የኢትዮጵያ የፊልም ፖሊሲ የማስፈጸሚያ ሰነድ እንደሚያስፈልገው ተጠቆመ

Home Forums Semonegna Stories የኢትዮጵያ የፊልም ፖሊሲ የማስፈጸሚያ ሰነድ እንደሚያስፈልገው ተጠቆመ

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • Author
    Posts
  • #8634
    Anonymous
    Inactive

    የኢትዮጵያ ፊልም ሰሪዎች ማህበርን ላለፉት ስድስት አመታት በምክትል ፕሬዝዳንትነት ሲመራ የቆየውና በአሁኑ ሰዓት የማህበሩ ስራ አስፈፃሚ ሆኖ በማገልገል ላይ እሚገኘው አርቲስት ደሳለኝ ሃሉ የአዲስ አበባ ሲኒማ ቤቶች አስተዳደር የቦርድ አባል ሆኖ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ የሹመት ደብዳቤ ተሰጥቶታል።

    ደሳለኝ ሃይሉ ከዘጠኝ ወራት በፊት የፀደቀው የኢትዮጵያ ፊልም ፖሊሲ እውን እንዲሆን ከታገሉ ፊልም ባለሞያዎች መሃል አንዱ ነው።

    የአርቲስቱ ሹመት በተለይም በሲኒማ ቤቶች አካባቢ በስፋት ሚታየውን ግልፅ ሌብነት ና የተጋነነ የአዳራሽ ኪራይ ያስቀረዋል ተብሎ ይታሰባል።

    #10707
    Anonymous
    Inactive

    ለፊልምና ለባህል ፖሊሲዎቻችን ተፈጻሚነት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎና አጋርነት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ
    —–

    የኢፌዲሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በባህል ቱሪዝምና ስፖርት ዘርፎች ለተሰማሩ ወጣቶች ያዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር በባህልና ፊልም ፖሊሲዎቻችን ዙሪያ ለወጣቶች በተደረገ ገለጻ፣ ማኅበራዊና ስነ-ምግባራዊ እሴቶቻችንን የሚያበረታቱ ባህሎቻችን በተመለከተና ወጣቶች ለስፖርታዊ ጨዋነት በሚኖራቸው አበርክቶ ዙሪያ በቀረበ የመነሻ ጽሁፍ በተደረገ ውይይት ተጠናቋል።

    በውይይቱም በተለይ ለፊልምና ለባህል ፖሊሲዎቻችን ውጤታማነትና ተፈጻሚነት በየደረጃው ያሉ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ የዘርፉ ባለሞያዎች፣ ባለሀብቶች፣ ግለሰቦችና እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በጋራና በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ተገልጿል።

    ምንጭ፦ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.