አቶ አዲሱ አረጋ፥ ያ’ኔ!

Home Forums Semonegna Stories አቶ አዲሱ አረጋ፥ ያ’ኔ!

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #11158
    Anonymous
    Inactive

    አቶ አዲሱ አረጋ የዛሬ ሁለት ዓመት፥ ሕዝባዊ እንቢተኝነቱ እንዳይቀጥል “አይደገምም” በማለት ታሳሪዎችን በማስተማር¡¡ የተጀመረው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ኒዮሊበራሎች በአገራችን “የቀለም አብዮት” ለማስነሳት እንደሆነ፣ የተፈጠውን የመልካም አስተዳደር ችግር ለመፍታት ጥረት እየተደረገ እንደሆነ ነግረውን ነበር።

    አቶ አዲሱ አረጋ፥ ያ’ኔ!
    (ይድነቃቸው ከበደ)

    የህወሃት መራሹ የኢህአዴግ የአገዛዙ ሥርዓት በሕዝባዊ እንቢተኝነት የዛሬ ሦስት እና ሁለት ዓመት በሚናጥበት ወቅት፤ መስከረም ወር 2009 ዓ.ም. የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ ሕዝባዊ ትግሉን ለመቀልበስ፣ በአገዛዙ በኩል የመጨረሻ እና ትልቁ የተባለ አፋኝ አዋጅ ታውጆ ነበር።

    የአዋጁን መውጣት ተከትሎ፤ ቁጥሩ ቀላል የማይባል ዜጎች በተለያዩ ቦታዎች በኃይል በማስገደድ እስራት ተፈጽሟል። በአዋሽ አርባ፣ አዋሽ ሰባት፣ ብርሸለቆ፣ ጦላይ፣ ሰንከሌና ሌሎች ካምፖች ውስጥ ለ‹ተሃድሶ ስልጠና› በሚል ለመግለፅ የሚከብዱ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት በእነዚህ ካምፖች ውስጥ ተፈጽሟል። በተለይ ከአዲስ አበባ ተይዘን ወደ አዋሽ 7 ከገባን ታሳሪዎች በፊት አንድ ወር ቀድመው እዚሁ ካምፕ የገቡ ከኦሮሚያ ክልል የተያዙ ወጣቶች የደረሰባቸው በደል ለመግለጽ እጅግ በጣም የሚከብድ ሰቅጣጭ ነው።

    በማጎሪያ ካምፖች ውስጥ በሺዎች በማሰር ይፈጸም የነበረው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት፣ በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ተቋማት፣ በአገር ወዳደ ኢትዮጵያዊያን ዘንድ ትልቅ መነጋገሪያ ሆነ። ይህ ደግሞ በወቅቱ በአገዛዙ ሥርዓት ላይ ጫና በመፍጥር የተጀመረው ሕዝባዊ እንቢተኝነት ሌላ ተጨማሪ ጉልበት ሆነ።

    ከጥቂት ቀናት በኋላ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መኖር አለመኖሩን እናጣራለን ያሉ “በመንግስት” ፍቃድ ታጉረን የምንገኝበት ካምፕ እንዲመጡ ተደርጓል። እንዲያናግራቸው ከተመረጡ ታሳሪዎች ጋር እኛን ወክለው ያዩትን እና የደረሰባቸውን የመብት ጥሰት ተናግሯል። በወቅቱ የመንግስት ሚዲያዎች ዜና ሲያቀርብ መሠረታዊውን የመብት ጥሰት ወደ ጎን በመተው፣ በጥሩ ሆኔታ ላይ እንደምንገኝ እና ስልጠና እየተከታተልን እንደሆነ ይገልጹ ነበር።

    በዚያን ጊዜ አቶ አዲሱ አረጋ፥ ያ’ኔ በአዋሽ አርባ፣ አዋሽ ሰባት፣ ብርሸለቆ፣ ጦላይ፣ ሰንከሌና ሌሎች ካምፖች ውስጥ በመዘዋወር፤ ‘መንግስት’ ወጣቶችን አላሰረም ‹ተሃድሶ ስልጠና› እየሰጠ ነው¡¡ ለማስባል በሚደረገው ጥረት፣ መንግስታዊ ድራማ አስመስሎ ለመከወን የአንበሳውን ድርሻ በታታሪነት ከፈጸሙት መካከል አቶ አዲሱ አረጋ አንዱ ናቸው።

    በተለይ እኔ በነበርኩበት ካምፕ አዋሻ 7፤ “አይደገምም” ኢትዮጵያ ካስመዘገበችው ዕድገት አንፃር አሁን የገጠማት “ሁከትና ብጥብጥ” አይገባትም፤ የሚል እንድምታ ያለው፣ “እኛ ታሳሪዎች” ሁከትና ብጥብጥ ማቆምና ማስቆም እንዳለብን የሚያትት። ሌላኛው ደግሞ “የቀለም አብዮት” ኒዮሊበራሎች፣ ግብጽ እና ኤርትራ ኢትዮጵያ ውስጥ ብጥብጥ እና አለመረጋጋት ለመፍጠር ስለሚፈልጉ “እኛ ታሳሪዎች” ከዚህ “የቀለም አብዮት” እራሳችንን እንድንጠብቅ የሚያሳስብ “የስልጠና” አርዕስት ላይ አቶ አዲሱ አረጋ ስልጠና በመስጠት በእኛ ታሳሪዎች ላይ “እጅግ በጣም” ጎብዘውብን ነበር¡¡

    አቶ አዲሱ አረጋ፥ ያ’ኔ ማለትም የዛሬ ሁለት ዓመት፥ ሕዝባዊ እንቢተኝነቱ እንዳይቀጥል “አይደገምም” በማለት ታሳሪዎችን በማስተማር¡¡ የተጀመረው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ኒዮሊበራሎች በአገራችን “የቀለም አብዮት” ለማስነሳት እንጂ፣ መጪው ጊዜ የኢትዮጵያ ሕዳሴ መሆኑ፣ ኢትዮጵያ ቁጥር አንድ ጠላቷ ድህነት እንደሆነ እና በወቅቱ የተፈጠው የመልካም አስተዳደር ችግር ለመፍታት ጥረት እየተደረገ እንደሆነ። አቶ አዲሱ ለመናገር እንጂ ለማዳመጥ ወይም ለመጠየቅ ቅንጣት ፍላጎታ ሳይኖራቸው እሳቸው እና “መንግስታቸው” ብቻ የሚፈልጉትን ነግረውን ያ’ኔ ሄደዋል።

    እኚህ ሰው አሁን ላይ “የለውጥ ኅይል” ከሚባሉት ውስጥ አንዱ ናቸው።

    ይድነቃቸው ከበደ

    አቶ አዲሱ አረጋ


Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.