ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ በታሪኩ ከፍተኛ የትርፍ ዕድገት አስመዘገበ

Home Forums Semonegna Stories ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ በታሪኩ ከፍተኛ የትርፍ ዕድገት አስመዘገበ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8388
    Semonegna
    Keymaster

    ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ በሒሳብ ዓመት ያስመዘገበው የተጣራ ትርፍ 728 ሚሊዮን ብር እንደሆነ የባንኩ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ይፋ ባደረገው ሪፖርት የተመለከተ ሲሆን፣ ይህም ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ145 በመቶ ብልጫ አለው።

    አዲስ አበባ (ኦኢባ) – ከተመሠረተ አሥረኛ ዓመቱን የያዘው ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ በታሪኩ ከፍተኛ የትርፍ ዕድገት በማስመዝገብ በ2010 ዓ.ም የሒሳብ ዓመት (fiscal year) ከታክስ በፊት 938 ሚሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ።

    ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ ቅዳሜ ጥቅምት 24 ቀን 2011 ዓ.ም ባካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ይፋ እንዳደረገው፣ የባንኩ የ2010 ዓ.ም የሒሳብ ዓመት የትርፍ መጠን ከቀድሞው የሒሳብ ዓመት ጋር ሲነጻጸር ከ140 በመቶ በላይ ዕድገት አሳይቷል።

    በቀደመው ዓመት ባንኩ ከታክስ በፊት 391 ሚሊዮን ብር ያስመዘገበ ሲሆን፣ የባንኩ ትርፍ በአንድ ዓመት ልዩነት የ547 ሚሊዮን ብር ብልጫ ያለውን ትርፍ ማስመዝገቡ የባንኩን የ2010 የሒሳብ ዓመት የትርፍ መጠን የተለየ አድርጎታል።

    ባንኩ በሒሳብ ዓመት ያስመዘገበው የተጣራ ትርፍ 728 ሚሊዮን ብር እንደሆነ የባንኩ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ይፋ ባደረገው ሪፖርት የተመለከተ ሲሆን፣ ይህም ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ145 በመቶ ብልጫ አለው።

    ኢትዮጵያ ውስጥ በማንኛውም ጊዜና ቦታ ገንዘብን በሞባይል ስልክ ለማንቀስቀስ የሚያስችሉት ሲቢኢ ብር እና አሞሌ

    ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ ያስመዘገበው የትርፍ ዕድገት ምጣኔ በባንክ ኢንዱስትሪው ከፍተኛው ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በዚህም ምክንያት የባንኩ የትርፍ ክፍፍል ወደ 54 በመቶ ከፍ ብሏል፡።

    የ2010 ዓ.ም በሒሳብ ዓመት በአብዛኛው ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበበት ሲሆን፣ የተቀማጭ ገንዘብ መጠን 19.9 ቢሊዮን ብር እንደደረሰና ጠቅላላ ሀብቱም 23.8 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተመልክቷል።

    መስከረም 11 ቀን 2001 ዓ.ም ተመሥርቶ ጥቅምት 15 ቀን 2001 ዓ.ም የመጀመሪያ ቅርንጫፉን አዲስ አበባ ውስጥ ደንበል ሲቲ ሴንተር ላይ ከፍቶ ሥራ የጀመረው ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ በአሁኑ ወቅት በመላው ሀገሪቱ ከ200 በላይ ቅርንጫፎች አሉት።

    ምንጭ፦ ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል (ኦኢባ)

    ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.