ከመጣንበት መንገድ በላይ የሚቀረን ይከብዳል!! (ለኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች)

Home Forums Semonegna Stories ከመጣንበት መንገድ በላይ የሚቀረን ይከብዳል!! (ለኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች)

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #11132
    Anonymous
    Inactive

    ኢትዮጵያ ቡና ከመቐለ 70 እንደርታ ባዶ ለባዶ ተለያዩ
    —–

    አዲስ አበባ – በኢትዮጵያ ወንዶች ፕሪምየር ሊግ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ኢትዮጵያ ቡና እና መቐለ 70 እንደርታ ሰኔ 11 ቀን 2011 ዓ.ም. ያደረጉት ጨዋታ ባዶ ለባዶ ተጠናቋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ የተደረገው 27ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ ያለምንም ግብ በሰላም ተጠናቋል።

    መቐለ 70 እንደርታ ዛሬ ያለምንም ግብ አቻ መለያየቱን ተከትሎ ሊጉን በ52 ነጥብ እየመራ ከለው ፋሲል ከነማን ተከትሎ በ50 ነጥብ በሁለተኛ ደረጃ ተቀምጧል። በ34 ነጥብ በሊጉ 11ኛ ደረጃ ተቀምጦ የነበረው ኢትዮጵያ ቡና በበኩሉ ነጥቡን ወደ 35 በማሳደግ በሊጉ ያለዉን ደረጃ ወደ 9ኛ ከፍ ማድረግ ችሏል።

    የፕሪምየር ሊጉ 28ኛ ሳምንት ቀጣይ መርሃ ግብር የፊታችን ቅዳሜና እሁድ የሚቀጥል ሲሆን ቅዳሜ ጅማ አባጅፋር ከኢትዮጵያ ቡና፣ ሀዋሳ ከተማ ከመከለከያ፣ ስሁል ሽሬ ከደደቢት፣ ባህር ዳር ከተማ ከወላይታ ድቻ ጋር ይጫወታሉ።

    እሁድ ሰኔ 16 ቀን 2011 ዓ.ም. የፕሪሚየር ሊጉ መሪ ፋሲል ከነማ ከሜዳው ዉጭ ከአዳማ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ፣ ሲዳማ ቡና ከድሬደዋ፣ መቐለ 70 እንደርታ በጥሎ ማለፉ ከደቡብ ፖሊስ ጋር እንደሚጫወቱ ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.