ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን ለ26ኛ ጊዜ ተከበረ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በሐዋሳ ከተማ ተከብሯል።

Home Forums Semonegna Stories ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን ለ26ኛ ጊዜ ተከበረ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በሐዋሳ ከተማ ተከብሯል።

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8794
    Semonegna
    Keymaster

    በተበባሩት መንግስታት ድርጅት ስር የሚከበረው ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን ዘንድሮ የሚከበረው ለ26ኛ ጊዜ ሲሆን የዘንድሮ ክብረ በዓል መሪ ቃልም “የአካል ጉዳተኞችን ማበረታት፣ የአካል ጉዳተኞችን ታቃፊነትና እኩልነት ማረጋገጥ” የሚል ነው።

    ሀዋሳ (ሰሞነኛ ) – ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ26ኛ ጊዜ በሀዋሳ ከተማ ተከበረ።

    የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ በበዓሉ ላይ ተገኝተው አንደገለጹት፥ አካታችነትና እኩልነትን በማስፈን የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሁሉም የህበረተሰብ ክፍል የጋራ ጉዳይ መሆን አለበት ብለዋል።

    አሁን ላይ የአካል ጉዳተኞች ችግሮች ተቀርፈዋል ማለት ባይቻልም፥ ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠት በእየደረጃው አካታች እቅዶችን በማቀድ ለተግባራዊነታቸው እንቅሰቃሴ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

    ለአካል ጉዳተኞች የተለያዩ ድጋፎች ማድረጉ የተጀመረ ሲሆን፥ ሀገር ውስጥ ዊልቼር ለማምረት መታቀዱም ነው የተገለጸው።

    እንደ ፋና (ኤፍ.ቢ.ሲ.) ዘገባ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሚሊየን ማቲያስ በበኩላቸው፥ አካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ በርካታ ስራወች እየተከናዎኑ መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህ በፊት በክልሉ አርባ ምንጭ የአረጋውያን ማዕከል ብቻ የነበረ ሲሆን፥ አሁን ላይ በቤንች ማጅ ዞን ተጨማሪ የአረጋውያን ማዕከል ለመክፈት አየተሠራ መሆኑን ጠቁዋል።

    በበዓሉ ለመታደም የተገኙት የአካል ጉዳተኞች በበኩላቸው፥ የትምህርት አገልግሎት ለማግኘት አስካሁን ድረስ ችግሮች ያሉባቸው መሆኑን ነው የተናገሩት። አገልግሎቱ የሚያገኙበት እድል ቢፈጠርም እንኳ ረጅም ርቀት መጓዝ ግድ እንደሚላቸውም አስረድተዋል። ከዚህም ሌላ የአካል ጉዳተኞችን የተመለከቱ መመሪያዎችና ደንቦች ላይ የአፈጻጸም ክፍተት የሚታይ መሆኑን አመላክተዋል። ለአብነትም አንዳንድ የሚወጡ የሥራ ማስታወቂያዎች ሙሉ ጤንነትን የሚጠይቁና የአካል ጉዳተኞችን የማይጋብዙ መሆኑን አንስተዋል።

    አብዘኞቹ የአገለግሎት መስጫ ተቋማትም የአካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረጉ አለመሆናቸውንም ገልጸዋል።

    በተበባሩት መንግስታት ድርጅት ስር የሚከበረው ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን ዘንድሮ የሚከበረው ለ26ኛ ጊዜ (እ.ኤ.አ. ከ1992 ጀምሮ) ሲሆን የዘንድሮ ክብረ በዓል መሪ ቃልም “የአካል ጉዳተኞችን ማበረታት፣ የአካል ጉዳተኞችን ታቃፊነትና እኩልነት ማረጋገጥ” (“Empowering persons with disabilities and ensuring inclusiveness and equality”) የሚል ነው።

    ኢትዮጵያ ውስጥ ለአካል ጉዳት እና ለአካል ጉዳተኞች የሚሰጠው አመለካከት የተሳሳተ በመሆኑ ሀገሪቱ ውስጥ የአካል ጉዳተኞችን ቁጥር በትክክል ማወቅ እጅግ አዳጋች እንደሆነና፣ የሚገመተውም ቁጥር ከትክክለኛው ቁጥር ዝቅተኛ እንደሆነ (under-reported) የተለያዩ ጥናቶች ያመለታሉ።

    አብዛኛው የኢትዮጵያ ህብረተሰብ አካል ጉዳተኝነትን ከፈጣሪ እንደመጣ ቁጣ ወይም መርገም እንደሚመለከተውና አካል ጉዳተኛ የሆነ ሰው ያላቸው ቤተሰቦችም ይሁኑ ህብተረሰቡ ሰለአካል ጉዳተኛው፣ ስለሚያስፈልገው ነገር ብሎም እንደማንኛውም ሰው ሙሉ ፍላጎትና መብት እንዳለው በግልጽ ከመወያየት ይልቅ መደበቅና ማሸሽን ይመርጣሉ። በዚህም ምክንያት አካል ጉዳተኞች አጅግ አዳጋች የሆነ ሕይወት እንዲገፉ ይገደዳሉ።

    በሀገሪቱ የአካል ጉዳተኞችን ጉዳይ በበላይ የሚመለከተውና የሚቆጣጠረው የሠራተኛነ ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሲሆን፥ በዚህ ሚኒስቴር ስር የሚገኝው የማኅበራዊ ደህንነት ልማት ማስፋፊያ ዳይሬክቶሬት የአካል ጉዳነኞችን ከሥራ እና ከማኅበራዊ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በፌደራል ደረጃ ይመለከታል፣ ያስተባብራል።

    በተጨማሪም የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ብሔራዊ ማኅበራት ፌዴሬሽን (FENAPD) ጥላ ስር ተደራጅተው ከ አካል ጉዳተኞች ጋር በተያያዘ የሚንቀሳቀሱ ስድስት ብሔራዊ ድርጅቶች ይገኛሉ። እነሱም፦

    1. የኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ብሔራዊ ማኅበር፣
    2. የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ብሔራዊ ማኅበር፣
    3. የኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ብሔራዊ ማኅበር፣
    4. የኢትዮጵያ ማየትና መስማት የተሳናቸው ብሔራዊ ማኅበር፣
    5. የኢትዮጵያ ሥጋ ደዌ ተጠቂዎች ብሔራዊ ማኅበር፣ እና
    6. የኢትዮጵያ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው ብሔራዊ ማኅበር ናቸው።

    ከእነዚህ ብሔራዊ ማኅበራት በተጨማሪ የአካል ጉዳተኞችን ታቃፊነትና እኩልነት በማረጋገጥ እንቅስቃሴዎች ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ጉልህ አስተዋጽዖ እያደረጉ የሚገኙ ማኅበራት ያሉ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ፦

    1. የኢትዮጵያ ብሔራዊ የአካል ጉዳተኞች ማኅበራት ኔትዎርክ (ENDAN)፣
    2. የኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኛ ሴቶች ብሔራዊ ማኅበር፣
    3. የትግራይ አካል ጉዳተኛ የቀድሞ ወታደሮች ማኅበር (ማኅበር ጉዱአት ኲናት ትግራይ) እና
    4. በኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞችና ልማት ማዕከል (ECDD) ተጠቃሽ ናቸው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.