አልተማረም እንዳትለው ዋሽንግተን በሚገኝ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ገብቶ ዲግሪ ጭኖ የወጣ እሳት የላሰ ምሁር ነው።
ፈሪ ነው እንዳትለው ሁሉም በፍርሀት በተሸበበት በዚያ ዘመን “ምኒልክ” የሚባል ስሙ እንደ ነበልባል የሚፋጅ ጋዜጣ አቋቁሞ የመለስ ዜናዊን አስተዳደር ሲያርበደብድ የኖረ ሰው ነው።
ታስሮ ዝነኛ መሆን ፈልጓል እንዳትለው የአሁን ባለስልጣኖች እየዞሩ ለእነ አቦይ ስብሀት በሚያሸረግዱበት ዘመን እሱ ከአንድም ዘጠኝ ግዜ ጨለማ ቤት ውስጥ ታስሮ በፅናት የኖረ ፅኑ ሰው ነው።
ታዋቂ መሆን ይፈልጋል እንዳትለው እስር ቤት ቁጭ ብሎ ከአራት በላይ አለም አቀፍ ሽልማትችን የተቀበለ ተአምረኛ ሰው ነው።
የደሀ ልጅ ነው እንዳትለው መሀል አዲስ አበባ ላይ ስንት ንብረት ያለው ልጥጥ ያለ የልጥጥ ሀብታም ልጅ ነው።
ተስፋ ቆርጧል እንዳትለው አሁንም ደረቱን ነፍቶ ትግሌን እቀጥላለው ይልሀል። እንግዲህ ይህን እስክንድር የተባለን ክስተት ከአንድ ተራ ካድሬ ጋር ሲያወዳድሩት ከማየት በላይ ምን የሚያሸማቅቅ ነገር አለ?! አቤቱ ይቅር በለን!!!
[Dagmawi Dagmawi]