ለፊልምና ለባህል ፖሊሲዎቻችን ተፈጻሚነት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎና አጋርነት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ
—–
የኢፌዲሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በባህል ቱሪዝምና ስፖርት ዘርፎች ለተሰማሩ ወጣቶች ያዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር በባህልና ፊልም ፖሊሲዎቻችን ዙሪያ ለወጣቶች በተደረገ ገለጻ፣ ማኅበራዊና ስነ-ምግባራዊ እሴቶቻችንን የሚያበረታቱ ባህሎቻችን በተመለከተና ወጣቶች ለስፖርታዊ ጨዋነት በሚኖራቸው አበርክቶ ዙሪያ በቀረበ የመነሻ ጽሁፍ በተደረገ ውይይት ተጠናቋል።
በውይይቱም በተለይ ለፊልምና ለባህል ፖሊሲዎቻችን ውጤታማነትና ተፈጻሚነት በየደረጃው ያሉ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ የዘርፉ ባለሞያዎች፣ ባለሀብቶች፣ ግለሰቦችና እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በጋራና በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ተገልጿል።
ምንጭ፦ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር