Home › Forums › Semonegna Stories › የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ መቋቋሙን ተከትሎ ወደ ተግባር ለመግባት የመዋቅርና የሕግ ማዕቀፍ ሥራን አጠናቀቀ
- This topic has 2 replies, 2 voices, and was last updated 6 years, 3 months ago by
Anonymous.
-
AuthorPosts
-
February 16, 2019 at 4:59 pm #9738
Anonymous
Inactiveበአሜሪካ ሀገር የሚኖሩ የዲያሥፖራ ማህበር አባላት ስልጠና ሰጡ።
—–በውጪ አገራት ዩኒቨርስቲዎች የሚያስተምሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሙሁራንና ተመራማሪዎች /TASFA/ በሚል ተደራጅተው ስልጠና እየሰጡ ይገኛሉ።
ከ 08-10/06/2011 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ በአዲስ አበባ ከተማ ኦሮሞ ባህል አደራሽ የኢፌዲሪ የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር፣ የውሀ መስኖና ኢነርጂ ሚንስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የህግ ባለሙያዎች እና ከኦሮሚያ ትምህርት፣ ሲቢል ሰርቪስ እና ከተለያዩ ቢሮዎች ለሚሰሩ አመራሮችና ባለሙያዎች የፕሮጀክት ማኔጅሜት ስልጠና በመስጠት ላይ ናቸው።
ፕሮግራሙን የከፈቱት የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት የሳይንስና አካዳሚክ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀኔራል ዶክተር ኤባ ሚጃና እያንዳንዳችን ያስተማረችንን ድሀ አገራችንን አቅማችን በፈቀደው ብድሯን ለመመለስ ተረባርበን መስራት አለብን ብለዋል።
የማህበሩ አመራሮችና አባላትም በበኩላቸው በራሳቸው ፈቃድና ወጭ መጥተው ያለባቸውን የሙያ ግዴታ ለመወጣት እየሰሩ ሲሆን ይሄን ተግባር በማስፍት ስልጠናው በቴክኖጂ ታግዞ ኦንላይን ትምህርት ጭምር እንደሚሰጥ 1000 ሰልጣኞች ለማሰልጠን ከመንግስት ጋር በመተባበር በታቀደው መሰረትየዛሬው ለ4ኛ ዙር 400 ሰልጣኞች ናቸው ቀጣይም በተመሳሳይ እንሰራለን ማለታቸውን የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዘግቧል፡፡
February 17, 2019 at 7:25 pm #9760Anonymous
Inactiveውክልናን በቪድዮ፡ የውክልና ሂደትን በ20 ደቂቃ
—–ኬብሮን ነዋሪነቱ በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት ሲሆን ኢትዮጵያ ለሚገኙ ወዳጅ ዘመዶቹ ውክልና ለመስጠት አስቦ ሂደቱን በአሜሪካን ሃገር ቢጀምርም ነገሮች እንዳሰባቸው ቀላል ሆነው አላገኛቸውም። በዚህ ምክንያት የተነሳም የውክልና አሰጣጥ ሥርዓቱን ለመቀየር ቆርጬ ተነሳሁ ይላል፤ ኬብሮን ።
እንዳለውም አደረገው። የውክልና ሥርዓቱን በማዘመን የሚወስደውን ጊዜ ከወራት ወደ ደቂቃዎች ለማሳጠር ችሏል። እንዴት?
ኬብሮን ደጀኔ ‘ሲሊከን ቫሊ’ በመባል የሚታወቀው የአሜሪካ ቴክኖሎጂ እምብርት ውስጥ ‘ቪዲቸር’ የሚባል ድርጅት ካቋቋመ አምስት ዓመት ሊሆነው ነው። አሁን ደግሞ ከኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመሆን የውልና ማስረጃን አሠራር ለማፋጠን ትልቅ ሚና ለመጫወት በቅቷል።
በዛሬው ዕለት በ’ቪዲቸር’ የተደገፈው የውክልና አሠራር በዋሺንግተን ዲሲ ባለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተመርቋል። ለሕዝብ አገልግሎትም ሥራ ላይ እንዲውል ይፋ ተደርጓል።
የተጓተተ የውክልና ሂደት
ከሁለት ዓመት በፊት ነበር ከውክልና አሠራር ጋር ኬብሮን ግብ ግብ የገጠመው። በኢትዮጵያ ያለን የንግድ ተቋም ዘመድ እንዲያንቀሳቅስለት በማሰብ የውክልና ሂደቱን ቢጀምርም በካሊፎርኒያና በአካባቢው ውክልና የሚጽፍለትም ሆነ የሚያረጋግጥለት ማግኘት ሳይችል ቀረ። ከስድሰት ሰዓታት የአየር ጉዞ በኋላ በዋሽንግተን ዲሲ ሂደቱን አስጀመረ። ውክልና የመስጠት ተግባሩ ግን ቀላል አልነበረም።
11 የተለያዩ ነገሮችን ማሟላት ይጠይቅ እንደነበር እንዲሁም በሕግ ባለሙያ አረጋግጦ ቢያንስ 40 ቀናት መጠበቅ ግድ እንሆነ ይናገራል። ከስንት ወጣ ውረድ በኋላ ኢትዮጵያ የደረሰው የውክልና ወረቀት ስህተት አለበት በመባሉ በድጋሚ ለማሠራት መገደዱንም ኬብሮን ይናገራል።
እንደዚህ ዓይነት ችግሮች መኖራቸውን ከዚህ ቀደም ከብዙ ሰዎች ይሰማ የነበረ ቢሆንም በእርሱ ላይ ከደረሰበት በኋላ አሠራሩን ለመቀየር ቆርጦ እንደተነሳ ይናገራል። በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ‘ቪዲቸር’ መካከል በተደረሰው ስምምነት መሰረት የውልና ማስረጃን አሠራር ለመቀየርና ‘ዲጂታላይዝ’ ወይም ‘አውቶሜት’ ለማድረግም ‘ቪዲቸር’ ለተሰኘው የኬብሮን ተቋም ፈቃድ ተሰጠ።
-
AuthorPosts
- You must be logged in to reply to this topic.