌቨን ጌታቸው በበኩላቸው ኢትዮጵያ ለጣሊያን ቅድሚያ ከሚሰጣቸው አገራት አንዷ መሆ ኗን ገልጸው፥ በግብርና፣ በጤና እና በኢንዱስትሪ መስኮች የተለያዩ የትብብር ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን አመልክተዋል። የዛሬው እገዛ በሞሪንጋ እየተሠራ ላለው ፕሮጀክት ሁለተኛው ዙር ድጋፍ መሆኑን ገልጸው ወደፊትም ትብብሩ እንደሚቀጥል አብራርተዋል።

    ከእቃዎቹ ርክክብ በኋላ የምግብ ሳይንስ እና ሥነ ምግብ ምርምር ላብራቶሪ ጉብኝት ተደርጓል። በጉብኝቱ ወቅት የኢንስቱትዩቱ ላብራቶሪ ኃላፊ አቶ መሰረት ወልደዮሐንስ በሰጡት ገለፃ መሠረት፥ የላብራቶሪ እቃዎቹ በአገሪቱ የመጀመሪያ መሆናቸውን እና በጣም ጠቃሚ የሆኑ የአሚኖ አሲድ መጠኖችን ከምግብና ከደም ናሙና ላይ ለመለየት የሚያግዙ እንደሆኑ ገልጸዋል።

    የላራቶሪ እቃዎቹ እንደ አገር በጣም ጠቃሚ መሆናቸውን አውስተው፥ ለግልም ይሁን ለመንግስት ተቋማት እንዲሁም ለዩኒቨርሲቲዎች በርካታ ድጋፍ የሚያደርጉ መሆኑን አቶ መሰረት አመልክተዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የላብራቶሪ-መሣሪያዎች

     


    Semonegna
    Keymaster

    እ.ኤ.አ ከ2019 እስከ 2023 ለሚተገበረው አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ 10 ቢሊዮን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን፥ ወጪው ከኢትዮጵያ መንግሥት፣ ከልማት አጋሮችና ባለድርሻ አካላት እንደሚሰባሰብ ለማወቅ ተችሏል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – በኢትዮጵያ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ተግባራዊ የሚሆን አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች በተገኙበት ዛሬ ይፋ ሆነ።

    በዚህ ወቅት እንደተገለጸው፥ አገሪቷ መከላከልን መሠረት ያደረገ ስልት ቀይሳ የምታደርገውን ጥረት በጉልህ ይደግፋል። በተለይም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ አካባቢዎች በተፈጠሩ አለመረጋጋት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ተላላፊ ለሆኑ በሽታዎች እንዳይጋለጡ አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችል ነው።

    እ.ኤ.አ ከ2019 እስከ 2023 ለሚተገበረው አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ 10 ቢሊዮን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን፥ ወጪው ከኢትዮጵያ መንግሥት፣ ከልማት አጋሮችና ባለድርሻ አካላት እንደሚሰባሰብ ለማወቅ ተችሏል።

    የጤና ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን እንደተናገሩት፥ በዕቅድ ዝግጅቱ የሚመለከታቸው መሥሪያ ቤቶች ተሳትፎ አድርገዋል።

    አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ ችገሮች ከመከሰታቸው በፊት አስቀድሞ በመለየት መከላከል፣ ችግሮች ሲከሰቱ ፈጣን ምላሽ መስጠት በኅብረተሰቡ ላይ በህመምና በሞት የከፋ ጉዳት ሳይደርስ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ስትራቴጂ ነው።

    ◌ SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest

    ባለፉት ሁለት ዓመታት የጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵይ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) ጋር በመሆን ዕቅዱን ዝግጅት ሲደረግ እንደነበረ ዶ/ር አሚር ገልጸው፥ አገሪቷ በዘርፉ ምን ክፍተት አለባት? የሚለውን በጥናት ላይ የተመሰረተ ሥራ መከናወኑን አስረድተዋል። እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፥ ዕቅዱ ከመዘጋጀቱ በፊት አገር አቀፍ የዳሰሳ ጥናት ተካሂዷል።

    ዶ/ር አሚር እንደሚሉት፥ በጥናቱ መሠረት ዝቅተኛ አፈጻጸም የታየበት አደጋ ሲከሰት ፈጣን ምላሽ መስጠት መሆኑ የተለየ ሲሆን ችግሩን ለመፍታት በሁለቱ ከተማ መስተዳደሮችና በዘጠኙ ክልሎች ማዕከላት ተቋቁሟል።

    ከኬሚካልና ጨረር ጋር በተያያዘ አደጋ ቢያጋጥም ምላሽ ለመስጠት በቂ ዝግጅት እንደሌለ በጥናት የተለየ ሌላው ችግር መሆኑን ጠቁመው በዚህም ላይ የማስተካከያ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አብራርተዋል።

    በዕቅዱ ላይ እንደ ክፍተት የተቀመጡ ችግሮችን ለመፍታት መንግሥት 25 ሚሊዮን ዶላር በመመደብ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጸዋል።

    የኢትዮጵይ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኤባ አባተ በበኩላቸው፥ አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅዱ በአገሪቷ ተላላፊ በሽታዎችና ወረርሽኝን አስቀድሞ ለመግታት ወሳኝ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።

    ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በዚሁ ወቅት እንደገለጹትዕ አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅዱ ወቅታዊና አስፈላጊ ነው። አደጋዎችን ቀድሞ የመከላከል፣ ብዙ ጉዳት ሳያደርሱ የመቆጣጠርና መልሶ የማገገምና እንዳይደገም የማድረግን አቅምን መገንባት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አገራዊ የጤና ደህንነት የትግበራ ዕቅድ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰቡን ዘርፈ ብዙ የጤና ችግሮች ለመፍታት በሚደረገው ጥረት ባለድርሻ አካላት በመናበብ እና አቅማቸውን ይበልጥ አጠናክረው መሥራት እንዳለባቸው ተገለጸ።

    የኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ማዕከል የስድስት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ከየካቲት 18 እስከ 21 ቀን 2011 ዓ.ም. በኢንስቲትዩቱ አዳራሽ ተካሂዷል።

    የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማው ዋና ዓላማ በሃገር አቀፍ ደረጃ የሕብረተሰብ ጤናን ከማስጠበቅ አንጻር የተሠሩትን በርካታ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ከዕቅድ አኳያ ምን ያክሉን ማሳካት እንደተቻለ፥ በመቀጠልም የታዩ ክፍተቶችን በመለየት በቀጣይ የተሻሉ ዘዴዎችን በመቀየስ ችግሮቹን ለማስወገድ ታስቦ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ነበር።

    የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኤባ አባተ በመክፈቻ ሥነ-ስርዓቱ ወቅት እንደገለጹት አጠቃላይ የሕብረተሰቡን ጤና አደጋዎች ለመከላከልና ለመቆጣጠር ይቻል ዘንድ ከፌዴራል ጀምሮ እስከ ታችኛው የሕብረተሰብ ክፍል ያለው አስተዳደራዊ መዋቅር ሰንሰለቱን ጠብቆ ጠንካራ የሆነ መስተጋብር ሊፈጥር ይገባል፤ በመሆኑም የክልል ጤና ቢሮዎች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በጤናው ዘርፍ በቅንጅት እየሠሩ የሚገኙ ሲሆን፥ ይህ መድረክ በዚህ የግማሽ ዓመት የሕብረተሰቡን ጤና ችግሮች ከመፍታት አንጻር የታዩ ጠንካራ ሥራዎች እና ድክመቶችን በመለየት በቀጣይ ለሚሠሩ ተግባራት ላይ የጋራ መግባባት የሚደረስበት በመድረክ ነው ብለዋል።

    ዶ/ር በየነ ሞገስ የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር በበኩላቸው እንደሀገር ከሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር አንጻር እየሠራን ነው፣ ምን ላይስ እንገኛለን፣ በዚህ ግማሽ ዓመት ምን ዋና ዋና ውጤቶች ተመዝግበዋል የሚሉትን በመፈተሽ በቀጣይ ችግር ፈቺ የሆኑ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የጋራ መግባባት የሚደረስበት መድረክ ነው የተዘጋጀው ሲሉ ተናግረዋል።

    የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ማዕከል ከዕቅድ አንጻር በግማሽ ዓመቱ ያከናወናቸውን ተግባራት፣ በመቶ ቀናት ውስጥ የታቀዱ ተግባራት፣ የነበሩ ጠንካራና አፈፃፀሞችና የነበሩ ክፍተቶች እንዲሁም የነበሩ ስጋቶች፣ ተይዞ የነበረው የበጀት አፈጻጸም፣ ዓለም አቀፍና አገር አቀፍ በሽታዎች ከዕቅድ አንጻር ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙ፣ ሀገራዊ የጤና ደህንነት እቅድ፣ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ስጋቶች፣ ተጋላጭነትና ምላሽ ዳሰሳ ጥናት በግምገማ መድረኩ ላይ በዝርዝርና በስፋት ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

    የጤና ሚኒስቴር እና በስሩ የሚገኙ መሥሪያ ቤቶች፣ የኢንስቲትዩቱ የበላይ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች፣ የክልል ጤና ቢሮዎች፣ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር የሥራ ሂደት ኃላፊዎች፣ የዕቅድ ክትትል እና ምዘና ኃላፊዎች እንዲሁም የእናቶችና ህፃናት ቡድን መሪዎች በውይይትና ግምገማ መድረኩ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት / ሰሞነኛ ኢትዮጵ

    የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት


Viewing 11 results - 1 through 11 (of 11 total)