ፖለቲካውን ከክረት በማላቀቅ ሀገሪቱን ከውጥረት ለማውጣት የበኩላችንን ለመወጣት ዝግጁ ነን – ዶክተር አምባቸው መኮንን
—–
ፖለቲካውን ከክረት በማላቀቅ ሀገሪቱን ከውጥረት በማውጣት አስተማማኝ ሰላም የሰፈነባት፤ ዜጎቿ በሙሉ ነፃነት የሚንቀሳቀሱባት ለማድረግ የበኩላችንን ለመወጣት ዝግጁ ነን አሉ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር ዶክተር አምባቸው መኮንን።
ዛሬ በክልሉ ምክር ቤት ርእሰ መስተዳደር በመሆን የተሾሙት ዶክተር አምባቸው ቃለ መሃላ ከፈፀሙ በኋላ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት ንግግር የአማራ ህዝቦችን የማስተዳደር ሀላፊነት ስለ ተሰጣቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።
አዲሱ ርዕሰ መስተዳደር በንግግራቸው በክልሉ በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ቀደም ሲል የተከናወኑ ስራዎች እንዳሉ ሆኖ በቀጣይ ግን የማስተካከያ ስራ የሚፈልጉ እንደ መንገድና መብራትን የመሰሉ የመሰረተ ልማት ስራዎች ክፍተቶች እንዳሉ ጠቁመዋል።
በክልሉ ርብርብ የሚፈልጉ የህዝብ የመልማት ፍላጎት እንዳለም በማንሳት፥ ያሉትን አወንታዊ እና አሉታዊ ሁኔታዎችን በመገምገም ፈጣን ስምሪት እንደሚከናወን ነው የጠቆሙት።
የክልሉ መንግስት በቀጣይ ትኩረት የሚያደርግባቸውን ጉዳዮችም በዝርዝር ያስቀመጡ ሲሆን፥ ጠንካራ መንግስታዊ መዋቅር በየደረጃው መዘርጋቱን በማረጋገጥ ጠንካራ የለውጥ አመራር መገንባት አንዱ መሆኑን አንስተዋል።
ሙሉውን ፋና ላይ ያንብቡ