ብርሃን ባንክ የ10ኛ ዓመት የምሥረታ ክብረ በዓሉን በደማቅ ሁኔታ አከበረ

Home Forums Semonegna Stories ብርሃን ባንክ የ10ኛ ዓመት የምሥረታ ክብረ በዓሉን በደማቅ ሁኔታ አከበረ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #12833
    Semonegna
    Keymaster

    ብርሃን ባንክ የ10ኛ ዓመት የምሥረታ ክብረ በዓሉን ሲያከብር ለኢትዮጵያ ልብ ህሙማን ሕፃናት መርጃ ድርጅት የ3 ሚሊዮን ብር እንዲሁም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የአጥንት ህክምና ክፍል የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ብርሃን ባንክ የ10ኛ ዓመት የምሥረታ ክብረ በዓሉን ህዳር 16 ቀን 2012 ዓ.ም. በተለያዩ ሥነ-ሥርዓቶች በስካይላይት ሆቴል በደማቅ ሁኔታ አክብሯል። በዝግጅቱ ባንኩ ለአገልሎት ክፍት ከሆነበት ከከፈረንጆች ጥቅምት (October) ወር 2009 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ዛሬ ያሉ የተለያዩ ዋነኛ ስኬቶቹን በማወደስ፣ የወደፊት ጊዜያትን ደግሞ በጠንካራ አቅም ሊጓዝ እንዳቀደ ነው ያስረዳው። የእለቱ ዝግጅት በሦስት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያነጣጠረ ሆኖ በተለያዩ መርሃግብሮች በስኬት ተጠናቅቋል።

    ከተለያዩ የህትመት እና ኤሌክተሮኒክስ ሚዲያ ተቋማት ተጋብዘው በቀረቡ የሚዲያ አካላት በተዘጋጀው የባንኩ የዲሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ እና የባንኩ ፕሬዚዳንት በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ እስከ 11፡45 ድረስ ተከናውኗል። በማስከተልም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ወንበሮቻቸውን እንደያዙ በመድረኩ ላይ በእውቅ የሙዚቃ ተጫዋቾች አማካኝነት ድንቅ የሆነ የቫዮሊን የሙዚቃ ኮንሰርት ለታዳሚያኑ ቀርቧል። ይህንንም ተከትሎ በአርቲስት ሃረገወይን አሠፋ የመድረክ አጋፋሪነት ለእንግዶቹ የሚቀርበው የአዳራሽ ውስጥ ዝግጅቱ በይፋ ተጀመረ። አርቲስት ሃረገወይን የባንኩን የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ካቀረበች እና አጠር ያለ የ10 ዓመታት የባንኩን የአመሰራረት አፅመ ታሪክ በአጭሩ አቅርባ መድረኩን እንዲረከቧት እና የእለቱን የክብር እንግዶች ወደ መድረክ እንዲጋብዙ የባንኩን ፕሬዚዳንት አቶ አብሃም አላሮን ወደ መድረኩ ጋበዘች።

    የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አብሃም አላሮ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት እንዲያስተላልፉ የብሔራዊ ባንክ ገዥ የሆኑትን ይናገር ደሴ (ዶ/ር) ወደ መድረክ ጋብዘው ገዥው ባንኩ በርካታ ባለአክሲዮኖችን በመያዝ ቀዳሚው የንግድ ባንክ መሆኑን ገልፀው ለመላው የባንኩ ማህበረሰብ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አቅርበዋል። በማስከተልም የቀረበው የባንኩ የዲሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጉማቸው ኩሴ የእንኳን አደረሳችሁ እና እንኳን ደስ ያላችሁ መልክት ሲሆን፥ ሰብሳቢው በመልዕከታቸው የባንኩን ስኬቶች በማወደስ ቀጣይ ሥራዎችን በተሻለ አቅም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ እምነታቸውን ገልፀዋል። ይህ ዝግጅት እንዲህ ባለው መልኩ ቀጥሎ በባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አብርሃም አላሮ አጠር ያለ የኢትዮጵያ ባንኮችን ታሪክ እና እድገት እንዲሁም ብርሃን ባንክ በ10 ዓመታት ዕድሜው ያሳየውን የአፈፃፀም ጉዞን የሚያሳይ ጥናት ቀርቧል። ፕሬዚዳንቱ ባንኩ ከምሥረታው ጀምሮ በተለያዩ ልኬቶች ያስመዘገባቸው ስኬቶቹ እጅግ አመርቂ እና ፍሬያማ የሚባሉ መሆናቸውን አብራርተው በቀጣይም እነኚህ ስኬቶቹ በላቀ መልኩ አሸብርቀው እንደሚቀጥሉ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።

    በማስከተል የቀረበው ለባንኩ መመሥረት እንዲሁም በተለያዩ መንገዶች ባንኩን ከምሥረታው ጀምሮ ላገዙ መሥራቾች፣ አመራሮች እንዲሁም ላለፉት አስር ዓመታት በባንኩ ላገለገሉ ሠራተኞች የእውቅና እና የምስጋና ስጦታዎችን የማበርከት ሥነ-ሥርዓት ነበር። ከምስጋና የምስክር ወረቀት (certificate) ጀምሮ 13 ሠራተኞቹን ጨምሮ ለተለያዩ ባለድርሻዎች በወርቅ በተሠሩ ስጦታዎች ተበርክቶላቸዋል። ይህንኑ መርሀ ግብር ተከትሎ ብርሃን ባንክ ለኢትዮጵያ ልብ ህሙማን ሕፃናት መርጃ ድርጅት የ3 ሚሊዮን ብር እንዲሁም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የአጥንት ህክምና ክፍል 2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል። ይህንኑ ስጦታ የማዕከላቱ ተጠሪዎች ዶክተር ሄለን በፈቃዱ (የልብ ሕሙማን ህፃናት ድርጅትን በመወከል) እና ዶክተር ብሩክ ላምቢሶ (የአጥንት ህክምና ክፍልን በመወከል) ከባንኩ የዲሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ እጅ ተቀብለዋል። ይሀንን ስጦታ ሲቀበሉም ድጋፉ በሚደረግላቸው እና የህክምና ወጪዎቻቸውን መሸፈን በማይችሉ አቅመ ደካማ ህፃናት እና አረጋውያን ስም አመስገነው ገንዘቡን ሙሉ በሙሉ ለታለመለት ዓላማ እንደሚያውሉ ከምስጋና ጋር ቃል ገብተዋል።

    በዝግጅቱ መጨረሻ ላይም የባንኩ ቀጣይ የንግድ ምልክት ወይም መለያ ምልክት ሆኖ የሚያገለግለውን አዲስ አርማ ለታዳሚያን ተዋውቆ የዕለቱ ዝግጅት በእራት መርሀ ግብር በደማቅ ሁኔታ ተገባዷል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ብርሃን ባንክ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.