ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ ስለተከሰከሰው አውሮፕላን አብራሪ ያሰራጨው ዘገባ ከእውነት የራቀ ነው ― የኢትዮጵያ አየር መንገድ

Home Forums Semonegna Stories ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ ስለተከሰከሰው አውሮፕላን አብራሪ ያሰራጨው ዘገባ ከእውነት የራቀ ነው ― የኢትዮጵያ አየር መንገድ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #10368
    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– ከ12 ቀናት በፊት የተከሰከሰው ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነው የቦይንግ 737 ማክስ 8 (Boeing 737 MAX 8) አውሮፕን አብራሪ ተገቢዉን የምሰለ በረራ (simulator) ስልጠና አልወሰደም በሚል መጋቢት 11 ቀን 2011 ዓ.ም. ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ (The New York Times) ሰላም ገብረኪዳን በተባለች ትውልደ ኢትዮጵያዊት ጋዜጠኛ ፀሐፊነት ያወጣው ዘገባ ከእውነት የራቀ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ።

    “ምንም እንኳን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ማክስ ምስለ በረራ ቢኖረውም የተከሰከሰውን አውሮፕላን ያበር የነበረው ፓይለት የዚህ ምስለ በረራ ስልጠና አልተሰጠውም” (Ethiopian Airlines had a Max 8 simulator, but pilot on doomed flight didn’t receive training on it) በሚል ርዕስ ኒው ዮርክ ታይምስ ያወጣው ዘገባው ከእውነት የራቀና ኃላፊነት የጎደለው መሆኑንም አየር መንገዱ አመለክቷል።

    የአደጋው መንስዔ እየተጣራ ባለበት በአሁኑ ሰዓት ሁሉም አካላት እንዲህ መሰል አሳሳች መረጃ ከማሰራጨት እንዲታቀቡም አየር በሚገባ መንገዱ በአጽንዖት አሳስቧል።

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መረጃ፥ የተከሰከሰው አውሮፕላን አብራሪ ሁሉንም አግባብነት ያላቸው የበረራ ስልጠናዎችን መውሰዱን አስታውቋል።

    ● SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest

    አውሮፕላን አብራሪው በቦይንግ የአውሮፕን አምራች ኩባንያ (The Boeing Company) እና በአሜሪካ አቪዬሽን አስተዳደር (US Federal Aviation Administration) የተቀመጡ ሁሉንም የበረራ ስልጠናዎችን መውሰዱንም ነው በመግለጫው የገለጸው።

    ዋና አብራሪው ከወራት በፊት በኢንዶኔዥያው ላየን ኤየር (Lion Air) በደረሰው ተመሳሳይ የአውሮፕላን አደጋ ጋር በተያያዘ አስፈላጊዉን የአደጋ ጊዜ የበረራ መመሪያ በቂ ግንዛቤ እንደተሰጠዉም ተገልጿል።

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ አብራሪዎቹን ለማሰልጠን የሚያስችሉ የተሟሉ 7 ምስለ በረራዎች ወይም የበረራ ማሰልጠኛዎች እንዳሉት አስታውቋል። በአሁን ወቅት ብቁና የተሟሉ ኪው 400፣ ቢ737 ኤን ጂ፣ ቢ 737 ማክስ፣ ቢ 767 ፣ ቢ 787 ፣ ቢ 777 እና ኤ 350 የተሰኙ ሰባት ምስለ በረራዎች እንዳሉት ይፋ አድርጓል።

    በአፍሪካም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከተሟላ የስልጠና መሣሪያ ጋር በቂ ስልጠና ከሚሰጡት ጥቂት ተቋማት መካከል አንዱ መሆኑንም ነው ያስታወቀው – የኢትዮጵያ አየር መንገድ። ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ ባልተለመደ ሁኔታ ከስልጠና ጋር ተያይዞ ለመሠረተ ልማት ግንባታ ከግማሽ ቢሊየን ዶላር በላይ ወጭ እንዳደረገ ተነግሯል።

    የዓለም አቀፍ ሕግን በመከተል የአደጋው መንስዔ ተጣርቶ ይፋ እስከሚደረግ ድረስ በትዕግስት መጠበቅ ተገቢ መሆኑንም አየር መንገዱ አስታውቋል።

    ምንጭ፡- የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ


Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.