በአማራ ክልል ከ450 ሺህ ለሚበልጡ ልጃገረዶች የማህፀን ጫፍ ካንሰር መከላከያ ክትባት ሊሰጥ ነው

Home Forums Semonegna Stories በአማራ ክልል ከ450 ሺህ ለሚበልጡ ልጃገረዶች የማህፀን ጫፍ ካንሰር መከላከያ ክትባት ሊሰጥ ነው

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8050
    Semonegna
    Keymaster

    የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት የሚሰጥበት ጊዜ ተራዘመ

    የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት የሚሰጥበት ቀን መራዘሙን የአማራ ክልል ጤና ጥበቃ ቢሮ አስታወቀ።

    ክትባቱ በኢትዮጵያ በሁሉም ክልሎች በጥቅምት ወር እና ከስድስት ወራት በኋላ ደግሞ ለሁለተኛ ዙር ሊሰጥ ታቅዶ ነበር። በቢሮው የክትባት መርሃ ግብር የቴክኒክ አማካሪ አቶ ሙሉጌታ አድማሱ እንደገለፁት ለክትባት የሚሆነው መድሃኒት በመዘግየቱ ምክንያት ክትባት የሚሰጥበት ቀን ወደ ህዳር 5/2011 ዓ.ም ተራዝሟል።

    በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚሰጠው የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት ዉጤታማነት በአማራ ክልል በሁሉም ዞኖች እና ወረዳዎች ለጤና ባለሙያዎች ስልጠና መሰጠቱንም አቶ ሙሉጌታ ነግረውናል። ከጤና ጥበቃ ቢሮ ያገኘነው መረጃ እንደሚያሳየው በክልሉ ከ4 መቶ 50 ሺህ በላይ ልጃገረዶች ክትባቱን ይወስዳሉ። እድሜያቸው 14 ዓመት የሆናቸው ልጃገረዶች ብቻ የክትባቱ ተጠቃሚ እንደሚሆኑም ለማወቅ ተችሏል።

    የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት እድሜያቸው ከ9 እስከ 14 ዓመት የሆናቸው ልጃገረዶችን የግብረ ስጋ ግንኙነት ከመፈጸማቸው በፊት ከበሽታው ለመከላከል ሲባል በዓለማቀፍ ደረጃ ይሰጣል። ይሁን እንጅ በኢትዮጵያ ደረጃ ለሁሉም ልጃገረዶች የሚበቃ መድኃኒት ገዝቶ ማቅረብ ባለመቻሉ ለበሽታው ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑት ላይ ክትባቱ እንደሚሰጥ ጤና ጥበቃ ቢሮው ገልጿል።

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.