ከ466 ሺህ ብር በላይ ለግል ጥቅሟ ያዋለች ግለሰብ በእስራትና በገንዘብ ተቀጣች

Home Forums Semonegna Stories ከ466 ሺህ ብር በላይ ለግል ጥቅሟ ያዋለች ግለሰብ በእስራትና በገንዘብ ተቀጣች

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8571
    Semonegna
    Keymaster

    ደብረ ብርሃን (ኢዜአ)–በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በአንጎለላና ጠራ ወረዳ ሀሰተኛ ሰነድ በመጠቀም ከመንግሥት ካዝና ከ466 ሺህ ብር በላይ ለግል ጥቅሟ ያዋለችው ግለሰብ በ18 ዓመት ጽኑ እስራትና የገንዘብ ቅጣት ተጣለባት።

    በሰሜን ሸዋ ዞን ፍርድ ቤት የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ወ/ሪት ዘርትሁን ያዘው ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንደገለጹት ፍርድ ቤቱ በግለሰቧ ላይ ቅጣቱን የወሰነው በወረዳው ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ጽህፈት ቤት ገንዘብ ያዥ ሆና ስትሠራ የመንግሥትን ገንዘብ ለግል ጥቅሟ ማዋሏ በመረጋገጡ ነው።

    ተከሳሿ ወ/ሮ አበበች ጽጌ ከ2007 እስከ 2009 ዓ.ም ድረስ በጽህፈት ቤቱ ስትሠራ ሀሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀትና መንግሥታዊ ሰነድ በመደበቅ የሙስና ወንጀል መፈፀሟ በሰውና በሰነድ ማስረጃ እንደተረጋገጠባትም አስረድተዋል።

    ግለሰቧ በአገር አቀፍ ደረጃ በውሃና በአካባቢ ንጽህና ፕሮጀክት (WASH) ግዢ ከአቅራቢዎች ላይ የተሰበሰበ ሁለት በመቶ ገንዘብ 171 ሺህ 417ብር ለግል ጥቅም ማዋሏ ተረጋግጦባታል ነው የተባለው።

    እንዲሁም በ56 ደረሰኞች ላይ በበራሪው ትክክለኛዉን የገንዘብ መጠን በመመዝገብና የከፋዮችን ስም በመቀያየር የገቢ መጠኑን በመቀነስ ለመንግሥት መግባት የነበረበት 94 ሺህ 90 ብር ሰነድ በማበላለጥ መጠቀሟም ነው የተገለፀው። በተጨማሪም በራሪ ደረሰኞችን ለከፋይ በትክክል ቆርጣ ከሰጠች በኋላ በሁለተኛና ሦስተኛ ካርኒዎች ላይ አቀናንሳ 181ሺህ 16 ብር ለግል ጥቅሟ ማዋሏን መረጋገጡን ባለሙያዋ ገልጸዋል።

    ግለሰቧ ወንጀሉን ከፈጸሟ በኋላ ከአካባቢው በመሰወሯ ፖሊስ ወንጀለኛዋን አድኖ በመያዝ ለማረሚያ ቤት እንዲያስረክብም ትዕዛዝ ተሰጥቷል። ከዚህ በተጨማሪ ለአምስት ዓመታት ከማንኛውም የእንቅስቃሴ መብቷ እንደታገደችም ተወስኖባታል።

    በሌላ ዜና፥ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለረጅም ጊዜ ታጥረው በቆዩ ቦታዎች ንብረታቸውን በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ባላነሱት ላይ እርምጃ መውሰድ ተጀመረ።

    የከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማት ማኔጅመንት ፅህፈት ቤት የደንብ ማስከበር ፅህፈት ቤት ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በጋራ በመሆን እርምጃ መውሰድ መጀመሩን አስታውቋል።

    በዚህም ያለ ልማት ለረጅም ጊዜ ታጥረው የቆዩ ቦታዎች ላይ የሚገኙ የአጥር ቆርቆሮዎችን ማንሳት መጀመሩን ገልጿል።

    አስተዳደሩ ባልለሙ ቦታዎች ላይ ንብረቶቻቸውን ያስቀመጡ አካላት ንብረታቸውን እንዲያነሱ ከሳምንት በፊት መግለጫ መስጠቱ የሚታወስ ነው። ይሁን እንጅ እነዚህ አካላት ንብረቶቻቸውን ማንሳት ባለመጀመራቸው ምክንያት አስተዳደሩ በዛሬው ዕለት ወደ እርምጃ መግባቱን ነው የገለጸው።

    አስተዳደሩ የሕዝብን ሃብት ለተገቢው ልማትና ለነዋሪዎች ተጠቃሚነት እንዲውል በጀመረው ተግባር ህገ ወጥነትን እንደማይታገስና፥ ህግ የማስከበር ሃላፊነቱን እንደሚወጣ መግለጹን ከከተማዋ ከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

    ምንጮች፦ ኢዜአ እና ኤፍቢሲ

    ለግል ጥቅሟ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.