የኢትዮጵያዊያን ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ከምርጫ ቦርድ ሕጋዊ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማግኘቱን ተከትሎ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ

Home Forums Semonegna Stories የኢትዮጵያዊያን ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ከምርጫ ቦርድ ሕጋዊ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማግኘቱን ተከትሎ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #12589
    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – በእነ ይልቃል ጌትነት (ኢንጂነር) የተቋቋመው የኢትዮጵያዊያን ሀገር አቀፍ ንቅናቄ (ኢሀን) ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሕጋዊ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማግኘቱን ተከትሎ ፓርቲው የወደፊቱን ትግል የትኩረት ነጥቦች አስመልክቶ ጥቅምት 27 ቀን 2012 ዓ.ም. በጽሕፈት ቤቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

    የኢትዮጵያውያ ሀገር አቀፍ ንቅናቄ በመግለጫው የፓርቲውን ራዕይ፣ ዓላማ፣ ተልዕኮ፣ ሀገራዊ እይታና የሚመራበትን ርዕዮተ-ዓለም በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቷል። በተጨማሪም በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች – ማለትም ሰሞኑን በሀገራችን ማንነትን መሠረት ባደረገ የተፈፀመውን ጥቃት እና የአዲስ አበባ ከተማን የባለቤትነት ጥያቄና የፖለቲካ ምርጫን በተመለከተ ያለውን አቋም ይፋ አድርጓል።

    ‘ነፃነት ከሌለ ምርጫ የለም። ሕዝባዊ አስተዳደር ለመትከልና የተለያዩ የፖለቲካ ሀሳብ አማራጮች ለሕዝብ አቅርቦ ሕዝቡ የፈለገውን እንዲመርጥ በቅድሚያ የዜጎችን ሙሉ ነፃነት ማክበርና ማስከበር ያስፈልጋል። ነፃነት ማለት በራሱ የአማራጮች መኖር ማለት ነው። ስለሆነም ነፃነት በሌለበት ምርጫ ሊኖር አይችልም። ለሕዝባዊ አስተዳደር እውን መሆን የዜጎችን ሙሉ ነፃነት ማስከበር የማይታለፍ ቅድመ-ሁኔታ ነው’ የሚለው የጋዜጣዊ መግለጫው ተቀዳሚ መልዕክት ነበር።

    አዲስ አበባ ከተማን በተመለከተ ደግሞ፥ አዲስ አበባ ከተማ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን የጋራ ምልክታችን እንደሆነች፤ የአዲስ አበባ ሕዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር መብቱ የተጠበቀ ሆኖ አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስለሆነች፣ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን የጋራ ምልክት ሆና እንድትቀጥል ኢሀን ጠንክሮ እንደሚሠራ አስታውቋል። አዲስ አበባ የኢትዮጵያን ፖለቲካና ኢኮኖሚ በተመለከተ ያላትን ታሪካዊ ድርሻ እንድትወጣ የኢትዮጵያዊያን ሀገር አቀፍ ንቅናቄ በሙሉ አቅሙ እንደሚሠራም ጋዜጣዊ መግለጫው አትቷል።

    በመጨረሻም ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል፣ በድሬድዋ ከተማ እና በሀረር ከተማ ማንነትን መሠረት ባደረገ መልኩ በዜጎች ላይ የተፈፀመው ዘግናኝ ጭፍጨፋ በገለልተኛ አካል ተጣርቶ ለሕዝብ ይፋ እንዲደረግ የኢትዮጵያዊያን ሀገር አቀፍ ንቅናቄ አበክሮ እንደሚንቀሳቀስ፤ እንዲህ ዓይነቱን ዓይን ያወጣ አስነዋሪ ተግባር ለፖለቲካ ፍላጎት ሲባል ማለባበስና ማድበስበስ በንፁሀን ሕይወት መሳለቅ ከመሆኑም በላይ ለሀገራችን ሰላምና መረጋጋት ላይ ትልቅ ደመና ያዘለ ጥፋት በመሆኑ፣ ፓርቲው ጉዳዩን ከምንጩ ጀምሮ ማጥራትና የማያዳግም እርምጃ መውሰድ ከሀገር ደኅንነት /national security issue) ጋር የተያያዘ ከባድ ታሪካዊ ኃላፊነት ነው ብሎ እንደሚያምን በጋዜጥዊ መግለጫው አስታውቋል።

    የኢትዮጵያዊያን ሀገር አቀፍ ንቅናቄ የሥራ አስፈፃሚ አባላት፦

    1. ኢ/ር ይልቃል ጌትነት – ሊቀመንበር
    2. አቶ ወረታው ዋሴ – ምክትል ሊቀመንበር እና የሕዝብ ግንኙነት
    3. ወ/ሮ መዓዛ መሐመድ – የውጭ ግንኙነት ኃላፊ
    4. አቶ አወቀ ተዘራ – የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ
    5. አቶ እስክንድር ጥላሁን – የጥናትና ስትራቴጂ ኃላፊ
    6. አቶመሳይአማዶ – የሕግጉዳይኃላፊ
    7. ወ/ሪትምዕራፍይመር – የፋይናንስጉዳይኃላፊ
    8. አቶቴዎድሮስአሰፋ – የአባላትመረጃናደኅንነትጉዳይኃላፊ
    9. ወ/ሪትወይንሸትሞላ – የሴቶችናየወጣቶችጉዳይኃላፊናቸው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኢትዮጵያዊያን ሀገር አቀፍ ንቅናቄ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.