የስኬታማ ሴቶችን ተሞክሮ ማስፋፋት ይጠበቃል – ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ
—–
ክቡር የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ የስኬታማ ሴቶችን ተሞክሮ ማስፋፋት እንደሚጠበቅ ገለጹ፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር “የላቀ ትኩረትና ቁርጠኝነት ለሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት” በሚል መሪ ቃል የማርች 8 በዓልን አክብሯል፡፡ በዓሉን ምክንያት በማድረግም የብዙ ሳይንሳዊ ፈጠራ ስራዎች ባለቤት የሆኑት ዶክተር ፋንታዬ ይማሙ ተሞክሯዎቻቸውን ለሌሎች ተመራማሪ ሴቶች እንድያካፍሉ ማድረጉ ይታወቃል፡፡
ፕሮፌሰር አፈወርቅ ለፕሮግራሙ ታዳሚ ሴት መምህራን፣ ተማሪዎችና ተመራማሪዎች፣ ለመስሪያ ቤቱ ሴት ሰራተኞች የዶክተር ፋንታዬን ፈለግ በመከተል ልምዳቸውን ማስፋፋት ይጠበቅባችኹል፣ ዓላማችን ብዙ ዶ/ር ፋንታዬዎችን ማየት ነው ብለዋል፡፡
ዶክተር ፋንታዬ በሳይንሱ ዘርፍ ለአገራችን የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን በማበርከታቸው ለተደረገላቸው ግብዣና የምስጋና የምስክር ወረቀት መስሪያ ቤቱን በማመስገን እንደ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ዓይነት አስታዋሽ ያስፈልገናልም ብለዋል፡፡
ምንጭ፦ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር