Home › Forums › Semonegna Stories › የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔ ጊዜያዊ ውጤትን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ (ምርጫ ቦርድ)
Tagged: ሲዳማ, የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔ, የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን, የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
- This topic has 1 reply, 2 voices, and was last updated 4 years, 11 months ago by
Anonymous.
-
AuthorPosts
-
June 18, 2020 at 11:03 pm #14857
Anonymous
Inactiveየሲዳማ ሕዝብ በክልል ለመደራጀት ያቀረበው ጥያቄ በሕገ-መንግሥቱ መሠረት ምላሽ ማግኘቱን የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል መንግሥት የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ለማ ገዙሜ ተናግረዋል።
የሲዳማ ሕዝብ በክልል ለመደራጀት ያቀረበው ጥያቄ በሕገ-መንግሥቱ መሠረት ምላሽ አግኝቷል
ሀዋሳ (ኢዜአ/ፋና) – የሲዳማ ሕዝብ በክልል ለመደራጀት ላቀረበው ጥያቄ ምላሽ ማግኘት (ራስን በራስ የማስተዳደር መብት መረጋገጥ) የሕገ-መንግሥቱና የፌዴራል ሥርዓቱ ውጤት መሆኑን የደቡብ ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ገለፁ።
አፈ-ጉባኤው አቶ ለማ ገዙሜ ይህንን የገለፁት የደቡብ ክልል ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ የሲዳማ ሕዝብ በክልል የመደራጀት ጥያቄ የመጨረሻ ሕጋዊ ሂደት የሆነው የሥልጣን ርክክብን አስመልክቶ በሰጡት የእንኳን ደስ አላችሁ ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።
የሲዳማ ሕዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ ዓመታትን ያስቆጠረና መስዋዕትነት የተከፈለበት ትግል ሲደረግ መቆየቱን አውስተዋል። በተለይ ከ2010 ዓ.ም. አጋማሽ የለውጥ ጉዞ በኋላ ቀደም ሲል በሕዝቡ ይነሱ የነበሩ ጥያቄዎች እውቅና ተሰጥቷቸው ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን ተከትሎ በክልል የመደራጀት መብቱን በሕዝበ ውሳኔ ማረጋገጡን ገልጸዋል።
በዛሬው ዕለት የደቡብ ክልል ምክር ቤት የመጨረሻ ሕጋዊ ሂደት ሆነውን የሥልጣን ርክክብ ሥርዓት ማከናወኑን ያስረዱት አቶ ለማ ገዙሜ፥ ለመላው የሲዳማ ሕዝብ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። የሕዝቡ እራስን በራስ የማስተዳደር መብት መረጋገጥ የሕገ-መንግሥቱና የፌዴራል ሥርዓቱ ውጤት መሆኑንም ገልፀዋል።
“የሲዳማ ሕዝብ ለዘመናት ያቆየውን ከሌሎች ጋር ተዋዶ የመኖር እሴቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ጽኑ እምነት አለው” ብለዋል።
በሌሎች የክልሉ አካባቢዎችም የተነሱ የአደረጃጀት ጥያቄዎች ሕገ-መንግሥታዊ ሂደታቸውን ጠብቀው መልስ እንደሚያገኙ ጠቁመው በየአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ጉዳዩን በትዕግስት መከታተል እንደሚገባቸው አመልክተዋል።
ከዚሁ ዜና ጋር በተያያዘ፥ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው ለመላው የሲዳማ ሕዝብ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት ማስተላለፋቸውን ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት (ፋና) ዘግቧል።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው እንደገለጹት፥ የሲዳማ ሕዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር የረጅም ዘመናት ጥያቄ በሕገ-መንግሥቱ መሠረት ምላሽ አግኝቷል።
የሲዳማ ሕዝብ ከሌሎች የክልሉ ሕዝቦች ጋር በጋራ ተቻችሎና ተግባብቶ የኖረ ደማቅ ታሪክ ያለው ሕዝብ ነው ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፥ ቀደም ሲል የነበረው አንድነት መተሳሰብና አብሮነት የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።
ክልል ለአስተዳደራዊ ሥራ የሚያገለግል እንጂ በሕዝቦች መካከል ድንበር ማኖር እንዳልሆነ የተናገሩት አቶ ርስቱ፥ የሕዝቡ የቆየ መቻቻል እና እርስ በርስ መደጋገፍ ከምን ጊዜውም በላይ ልቆ እንዲጠነክር ምኞታቸውን ገልጸዋል።
የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ከአዲሱ የሲዳማ ክልል ጋር በመቀናጀት ለጋራ እድገትና ተጠቃሚነት ጠንክሮ በመሥራት የሀገራችንን እድገት ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር እንተጋለን ብለዋል።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ለመላው የሲዳማ ሕዝብ እንኳን ደስ ያላችሁ በማለት መልዕክታቸውን ማስተላለፋቸውን ከክልሉ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ምንጮች፦ ኢዜአ/ፋና
-
AuthorPosts
- You must be logged in to reply to this topic.