የልዑል አለማየሁ አፅም ወደ እናት ሀገሩ እንዲመለስ ተጠየቀ

Home Forums Semonegna Stories የልዑል አለማየሁ አፅም ወደ እናት ሀገሩ እንዲመለስ ተጠየቀ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #10387
    Semonegna
    Keymaster

    በቪክቶሪያ እና አልበርት ሙዚየም የሚገኙ የመቅደላ ስብስብ ቅርሶች በአጭር ጊዜ ሊመለሱ ይችላሉ
    —–

    ለንደን የሚገኙ ቅርሶች የሚያዙበት ሁኔታና የሚተዳደሩበት ሕግ በጣም ጠንካራ ነው። በየትኛውም አጋጣሚ እጃቸው ላይ የገባ ቅርስ በሕጉ መሠረት ይተዳደራል። ስለሆነም የእኛም ቅርሶች የዚሁ አካል ናቸው ማለት ነው። ይሁን እንጂ እነዚህ ቅርሶች ለኢትዮጵያውያን የማንነትና የእድገት መሠረቶች ናቸውና ሊመለሱልን እንደሚገባ በተደጋጋሚ ሲጠየቁ ቆይተዋል።

    እ.ኤ.አ በ2018 ከወደ ቪክቶሪያ እና አልበርት ሙዚየም ብቅ ያለው መረጃ በረጅም ጊዜ ውሰት ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ማድረግ እንደሚቻል ገለጸ። የማንን ቅርስ ማን አበዳሪ? ማንስ ተበዳሪ? እንዴት አይነት ድፍረት ነው?ወዘተ… ብለን ተቆጨን። እነሆ የይመለሱልን የሕዝብ ጥያቄው በክብርት ዶ/ር ሂሩት ካሳው (የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር)፣ በልዑካን ቡድኑና በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል ቅርሶቹ ተጎበኙ፤ ጥያቄውም ቀረበ ሰፊ ውይይትም ተደረገ። ዳይሬክተሩ ዶ/ር ትሪስትራም ኸንት /Tristram Hunt/ ጥያቄው ተገቢ መሆኑን ‘ውሰት’ የሚለው ቃልም ለኢትዮጵያውያን ከባድ መሆኑን እንደተረዱት በመግለጽ የተቸገሩት የሕግ ጉዳይ በመሆኑና ምላሽ ለመስጠት ያለን አማራጭ ይህ ብቻ ስለሆነ ነው አሉ። አክለውም ያለን አማራጭ ይህን ቀዳዳ በመጠቀም ሊስተካከሉ የሚችሉ አባባሎችን ተጠቅመን የሚመለሱበትን ሁኔታ መፍጠር ይህን ካላደረግን ግን በሕጉ ላይ ጸንተን ወደፊት የሚሆነውን ነገር መመልከት ይኖርብናል ብለዋል። በመቀጠልም ከክብርት ሚንስትሯም የተለያዩ ማሳመኛ ምክንያቶች ከቀረቡ በኋላ በሙዚየሙ፣ በኤምባሲውና በሚንስቴር መሥሪያ ቤቱ በኩል ጊዜ ሳይሰጠው በአስቸኳይ መግባቢያ ሰነዱን ካለው ሕግ ጋር በማይጋጭና የኢትዮጵያን ጥያቄ ሊመልስ በሚችልበት ሁኔታ ሠርተን በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት እልባት እንደሚያገኝ ዳይሬክተሩ ገልጸው ስምምነት ላይ ተደርሷል።

    በፈጣንና ታታሪ አመራሮችና ባለሙያዎች የተደራጀው ኤምባሲም ባለው ሙሉ አቅምና ጊዜ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በመወጣት ቅርሶቹ ወደ አገራቸው እንዲገቡ እንደሚያደርጉ ሃላፊነቱን መቀበላቸውን ክቡር አምባሳደሩ ፍሰሃ ሻወል ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.