አጣየ፣ ካራቆሬ፣ ማጀቴ እና አካባው በሚኖሩ ዜጎች ላይ የታጠቁ ኃይሎች እያደረሱት ያለው ኢ-ሰብአዊ በደል

Home Forums Semonegna Stories አጣየ፣ ካራቆሬ፣ ማጀቴ እና አካባው በሚኖሩ ዜጎች ላይ የታጠቁ ኃይሎች እያደረሱት ያለው ኢ-ሰብአዊ በደል

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • Author
    Posts
  • #10519
    Anonymous
    Inactive

    በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ አካባቢዎች በተቀሰቀሰ ግጭት በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት አደረሰ
    —–

    በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ አካባቢዎች የተቀሰቀሰው ግጭት አሁንም ተባብሶ ቀጥሏል።

    ግጭቱ ትናንት ከቀኑ 9:30 ጀምሮ በአጣዬ በማጀቴና በካራ ቆሬ አካባቢዎች መባባሱም ተሰምቷል።

    ስለ ጉዳዩ የጠየቅናቸው የአጣዬ ከተማ ከንቲባ አቶ ጌታቸው በቀለ ግጭቱ በአካባቢው ነዋሪና በታጠቁት ኃይሎች መካከል መፈጠሩን ነግረውናል።

    ምክንያቱ በውል እንደማያውቁ የገለፁልን አቶ ጌታቸው የታጠቀው ኃይል ከትናንት ቅዳሜ ጀምሮ በፈፀመው ጥቃት 9 ሰዎች መገደላቸውንና በርካቶች መቁሰላቸውን ገልፀውልናል።

    ግጭቱ አሁንም ተባብሶ ቀጥሏል ያሉት ከንቲባው ቤት ለቤት ዘረፋ መጀመሩንና 3 ሰዎች ታፍነው መወሰዳቸውንም ነግረውናል።

    በአካባቢው የነበረው የክልሉ ልዩ ኃይል ጥቃቱ ከአቅሙ በላይ በመሆኑ መከላከያ ኃይል መግባቱንም ከንቲባው አያይዘው ተናግረዋል።

    የኤፍራታና ግድም ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደምሰው መሸሻ በበኩላቸው ተደራጅቶ ዘመናዊና የቡድን መሳሪያዎችን የታጠቀው ቡድን በከፈተው ጦርነት ብዙዎች ተገድለዋል ብለዋል።

    በአካቢው ያሉ የእምነት ተቋማት ጭምር ጥቃት እንደደረሰባቸው ነው አስተዳዳሪው የገለፁት።

    ዋና አስተዳዳሪው አክለውም ወደ አካባቢው የገባው የመከላከያ ኃይል ሁኔታውን ማረጋጋት እንዳልቻለ ገልፀዋል።

    ምንጭ፦ ኢቢሲ

    #10551
    Anonymous
    Inactive

    የኮሬ ማኅበረሰብ አባላት አቤቱታ
    —–

    የታጠቁ ቡድኖች በደቡብ ክልል አማሮ ወረዳ በሚገኙ የኮሬ ማኅበረሰብ አባላት ላይ ግድያ እየፈጸሙ እንደሚገኙ የማኅበረሰቡ አባላት አስታወቁ።

    የማኅበረሰቡ አባላት ትናንት በጉዳዩ ላይ በሀዋሳ ከተማ ባካሄዱት ውይይት ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖች በማኅበረስቡ አባላት ላይ የግድያ እና መፈናቀል ጥቃት እየፈጸሙ ይገኛሉ ብለዋል። መንግሥት በአካባቢው የሚንቅሳቀሱ የታጠቁ ኃይሎቸን ትጥቅ እንዲያስፍታ ፣ ተፈናቃዮችን ወደ ቀድሞ ቦታቸው እንዲመልስ እና የሕይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎችም ካሣ እንዲከፍል ጠይቀዋል። ውይይቱን የተከታተለው የሀዋሳው ዘጋቢያችን ዝርዝሩን ልኮልናል።

    ምንጭ፦ ዶቸ ቨለ

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.