በ60 ሚሊዮን ብር የተገነባው የመደ ወላቡ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በይፋ ተመረቀ
—–
በባሌ ዞን በመደ ወላቡ ወረዳ በ60 ሚሊዮን ብር የተገነባው የመደ ወላቡ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ባሳለፍነው ሳምንት በይፋ ተመርቋል።
ሆስፒታሉን በይፋ የመረቁት የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ናቸው፡፡
ኤክስ ሬይን ጀምሮ በርካታ የህክምና ቁሳቁሶችን ያሟላው ሆስፒታል ለ150 ሺህ የአካባቢው ነዋሪዎች አገልግሎት መስጠት ይችላል ሲል የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቧል።
በ2005 ዓ.ም. ግንባታው የተጀመረው ሆስፒታሉ በ2009 ዓ.ም. በከፊል ተጠናቆ ሥራ እንደጀመረ በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ ተገልጿል።
ምንጭ፦የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን