በትግራይ ክልል የሰቲት ሑመራ ከተማ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ

Home Forums Semonegna Stories በትግራይ ክልል የሰቲት ሑመራ ከተማ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8663
    Semonegna
    Keymaster

    ሑመራ (ኢዜአ)– በትግራይ ክልል የሰቲት ሑመራ ከተማ ነዋሪዎች የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ክልላዊና ሀገራዊ ጉዳዮችን አስመልክተው በቅርቡ ላደረጉት ንግግር ድጋፋቸውን በሰላማዊ ሰልፍ ገለጹ።

    ነዋሪዎቹ ለዶ/ር ደብረጽዮን ያላቸውን ድጋፍ ለመግለጽ ትናንት በተሽከርካሪዎች የጀመሩት ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ ወጣቶችን ጨምሮ በሰቲት ሑመራ ከተማ ነዋሪዎች ተጠናክሮ ቀጥሏል።

    በሰልፉ ላይ የተሳተፉት ወጣቶች፣ ማኅበራትና ነዋሪዎች “የትግራይ ሕዝብ ታሪክ የሚያኮራ እንጂ የሚያሳፍር ታሪክ የለውም! የሕግ በላይነት ይከበር! በሙስና የተጠረጠሩ በቁጥጥር መዋላቸውን ብንደግፍም በሙስናና ኢ-ሰብዓዊ አያያዝ ሽፋን ብሔር ተኮር ጥቃት ይቁም! የውጭ ጣልቃ ገብነት ይቁም!” የሚሉና ሌሎች የተለያዩ መፈክሮች ይዘው ሰልፉ ላይ ታይተዋል። የትግራይ ሕዝብ ለሰላም፣ ለእኩልነት፣ ለፍትህና ለዴሞክራሲ የቆመ ነው ሲሉም ድምጻቸውን አሰምተዋል።

    መንግስት የሕግ በላይነት ለማስከበር የጀመረው እንቅስቃሴ እንደሚደግፉት የገለጹት ሰላማዊ ሰልፈኞቹ፣ ሕግን የማስከበር ሥራው በሁሉም አካላትና የመሥሪያ ቤት ዘርፎች እንዲተገበር ጠይቀዋል።

    በሰልፉ ላይ የተሳተፉ የቃፍታ ሑመራ ወረዳ ነዋሪ አቶ ተመስገን ካሕሳይ “የትግራይሕዝብ በእኩልነትና በፍትህ ያምናል፤ ለዓመታት የታገለውም የሕግ በላይነት እንዲረጋገጥ ነው” በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

    የትግራይ ሕዝብ ከሌሎች ወገኖቹ ጋር መስዋዕትነት የከፈለው ለህግ ልዕልና መረጋገጥ ነው – የክልሉ መንግስት

    ወጣት የዕብዮ ኃይሉ የተባለ ሌላው የወረዳው ነዋሪ በበኩሉ “እኛ ሕግ የጣሰና በሙስና የተዘፈቀ መደበቂያ አንሆንም፤ መጠየቅ ያለባቸው በትግራይ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ክልሎች ያሉ በመሆኑ ሕግ የማስከበር ሥራ በሁሉም ሊተገበር ይገባል” ብሏል። የትግራይ ሕዝብ ከሌሎች ኢትዮጵያዊ ወንድሞቹ ጋር ሆኖ መታገሉን ገልጾ አሁንም የሕግ የበላይነትን ለማስከበር በሚደረጉ ጥረቶች ማንኛውም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆኑን አመልክቷል።

    የሰቲት ሑሞራ ከተማ ነዋሪ አቶ ሰለሞን አረጋይ በበኩላቸው “ዶ/ር ደብረጽዮን ያደረጉት ንግግር ሰላምና ልማትን የሚፈልግ ማንኛውንም ብሔር የሚመለከት በመሆኑ ድጋፌን ለመግለጽ ወጥቻለሁ” ሲሉ ገልጿል።

    The recent action to impose the rule of law in Ethiopia is getting political agenda – Dr. Debretsion

    ወጣት መሰለ ዕቁባይ በበኩሉ ስለ ሰላም እየዘመሩ የትግራይ ሕዝብን ሰላም ለማወክ መሞከር አግባብ ያልሆነና ተቀባይነት እንደሌለው ተናግሯል። የትግራይ ሕዝብ ከሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች ጋር ሆኖ የታገለው ሰላምና የሕግ የበላይነት እንዲረጋገጥ በመሆኑ ማንኛውንም ጭቆና እንደማይሸከም አመልክቷል።

    በሰልፉ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ርስቁ አለማው እንዳሉት ሰላምና የሕግ የበላይነት እንዲከበር የትግራይ ሕዝብ ከሌሎች የኢትዮጵያ ወገኖቹ ጋር በመሆን መስዋዕት ከፍሏል። በአሁኑ ወቅትም ከሌሎች ሰላም ወዳድ የአገሪቱ ሕዝቦች ጋር በመሆን ሕግ ለማስከበር ድምጹን በሰላማዊ መንገድ እያሰማ መሆኑን ተናግረዋል።

    “በዞናችን የማንነት ጥያቄ ባይኖርም አንዳንድ ሰላም የማይፈልጉ አካላት ሰላሙን ለመንሳት ሌት ተቀን ቢሠሩም ሕዝቡ በትዕግስት እና በሰላም ድምጹን እያሰማ ነው” ብለዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    ሰቲት ሑመራ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.