Home › Forums › Semonegna Stories › አድዋ – የጥቁሮች ሕዝቦች የነጻነት እርሾ
Tagged: Global alliance for Justice the Ethiopian Case, በርሊን, አድዋ, አጼ ምኒልክ, የአድዋ ድል, የአድዋ ጦርነት, የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ
- This topic has 3 replies, 2 voices, and was last updated 6 years, 3 months ago by
Anonymous.
-
AuthorPosts
-
February 28, 2019 at 1:23 am #9952
Anonymous
Inactiveተማሪዎች እና መምህራን 123ኛውን የአድዋን ድል እየዘከሩ ነው
—–‹‹3ቱ የካቲቶች›› የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ እስከ የካቲት 30 ይቆያል
የ‹መለከት አፀደ ሕጻናትና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት› ተማሪዎች በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ሥር በሚገኘው በብላቴን ጌታ ኅሩይ ወ/ሥላሴ የሥነ ጥበባት ማዕከል በመገኘት 123ኛውን የአድዋን ድል እየዘከሩ ነው፡፡
የአድዋን ድል በማስመልከትም ያዘጋጁትን ቴአትር አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የልጆች ክፍል አዘጋጆች በቦታው ተገኝተው የተማሪዎቹን ጉብኝትና ቴአትር ቀረጻ አድርገዋል፡፡
ሕጻናቱ ባቀረቡት ቴአትር ላይ አገር ስለመውደድ፣ ስለፍቅር እና የፆታ እኩልነትን አስመልክተው አስተማሪ ጭብጦችን አንስተዋል፡፡
‹‹3ቱ የካቲቶች›› የተሰኘው የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ እስከ የካቲት 30 ስለሚቆይ ሁላችሁም እንድትጎበኙት ተጋብዛችኋል፡፡
—————————-
አድራሻች፡- የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ፣ ከፒያሳ ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል በሚወስደው መንገድ፣ ሆስፒታሉ አካባቢ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጉለሌ ቅርንጫፍን አልፎ በሚገኘው ቅያስ 500 ሜትር ገባ ብሎ፡፡ምንጭ፡- የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ
February 28, 2019 at 1:50 am #9955Anonymous
Inactiveኢትዮጵያ በጣሊያን ወራሪ መንግስት ለተፈፀመባት ዘግናኝ እልቂት ተገቢ ካሳ እንድትጠይቅ ጥሪ ቀረበ
—–ከ82 ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ በወራሪው የኢጣሊያን መንግስት በተፈፀመባት ወረራ በግፍ ለተሰውት ንፁሃን ዜጐችና ለወደመባት ንብረት ተገቢ ካሳ ሊከፈላት እንደሚገባ የሚጠይቅ አለም አቀፍ ንቅናቄ መጀመሩ ይፋ ሆነ፡፡
አለምአቀፍ ህብረት ለፍትህ የኢትዮጵያ ጉዳይ (Global alliance for Justice the Ethiopian Case) የተባለው አለም አቀፍ ድርጅት ይፋ ያደረገው ይኸው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ የየካቲት 12/1929 ዘግናኝ እልቂትን ጨምሮ ጣሊያን በአምስት ዓመቱ የወረራ ዘመን ከአንድ ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያንን በግፍ የጨፈጨፈች ሲሆን ለዚህ ኢ-ሰብአዊ ድርጊቷ ለኢትዮጵያ መንግስት ተገቢ ካሳ ልትከፍልና ህዝቡን በይፋ ይቅርታ ልትጠይቅ ይገባል ተብሏል፡፡
በድርጅቱ ይፋ የተደረገው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ አገራት በተለያዩ ጊዜያት ወረራ በመፈፀም በግፍ ለጨፈጨፏቸው ንፁሀን ዜጐችና ላወደሙት ንብረት በቢሊዮኖች የሚቆጠር ካሳ እየከፈሉና ህዝቡን በይፋ ይቅርታ እየጠየቁ ይገኛሉ። በደል የተፈፀመባቸው አገራትም ሊከፈላቸው የሚገባውን የካሳ መጠን በመግለጽ፣ ጥያቄ እያቀረቡ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት ግን እስከአሁን ምንም አይነት ጥያቄ ሳያቀርብ ቀርቷል፡፡
February 28, 2019 at 1:54 am #9956Anonymous
Inactiveለ123ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል የሚደረገው ዝግጅት መጠናቀቁን የአዲስ አበባ አስተዳደር አስታወቀ
—–123ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ምክንያት በማድረግ ለበዓሉ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።
የከተማ አስተዳደሩ የኪነ ጥበብ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ዛሬ በሰጠው መግለጫ በዓሉ የአድዋ ድልን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በሚያስችሉ የተለያዩ መርሃ ግብሮች ታስቦ ይውላል ብለዋል።
የቢሮው ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ በሰጡት መግለጫ የአድዋ ድል የአባቶች ተጋድሎ መስዋዕትነት የሚዘከርበት በዓል ነው ብለዋል።
በዋዜማው በጣይቱ ሆቴል የኪነጥበብ ድግስ መዘጋጀቱም በመግለጫው ተገልጿል።
በተመሳሳይ በዋዜማው በሚኒሊክ አደባባይ የተለያዩ ትያትር ቤቶች የባህል ትሪዒቶችን ጨምሮ የተለያዩ ዝግጅቶችን ያቀርባሉ።
በዕለቱም በሚኒሊክ አደባባይ ድሉን በማስመልከት የተለያዩ መርሃግብሮች ይከናወናሉ።
በምኒሊክ አደባባይ የሚኖረው መርሃግብር ከተጠናቀቀ በኋላም ከሚኒሊክ አደባባይ እስከአድዋ ድልድይድረስ የእግር ጉዞ ይካሄዳል።
ድሉን ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማስተላለፍ በማሰብ በተጨማሪም በዕለቱ በእንጦጦ ቤተመንግስት ግብር የማብላት ስነስርዓት ይከናወናል።
ከ8 ሰዓት ጀምሮ ደግሞ በመስቀል አደባባይ አንጋፋና ወጣት አርቲስቶች የተለያዩ ዝግጅቶችን እንደሚያቀርቡም ይጠበቃል።
በተያያዘም 123 የአድዋ ድል ለማሰብ የደራሼ ባህል ቡድን አባላት አዲስ አበባ ገብተዋል።
የአድዋ ድል ከ123 ዓመታት በፊት በአድዋ ተራሮች ላይ የተደረገ ኢትዮጵያውን አባቶች አውሮፓዊውን ቅኝ ገዢ ጣሊያንን መክተው የመለሱበት መሆኑ ይታወሳል።
ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
-
AuthorPosts
- You must be logged in to reply to this topic.