የኢትዮጵያ የምግብ፣ የመድኃኒት እና ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን አገልግሎቱን በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዘመኑን ይፋ አደረገ
—–
የኢትዮጵያ የምግብ፣ የመድኃኒት እና ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን የምግብና መድኃኒት ፈቃድ አሰጣጥ፣ የመድሃኒት ግዢ ፈቃድ፣ የምግብና መድኃኒት የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ አሰጣጥን ቀልጣፋና ግልፅ የሚያደርግ ዘመናዊ አሰራርን መተግበር ጀምሬያለሁ ብሏል፡፡ዛሬ በሒልተን ሆቴል በተካሄደው የአገልግሎቱ ማስታወቂያ መርሃ ግብር ተገኝተን እንደሰማነው እስካሁን በማኑዋል የነበረው የተቋሙ አሰራር በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ታግዞ የተሻለ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡
eRIS የተባለው ኤሌክትሮኒክ የቁጥጥርና የመረጃ ስርዓት ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ የምግብና የመድኃኒት ምርቶችን ደህንነት የማረጋገጥ ስራውን የሚያሻሽል ነው ተብሏል፡፡የምዝገባ ሥርዓቱን ማዘመን የመድሃኒት አቅርቦት እጥረትን ለመቀነስ ያስችላል የሚል ተስፋም ተጥሎበታል ተብሏል፡፡ የካቲት 20 ቀን 2011 ዓም ይፋ የተደረገው ዘመናዊ አሠራር በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፀደቀው የምግብና መድሃኒት ቁጥጥር አዋጅ አንድ አካል መሆኑንም ሸገረ ኤፍ ኤም ራድዮ ዘግቧል፡፡
ምንጭ፦ ሸገረ ኤፍ ኤም ራድዮ