ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ከግብር በፊት ባንኩ ያገኘው ትርፍ 658.75 ሚሊዮን ብር ማግኘቱን አሳወቀ

Home Forums Semonegna Stories ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ከግብር በፊት ባንኩ ያገኘው ትርፍ 658.75 ሚሊዮን ብር ማግኘቱን አሳወቀ

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • Author
    Posts
  • #8941
    Semonegna
    Keymaster

    ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ከግብር በፊት ያገኘው ትርፍ ብር 658.75 ሚሊዮን ሲሆን ይህም ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ተመዝግቦ ከነበረው ትርፍ ጋር ሲነጻጸር 13.97 ሚሊዮን ወይም 2.2 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እውቅና ካገኙ የግል ባንኮች መካከል አንዱ የሆነው ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ 19ኛ መደበኛና 17ኛ ድንገተኛ የባለአክስዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ ኅዳር 22 ቀን 2011 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ አካሄደ።

    በጉባኤው ላይ በቀረበው የዳይሬክተሮች ቦርድ ሪፖርት መሠረት፥ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ የባንኩ አጠቃላይ ሀብት ብር 26.7 ቢሊዮን ደርሷል። ይህም ባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ከነበረው ብር 21.1 ቢሊዮን ጋር ሲነጻጸር የ26.4 በመቶ ዕድገት ያሳየ ሲሆን፣ ባንኩ ቀጣይነትና ዘላቂነት ያለው ዕድገት ማስመዝገብ መቀጠሉን ያመለክታል።

    ከግብር በፊት ባንኩ ያገኘው ትርፍ ብር 658.75 ሚሊዮን ሲሆን ይህም ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ተመዝግቦ ከነበረው ትርፍ ጋር ሲነጻጸር 13.97 ሚሊዮን ወይም 2.2 በመቶ ዕድገት አሳይቷል። በበጀት ዓመቱ መጨረሻ የባንኩ አጠቃላይ ሀብት ብር 26.7 ቢሊዮን በማድረስ ባለፈው ዓመት ከነበረው ብር 21.1 ቢሊዮን ጋር ሲነጻጸር የ26.4 በመቶ ዕድገት አሳይቷል። በ2010 የበጀት ዓመት መጨረሻ ላይ የባንኩ አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ መጠን ብር 21.6 ቢሊዮን ደርሷል። ይህም አሃዝ ካለፈው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የብር 5.1 ቢሊዮን ወይም የ30.6 በመቶ ዕድገት የሚያሳይ ነው።

    Nib International Bank announces 658.7 million birr pre-tax profit in the fiscal year

    በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ብድር የወሰዱ 541 ደንበኞችን ጨምሮ እስካሁን ወደ 11,626 የሚሆኑ ደንበኞች በተለያዩ ወቅቶች ለተለያዩ ዓላማዎች የብድር ተጠቃሚ ሆነዋል። በዚሁ መሠረት በ2010 በጀት ዓመት የባንኩ የብድር መጠን ወደ ብር 13.5 ቢሊዮን ያደገ ሲሆን ይህም አሃዝ ካለፈው ዓመት ተመመሣሣይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የብር 2.8 ቢሊዮን ወይም 26.5 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።

    በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የባንኩ አጠቃላይ ካፒታል ብር 3.4 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን ይህ አሃዝ ካለፈው ዓመት ተመሣሣይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የብር 414.5 ሚሊዮን ወይም የ14 በመቶ ዕድገት አሳይቷል። በበጀት ዓመቱ የባንኩ የተመዘገበ/የተፈረመ ካፒታል ብር 2.2 ቢሊዮን፣ የተከፈለ ካፒታል ደግሞ ብር 2.2 ቢሊዮን ደርሷል።

    ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ያለውን ጠንካራ መሠረት ለመጠበቅ እንዲቻል የባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት፣ አራት ኪሎ የሚገኘው፣ በሆሳዕናና በሐዋሣ ከተሞች የሚገኙት ሕንጻዎች የግንባታ ሥራ በማፋጠን ላይ ሲሆን፤ በወልቂጤና በዱከም ከተሞች አስገንብቶ ያስመረቃቸው ሕንፃዎችም የተለያዩ አገልግሎቶችን ለመስጠት በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛሉ። የባንኩ ቋሚ ንብረት በባለፈው ዓመት ከነበረበት ብር 495.6 ሚሊዮን ወደ ብር 1.9 ቢሊዮን ማደጉንም በስብሰባው ላይ ተገልጿል።

    ምንጭ፦ NibBankSC.com
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ


    #9047
    Anonymous
    Inactive

    ብርሃን ኢንሹራንስ ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ትርፍ አስመዘገበ

    ኩባንያው ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት በዕቅድ ከተያዘው 17 ሚሊዮን ብር የትርፍ መጠን አንፃር ሲታይ ከዕቅድ በላይ ትርፍ አስመዝግቧል፡፡ ኩባንያው በ2009 ዓ.ም. 9.6 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ አስመዝግቦ ነበር፡፡ የ2010 ዓ.ም. ትርፉ ከካቻምናው ሲነፃፀር የ115 በመቶ ዕድገት እንደታየበት አስታውቋል፡፡

    በ2010 ዓ.ም. የኩባንያው ዓመታዊ የተመዘገበ የገቢ መጠንም ወደ 104.3 ሚሊዮን ብር ከፍ በማለቱ ከካቻምናው አኳያ መጠነኛ ለውጥ በማሳየት የአምስት በመቶ ጭማሪ አስተናግዷል፡፡ ከጠቅላላው የዓረቦን መጠን ውስጥ የተሽከርካሪ ኢንሹራንስ የአንበሳውን ድርሻ በመያዝ 59 በመቶ፣ በገንዘብ ሲሰላም የ61.3 ሚሊዮን ብር ድርሻ ይዟል፡፡ የገንዘብ ነክ ኢንሹራንስ 16 በመቶ ወይም 16.4 ሚሊዮን ብር በማስመዝገብ በሁለተኛ ደረጃ ይከተላል፡፡

    በሒሳብ ዓመቱ የቀረቡ የጉዳት ካሳ ጥያቄዎችን በተመለከተ ኩባንያው 66.6 ሚሊዮን ብር የነበረ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥም 50.1 በመቶ የሚሆነው ክፍያ ተፈጽሟል፡፡ ከአጠቃላይ የካሳ ክፍያ ጥያቄዎች ውስጥ 43.5 ሚሊዮን ብር ወይም 65 በመቶ የሚሆነው የተመዘገበው በተሽከርካሪ ኢንሹራንስ እንደነበር ያመለክታል፡፡

    Read more: https://bit.ly/2PXgDuf

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.