ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተመረጡ

Home Forums Semonegna Stories ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተመረጡ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8342
    Semonegna
    Keymaster

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አድርገው መረጡ። ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር መሥራች ናቸው።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ጥቅምት 22 ቀን 2011 ዓ.ም በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ሹመትን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አድርገው መርጠዋቸዋል።

    የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 5ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 4ኛ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ይካሄዳል። በስብሰባው በሕገ መንግስቱ አንቀጽ 81 ንዑስ አንቀጽ 1 መሰረት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚያቀርቡትን የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እጩ ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት ሹመት መርምሮ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል። ስለዚህ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምርጫ ያቀረቧቸው ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሆነው ይሾማሉ ተብሎ ይጠበቃል።

    በአሁኑ ወቅት ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው እያገለገሉ ያሉት አቶ ዳኜ መላኩ እና አቶ ጸጋዬ አስማማው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሾሙት ሰኔ 16 ቀን 2008 ዓ.ም ነበር።

    ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ማን ናቸው?

    ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ  በ1985 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት ኮሚሽን የሕግ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል። በ1987 ዓ.ም. የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበርን (Ethiopian Women Lawyers Association/ EWLA) ከሌሎች የሕግ ባለሙያ ሴቶች ጋር በመሆን አቋቁመው በ1988 ዓ.ም. ማኅበሩ በይፋ ሥራ ጀመረ። በዚያም ጊዜ ወ/ሮ መዓዛ የማኅበሩ ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እስከ 1997 ዓ.ም. ድረስ ሠርተዋል።

    ወ/ሮ መዓዛ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምጣኔ ሀብት ኮሚሽን ለአፍሪካ (United Nations Economic Commission for Africa) የተባለው ዓለም-አቅፍ ድርጅትን በ2003 ዓ.ም. በመቀላቀል፥ በዚሁ ድርጅት ውስጥ ከሰኔ ወር 2004 ዓ.ም. ጀምሮ የሴቶች መብት አማካሪ ሆነው ሠርተዋል።

    ከሕግ ባለሙያነታቸው በተጨማሪ በ2003 ዓም ኢትዮጵያ ውስጥ በ13 ጠንካራ ኢትዮጵያውያን ሴቶች ተደራጅነት የተቋቋመው እናት ባንክ (አ/ማ) ሲመሠረት ከመሥራችቹ ውስጥ ጉልህ ሚና የተጫወቱ አባል ነበሩ። ባንኩ ውስጥም ከአራት ዓመታት በላይ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል ሆነው አገልግለዋል።

    ኢትዮጵያ ውስጥ ለሴቶች እኩልነትና ለሴቶች መብት በመታገል ላደረጉት አንጸባራቂ ውጤት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ በህዳር ወር 1996 ዓ.ም ‘የሀንገር ፕሮጀክት ሽልማት’ (Hunger Project Award) የአፍሪካ ተሸላሚ ሆነዋል። ከዚያም ቀጥሎ (ከሁለት ዓመት በኋላ) የኖቤል የሰላም ሽልማት ዕጩ ሆነው ሊቀርቡ ችለዋል።

    በ2006 ዓ.ም. ዘረሰናይ ታደሰ ተደርሶ የተዘጋጀው (ዳይሬክት የተደረገው) “ድፍረት” የተሰኘውና በዓለም አቀፍ ደረጃ መልካም ተቀብይነትን ያገኘው ፊቸር ፊልም (feature film) ሂሩት አሰፋ የተባለች አንዲት የ14 ዓመት ልጃገረድ ኢፍትሀዊ በሆነ ባህል የሞት ፍርድ ተፈርዶባት ከዚያም የሕግ ባለሙያ (ጠበቃ) የሆነችውን ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊን አግኝታ የሚሆነውን የሚተርክ እንደሆነ ይታወሳል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    መዓዛ አሸናፊ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.