በኢትዮጵያ መንግሥት እየተፈጸመ ያለዉ የሰብዓዊ መብት ረገጣ በነፃ እና ገለልተኛ አካል ምርመራ ሊደረግበት ይገባል ― ኦነግ

Home Forums Semonegna Stories በኢትዮጵያ መንግሥት እየተፈጸመ ያለዉ የሰብዓዊ መብት ረገጣ በነፃ እና ገለልተኛ አካል ምርመራ ሊደረግበት ይገባል ― ኦነግ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #13493
    Anonymous
    Inactive

    በኢትዮጵያ መንግሥት እየተፈጸመ ያለዉ የሰብዓዊ መብት ረገጣ በነፃ እና ገለልተኛ አካል ምርመራ ሊደረግበት ይገባል
    የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) መግለጫ

    ከምዕራብ ኦሮሚያ (የወለጋ ዞኖች) ቴሌፎንና ኢንተርኔትን የመሳሰሉት የመገናኛ አገልግሎቶች በመንግሥት ከተቋረጡ አንድ ወር አለፈ። ከዚህም የተነሳ የዕለት ተዕለት ክስተቶችን በጊዜዉ ከነበቂ መረጃ ጋር ማግኘት አዳጋች ቢሆንም እንኳ የመንግሥት ወታደሮችና ታጣቂዎች በሰላማዊ (ትጥቅ-አልባ) ዜጎች ላይ እያካሄዱ ባሉት ግድያ የሰዎች ሕይወት እንደቅጠል እየረገፈ መሆኑ መተለያየ መንገድ እየተሰማ ነዉ። በተለይም በሁለት ዞኖች (ምዕራብ ወለጋ እና ቄሌም ወለጋ) ዉስጥ የኢትዮጵያ መንግሥት ወታደሮች በሕዝቡ ላይ እየፈጸሙ ያሉትን ግድያና ጭፍጨፋ በቃላት መግለጽ እንኳን ይከብዳል። የሰብዓዊ መብት ጥሰትና የጦር ወንጀል የሚሉት ቃላቶችም በትክክልና በበቂ ሁኔታ ልገልጹት አይችሉም። በደቡብ ኦሮሚያ (በጉጂ ዞኖች) ያለዉ ሁኔታም እምብዛም ከዚህ የተለየ አይደለም። በዚህ መልኩ ከአንድ ዓመት በላይ በወታደራዊ አስተዳደር (ኮማንድ ፖስት) ሥር በሕዝቡ ላይ እየደረሰ ያለዉን እሮሮና ስቃይ በተለያዩ ጊዜያት ገልጸን መፍትሄ እንድፈለግለት ብንወተዉትም እስካሁን የሕዝባችን ኡኡታና ችግሩ ተገቢዉን ተሰሚነት ሊያገኝ አልቻለም።

    ባሁኑ ጊዜ በተጠቀሱት ቦታዎች በተለይና በተለያዩ የኦሮሚያ አከባቢዎች ባጠቃላይ በሰላማዊ (ትጥቅ-አልባ) ዜጎች ላይ የሚፈጸም ግድያና ጭፍጨፋ፣ የጅምላ እስር፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸዉ መባረር፣ ባጠቃላይ በሕዝባችን ላይ እየደረሰ ያለዉ የሰብዓዊ መብት ረገጣና የጦር ወንጀል (war crime) ከመቼዉም ጊዜ ባላይ ዘግናኝና ከባድ ሆኗል። በነፃና ገለልተኛ አካል የሚደረግ ምርመራ፣ እንዲሁም አስቸኳይ መፍትሄ የሚፈልግ አንገብጋቢ ጉዳይ ነዉ ብለንም እናምናለን።

    ሆን ተብሎ በዶ/ር አብይ አህመድ በሚመራዉ የኢትዮጵያ መንግሥት በሰላማዊ ሕዝባችን ላይ እየተፈጸመ ያለዉን ይህንን እሮሮና ሰቆቃን እጅግ አጥብቀን እናወግዛለን። ይህ እሮሮና መከራ ባስቸኳይ እንድቆምም አበክረን እንጠይቃለን። ይህ ችግር ባስቸኳይ ካልተገታ በስተቀር ከዚህም ወደባሰ ሁኔታ አድጎ ከማንም ቁጥጥር ዉጪ ልሆን እንደሚችል ስጋታችን እየጨመረ መሆኑንም አሁንም በድጋሚ አስረግጠን ልንገልጽ እንወዳለን። ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ የሕይወት መጥፋትና የንብረት ዉድመትን ጨምሮ እስካሁን ለደረሱትና በቃጣይም ልደርሱ ለሚችሉት ጉዳቶች ሁሉ ተጠያቂዉ የኢትዮጵያ መንግሥት (የዶ/ር አብይ አህመድ አስተዳደር) መሆኑንም ግልጽ እናደርጋለን።

    በመጨረሻም መፍትሄ ይሁን ዘንድ የሚከተሉት እርምጃዎች እንድወሰዱ ኦነግ በአጽንኦት ይጠይቃል፦

    1. በግድያና ጭፍጨፋ፣ በእስራት እና በማንኛዉም መልኩ በሰላማዊ ዜጎች ላይ በመንግሥት እየተካሄደ ያለዉ ይህ እሮሮና ማሰቃየት ባስቸኳይ እንዲቆምና ይህንን እያካሄዱ ያሉት የመንግሥት ኃይሎች (ወታደሮች) ወደ ካምፕ እንዲመለሱ፤
    2. ያሉት ችግሮች በዉይይትና በሰላም መፍትሄ የሚያገኙበትን ሁኔታ መንግሥት እንዲያመቻች፤
    3. ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ የተለያየ ጉዳት የደረሰባቸዉ እና ቀዬአቸዉን ለቆ ለመሸሽ የተገደዱ ሰዎች ወደ ቀዬአቸዉ ተመልሶ ስላማይ ኑሮዋቸዉን እንዲኖሩ፣ ከደረሰባቸዉ ጉዳት የሚያገግሙበት እገዛም እንዲደረግላቸዉ። ያለምንም ጥፋትና ህጋዊ ዉሳኔ በተለያዩ ቦታዎች የታሠሩት እንዲፈቱ እና በኢፍትሃዊ መንገድና በተለያዩ ሴራዎች ከትምህርት ገበታቸዉ የተለዩ ተማሪዎች ወደ ትምህርታቸዉ የሚመለሱበት ሁኔታ ባስቸኳይ ተመቻችቶላቸዉ እንዲመለሱ እንዲደረግ፤
    4. በሰላማዊ ሰዎች ላይ እየተፈጸመ ያለዉን ግፍና ሰቆቃ፣ በዚህም እየደረሰ ያለዉን ጉዳት በተመለከተ በነፃና ገለልተኛ አካል አስፈላጊዉ ምርመራ (international investigation) እንዲደረግበት።

    ድል ለሰፊዉ ሕዝብ!
    የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)
    ጥር 23 ቀን 2012 ዓ.ም.

    የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.