የተከሰተውን የአተት ወረርሽኝ ለመቆጣጠር ግብረ ሃይል ተቋቋመ
—–
በአምስት ክልሎች የተከሰተውን የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) ወረርሽኝ ለመቆጣጠር ግብረ ኃይል መቋቋሙን የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አሰታወቀ።
በአምስት ክልልች በተከሰተው የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) ወረርሽኝ እስከአሁን የ15 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ ፡፡
ወረርሽኙን በአፋጣኝ ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የህክምና ግብአቶች በሁሉም ክልሎች ወደሚገኙ የኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅርቦት ኤጀንሲ መጋዘኖች መላካቸውንም ኢንስቲትዩቱ ገልጿል፡፡
እስካሁን ድረስ በኦሮሚያ 138፣ በአማራ 198፣ በሱማሌ 33 እና በትግራይ 8፤ በድምሩ 377 ሰዎች በአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) ተይዘዋል ብሏል ኢንስቲትዩቱ።
ምንጭ፦ ኢቢሲ