የኦሮሞ ቋንቋ እና ባህል ማበልፀጊያ ክበብ በድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተቋቋመ

Home Forums Semonegna Stories የኦሮሞ ቋንቋ እና ባህል ማበልፀጊያ ክበብ በድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተቋቋመ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #11426
    Semonegna
    Keymaster

    ክበቡ የአፋን ኦሮሞ ቋንቋ እና ባህል እንዲሁም ተዛማጅ እሴቶችን በማስተዋወቅ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ የነበረውን ፍቅር፣ ሰላምና አብሮ የመኖር እሴት ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ጠንክሮ እንደሚሠራ እምነታቸው መሆኑን የድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ተናግረዋል።

    ድሬ ዳዋ (ሰሞነኛ) – “ቋንቋችንን፣ ባህላችንን፣ እሴቶቻችንንና ታርካችንን ጠብቀን ለመጪው ትውልድ ማስረከብ የአሁኑ ትውልድ ግዴታ ነው።” በሚል መሪ ቃል የአፋን ኦሮሞ ቋንቋ እና ባህል ማበልፀጊያ ክበብ በድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተቋቁሟል። በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ እና ባህል ክበብ ምሥረታ ቀደም ብለው ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ያሬድ ማሞ፣ የኦሮሞ ቋንቋ እና ባህል ክበብ ፕሬዝዳንት ተማሪ ገሊማ፣ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት ተማሪ ጥበቡ ሙሉጌታ እንዲሁም የ2011 ዓ.ም የተማሪዎች ምረቃ ኮሚቴ ሰብሳቢ ተማሪ ቢቅላ ጋሮምሳ የክበቡን መመሥረት በማብሰር መርሃ ግብሩን ይፋ አድርገዋል።

    ክበቡ የአፋን ኦሮሞ ቋንቋ እና ባህልን በማስተዋወቅ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ የነበረውን ፍቅርና ሰላም እንዲሁም አብሮ የመኖር እሴት ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ጠንክሮ እንደሚሠራ እምነታቸው መሆኑን የድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ያሬድ ማሞ ተናግረዋል። ዶ/ር ያሬድ አያይዘውም ክበቡ ለሌላ ዓላማና እኩይ ተግባር እንደማይውል ሙሉ እምነታቸው መሆኑን በመግለጽ፤ ግንባር ቀደም ክበብ በመሆኑ ሌሎች ብሔሮችም ተመሳሳይ ጥያቄ ይዘው ቢመጡ ክበቡ እነሱን የማገዝ ሃላፊነት እንዳለበት አሳስበዋል። በመጨረሻም ዶ/ር ያሬድ ተማሪዎቻችን ከተለያዩ ብሔር ብሔረሰብ በመምጣታቸው የራሳቸውን ቋንቋና ባህል ለማስተዋወቅ ክበብ ለመመሥረት ቢፈልጉ ዩኒቨርሲቲው እኩል ድጋፍ እንደሚያደርግም ገልፀዋል።

    በምስረታው ላይ ታዋቂ ሰዎች፣ አባገዳዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፎበታል። የኦሮሞን ባህል ከማስተዋወቅ አንጻርም የኦሮሞ ባህላዊ ምግቦች ቅምሻ ሥነ-ስርዓትና የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች አለባበስ ትዕይንትም ተካሂዷል። በእለቱ የአፋን ኦሮሞ ቋንቋ፣ ባህልና ታርክ ላይ የተመሠረተ ጥናታዊ ጽሁፍ በዶ/ር ተሾሜ ኤጌሬ የጅማ ዩኒቨርሲቲ የኦሮሞ ገዳ እንስቲትዩት ኤክስክዩቲቭ ዳይሬክተር፡ በአፋን ኦሮሞ ቋንቋና ታርክ ጥናታዊ ጽሁፍ አቅርቦ በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል።

    የዩኒቨርሲቲው የአፋን ኦሮሞ ቋንቋና ባህል ክበብ ፕሬዝዳንት እና መሥራች ተማሪ ገልማ ብዱ እንደተናገረው ክበቡ ኃይማኖት ተኮር ነገሮችን ከማንፀባረቅና ከማንኛውም የፖለቲካ አመለካከት የፀዳመሆኑን በመግለጽ የኦሮሞን ቋንቋ እና ባህል ከሌሎች ብሔር ብሔረሰቦች ጋር በማዋሀድ ልምድ ልውውጥ በማድረግ በልዩነታችን ውስጥ ውበት አንድነታችን የሚጠናከርበትና የሚካሄድበት ክበብ ነው ብሏል። በክበቡም የሌሎች ብሄር ብሄረሰቦች ተወላጆች አባል ሆነው መሳተፍና አኩሪ የኢትዮጵያዊነት መልካም ባህላቸውን ማበልጸግ እንደሚችሉ ተናግረዋል።

    በዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት ስር ክበባትን ማደራጀት በሚፈቅደው መመሪያ መሰረት የኦሮምኛ ቋንቋና ባህልን ለማበልፀግ እንደ አንድ ክበብ የኦሮምኛን ቋንቋና ባህል ክበብ ሚያዝያ 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ተመሥርቷል። የክበቡም ምሥረታ በአፍራን ቀሎ ባንድ ጣዕመ ዜማ፣ መነባነብ በገጣሚ እና ደራሲ ሲሳይ ዘለገሃሬ እና በዩኒቨርሲቲያችን ተማሪዎች ቀርቧል። በዩኒቨርሲቲያችን እስታዲየም ከአዲስ አበባ በተጋበዙ ታዋቂ የኦሮምኛ ዘፋኞች፣ የቀድሞ የአፍራን ቀሎ መሥራቾችና ዘፋኞች ተገኝቷል። እንዲሁም የማነቃቂያ ንግግሮች፣ የዕውቅና እና የስጦታ ሥነ-ስርዓቶችም ተካሂዷል።

    ምንጭ፦ ድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኦሮሞ ቋንቋ እና ባህል


Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.