ኢትዮጵያ ለምትገነባው የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧ ከጅቡቲ ጋር ስምምነት ተፈራረመች

Home Forums Semonegna Stories ኢትዮጵያ ለምትገነባው የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧ ከጅቡቲ ጋር ስምምነት ተፈራረመች

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #9720
    Semonegna
    Keymaster

    ግንባታው በሦስት ዓመት የጊዜ ገደብ ውስጥ የሚጠናቀቀው የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ከኦጋዴን ኢላላና ካሉብ (ሶማሊ ክልል) ተነስቶ ጅቡቲ ወደብ የሚደርስ ሲሆን ጅቡቲ ላይ ነዳጁ ይቀነባበራል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ኢትዮጵያ ለምትገነባው የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧ ከጅቡቲ ጋር ስምምነት ተፈራረመች።

    በኢትዮጵያ እና ጅቡቲ መንግስታት መካከል የተፈረመው ስምምነት ኢትዮጵያ ለምትገነባው የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧ በጅቡቲ ምድር ለማቀነባባሪያ የሚሆን መሬት ለማግኘትና ጥበቃ ለማድረግ የሚያስችል ነው።

    ስምምነቱን የፈረሙት በኢትዮጵያ የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር ሳሙኤል ኡርካቶ (ዶ/ር) ና በጅቡቲ የነዳጅና ተፈጥሮ ሃብት ሚኒስትር ሚስተር ዮኒስ አሊ ጒዲ ናቸው።

    760 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ማስተላለፊያ ቧንቧ ግንባታው 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር የሚፈጅ ሲሆን 700 ኪሎ ሜትር በኢትዮጵያ፣ 60 ኪሎ ሜትሩ ደግሞ በጅቡቲ ምድር የሚያልፍ ነው።

    ◌ ALSO: Ethiopia is ready to use Red Sea Ports of Assab and Massawa of Eritrea

    ግንባታው በሦስት ዓመት የጊዜ ገደብ ውስጥ የሚጠናቀቀው የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ከኦጋዴን ኢላላና ካሉብ (ሶማሊ ክልል) ተነስቶ ጅቡቲ ወደብ የሚደርስ ሲሆን ጅቡቲ ላይ ነዳጁ ይቀነባበራል።

    የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትሩ ዶ/ር ሳሙኤል ኡርካቶ ስምምነቱ የሁለቱን አገራት የረጅም ጊዜ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ግንኙነት እንደሚያጠናክረው ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እየገነባችው ያለው የተፈጥሮ ሃብት መጠቀሚያ መሠረተ ልማት የአገራቱን የጋራ ተጠቃሚነት የሚያጠናክር ነው ብለዋል። በከፍተኛ ድርድር ውሳኔ ያገኘው ይህ ስምምነት ዓለም አቀፍ መስፈርት ያሟላ መሆኑንም ዶ/ር ሳሙኤል አክለዋል።

    የጅቡቲው የነዳጅና ተፈጥሮ ሃብት ሚኒስትር በበኩላቸው ስምምነቱ የሁለቱን ወንድማማች አገራት የጋራ ተጠቃሚነት ስለሚያጎለብት ጅቡቲ ጥበቃውን ታጠናክራለች ነው ያሉት። የመሠረተ ልማት ግንባታው በጅቡቲ በማለፉ ከምታገኘው ጥቅም ባሻገር በርካታ ዜጎቿን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ገልጸዋል።

    የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧውን መቀመጫውን ሆንግ ኮንግ ከተማ ያደረገው ያቻይናው GCL-Poly ኩባንያ እንደሚገነባው ተጠቁሟል። GCL-Poly ኩባንያ የተቋቋመው እ.ኤ.አ በ1996 ሲሆን፥ በተለያዩ የኃይል ማመንጫ ግንባታዎች ላይ የተሰማራው ጎልደን ኮንኮርድ ሆልዲንግስ ሊሚትድ (Golden Concord Group Limited) የተባለው ግዙፍ ድርጅት ቅርንጫፍ (subsidiary) ነው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    [caption id="attachment_9717" align="aligncenter" width="600"]የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ PHOTO: Ethiopian Broadcasting Corporation[/caption]


Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.