አምቦ ዩኒቨርሲቲ በሰላም ጎዳና
—–
በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመው የሰላም ፎረም ለመማር ማስተማር ሥራ አስተዋጽዖ ማድረጉ ተገለጸ።
በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመው የማህበረሰብ አቀፍ የሰላም ፎረም የመማር ማስተማር ሥራን በሁሉም የዩኒቨርሲቲው ካምፓሶች በተያዘለት መርሀ ግብር ለማስቀጠል አስተዋጽዖ ማድረጉን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ታደሰ ቀነአ ገለጹ።
የሰላም ፎረሙ በሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት አስመልክቶ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት የተቀናጀ ጥረት እያደረገ ያለ መሆኑን ዶክተር ታደሰ ገልጸዋል፡፡
በዚህም ውጤታማ ሆነዋል ባሏቸው የወሊሶ፣ የጉደርና የአዋሮ ካምፓሶች የዘመኑ ትምህርት በጥሩ ሁኔታ እንደቀጠለ ተናግረዋል፡፡ ሰላም ከሌላ ትምህርት እንደሚቆምና ይህም ተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸውን ከመጉዳት ባለፈ በሀገርም ላይ ጫና ስለሚፈጥር ሁሉም ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት መረባረብ እንዳለበት ዶክተር ታደሰ ጠቁመዋል፡፡
ምንጭ፦ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር